Get Mystery Box with random crypto!

የስብዕና ልህቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የሰርጥ አድራሻ: @human_intelligence
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 89.04K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-07-17 23:51:06 መሰውር - ኘሌቶ

ምንጭ ፦ ፍልስፍና (ከዘርዐ ያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ)
ፀሀፊ ፦ ፍሉይ አለም

በመንገድህ ላይ አንዲት አሮጊት አጋጠመችህ፤ እናም ይህቺ ሴት ትንሽ፣ ግን እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነን ስጦታ ሰጠችህ - አስማተኛ ቀለበት!

ይህም ቀለበት አንተን ለሌሎች እንዳትታይ አድርጎ ይሰውርሃል፤ ወደፈለግከው ስፍራ መጓዝ ትችላለህ፤ ማንም ሰው አንተን ማየት አይችልም፡፡

ጥያቄውም ይህ ነው በዚህ ቀለበት ምን ታደርጋለህ? ይህን አስማታዊ ኃይል እንዴት ትጠቀመዋለህ?

“የጋይጂ ቀለበት” ሪፐብሊክ በተሰኘው የፕሌቶ ዘመን አይሽሬ ስራ ውስጥ እናገኘዋለን፡፡ መጽሐፉ የፕሌቶ ታላቅ ወንድም ስለሆነውና ግላውኮን ጋይጂ ስለተባለ አንድ ተራ በግ ጠባቂ ታሪክ ይነግረናል።

ይህ እረኛ ከክርስቶስ መወለድ ሰባት መቶ አመታት በፊት የሊድያ ግዛት ተብላ በምትጠራው ስፍራ ይኖር ነበር፡፡ (ይህን ግዛት አሁን ላይ በቱርክ ውስጥ እናገኘዋለን።)

ፕሌቶ ታሪኩን እንዲህ ይተርከዋል፡-

ከእለታት በአንዱ ቀን በእጅጉ ሃይለኛ
የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በሊድያ ግዛት ውስጥ ተከሰተ፡፡ በምድር ገጽ ላይም ትልቅ መሰንጠቅ ተፈጠረ፡፡ በስንጥቁ መሃልም እረኛው ጋይጂ አንድ የተደበቀ ዋሻ ተመለከተ፡፡ በዋሻው ውስጥም ጋይጂ ከነሐስ የተሰራ የፈረስ ሐውልት አገኘ፡፡ በዚህ ሐውልት ውስጥ በከፊል የበሰበሰ የአንድ ግዙፍ ሰው ሙት አካል ይገኝበት ነበር፡፡ በአስክሬኑ የቀኝ እጅ አንደኛው ጣት ላይም ወርቃማ ቀለበት ያብረቀርቅ ነበር፡፡ እናም ጋይጂ ይህንን ቀለበት ለራሱ ወሰደው፡፡

እረኛው ይህ ቀለበት ተራ ቀለበት እንዳልነበረ ለመረዳት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ በቀለበቱ አናት ላይ ያለችውን ጌጥ ሲያሽከረክራት፣ ጋይጂ ሰው እንዳያየው ሆኖ ተሰወረ፡፡ ቀለበቱ ለጋይጂ የመሰወርን ኃይል ሰጠው።

አስደናቂ የመሰወር ኃይልን እንዳገኘም፣ ይህ ተራ የበጎች እረኛ ወደ ቤተ መንግስት ቅጥር ዘለቀ፡፡ በዚያን ዕለት ምሽትም ከንግስቲቷ ጋር ተኛ፡፡ ንጉሱንም ገደለው፡፡ ንግስናንም ተቀበለ፡፡ እናም ራሱን የሊድያ ግዛት ገዢ አድርጎ ሾመ።

ፕሌቶ በዚህ ታሪክ ውስጥ ለማስተላለፍ የሞከረው ዋነኛ ሃሳብ ቢኖር ይህ ነው ሰዎች መጥፎ ድርጊቶችን የማያደርጉት ብያዝስ በሚል ፍራቻ ነው።

ሙሉ ለሙሉ የማንታይበት እና የምንሰወርበት ኃይል ቢኖረን - ከውርደት፣ ከመያዝ አልያም ከመታየት ፍራቻ እንላቀቃለን፡፡ ፕሌቶም - የመሰውርን ኃይል ያገኘ እና የሌላን ሰው ንብረት ላለመዝረፍ ያሰበ አልያም መጥፎ ተግባርን መፈጸም ያልፈለገ ቢኖር፣ እርሱ የአለማችን ሞኝ ሰው ነው' ይለናል፡፡

አንተስ የመሰወር ኃይል ቢኖርህ ምን ታደርጋለህ?

በአጠገብህ ያለ ጓደኛህን ጠይቀው፤ ራስህንም ጠይቅ፡፡

የሚያስገርም፣ የሚያስቅ አልያም የሚያሳቅቅ ምላሽን ታገኛለህ ። እናስ የመሰውር ኃይል ቢሰጥህ ባንክ ቤት አትዘርፍም? ልክ እንደ ጋይጂ ወደ ቤተመንግስት ለመግባት አትሞክርም? ከዚህም ሲከፋ ለመናገር የሚከብዱ ወንጀሎችንስ አትፈጽምም?

እናም... እኛን ወንጀልን ከመፈጸም የከለከለን ነገር ቢኖር “ሰው ምን ይለኛል' የሚለው ሃሳብ ብቻ ነው።

የፕሌቶ 'ሰዎች መልካም የሚሆኑት በምርጫቸው ሳይሆን ተገደው ነው' የሚለው ሃሳብ ለዘመናት ብዙ ፈላስፋዎችን አጨቃጭቋል። ሆኖም ይህ የጋይጂ ቀለበት ከሁለት ሺ አመታት በላይ ያስቆጠረ አፈ-ታሪክ ቢሆንም፣ ከምንግዜም በላይ አሁን ላይ ላለነው ሰዎችም የሚሰራ ምሳሌ ነው።

ለምሳሌ፤ ትክክለኛ ማንነታቸውን የማይገልጽ የፌስቡክ አካውንት ያላቸው ግለሰቦች፣ ማን እንደሆኑ አይታወቁምና እጅግ በዘቀጠ ሁናቴ ጸያፍ ስድቦችን ሲወራወሩ አልያም ጠብ አጫሪ እና በህግ ሊያስጠይቋቸው የሚችሉ የጥላቻ ንግግሮችን ሲዘሩ ይውላሉ፡፡

ሌላ ምሳሌ የሚሆነን እና የዘመናዊው ዓለም የመሰውር ቀለበት የሆነው ገንዘብ ነው፡፡ አስተውለህ ከሆነ የናጠጡ ሃብታሞች ምን ያህልም ጥፋት ቢያጠፉ ከህግ አይን የሚሰውራቸው ኃይል አላቸው፡፡ በገንዘባቸው ከምንም አይነት የወንጀል ውንጀላ ነጻ ይሆናሉ፡፡ ይህ ደግሞ በእጅጉ ጨካኝ የሆኑ እና ስለ ሌላው ግድ የሌላቸውን ህሊና አልባ ሰዎችን ፈጥሯል።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
15.4K views20:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 18:23:15 ውድ አልማዞች!
•••••••
የግመል ነጋዴው በገበያው ለሽያጭ ከቀረቡት ግመሎች መካከል በአንዱ እጅግ ስለተሳበ ከሻጩ ጋር ድርድር ጀመረ። በገዢና በሻጭ መካከል ብዙ ደቂቃዎችን የፈጀ የቀንስልኝ፣ አልቀንስም ክርክር ከተደረገ በኋላ ገዢው በዋጋ ተስማምቶ ግመሉን ገዝቶ ወደ ቤቱ ሄደ።

የግመል ነጋዴው ቤቱ እንደደረሰ አገልጋዩን ጠርቶ የግመሉን ኮርቻ እንዲያወርድ ይነግረዋል። አገልጋዩ የግመሉን ኮርቻ ሲፈታ ከኮርቻው ስር አነስተኛ መጠን ያላት የተቋጠረች ከረጢት ያገኛል። ከረጢቷን ሲፈታ በውድ የአልማዝ ማእድን ተሞልታለች።

አገልጋዩም "አለቃ የገዟት ግመል በነጻ ይዛ ያመጣችውን በረከት ይመልከቱ!" ሲል በደስታ ተሞልቶ ጮኸ። ነጋዴውም  በአገልጋዩ መዳፍ ላይ በጸሐይ ብርሀን የሚንቦጎቦጉ የአልማዝ እንክብሎች ሲመለከት እጅግ ተደነቀ።

ይሁንና "ግመሏን እንጂ አልማዞቹን አልገዛኋቸውም። አሁኑኑ ለባለቤቱ መመለስ አለብኝ" አለ - ነጋዴው።

አገልጋዩም "ምን የማይረባ አለቃ ነው ያለኝ?!" ሲል በሆዱ ካወራ በኋላ "ማንም ሰው የአልማዞቹን ትክክለኛ ባለቤት ሊያውቅ አይችልም! ሲል ተናገረ።

ይሁንና ነጋዴው ምክሩን ችላ ብሎ ጊዜ ሳይወስድ ባለቤቱም ፍለጋ ወደ ገበያው ተመለሰ። ብዙም ሳይለፋ የተቀሩ ግመሎችን ለመሸጥ ገዢ ሲጠብቅ የነበረውን የግመል ሻጭ አግኝቶ ትንሿን ከረጢት መለሰለት።

የግመል ሻጩም እጅግ ተደስቶ " እጅግ የከበሩ ማእድናቴን በግላሱ ስር መደበቄን ዘንግቼ ነበር። አሁን ሽልማት እንዲሆንህ በከረጢቱ ውስጥ ካሉት አልማዞች ውስጥ ለዐይንህ ደስ ያሰኘህን ውሰድ!' አለ።

"ለከፈልኩት ገንዘብ ጥሩ ግመል ሽጠህልኛል። ተጨማሪ ሽልማትም ስጦታም አልቀበልም።" አለ - ነጋዴው። ነጋዴው ስጦታውን አልቀበልም ቢልም ግመል ሻጩ እንዲቀበለው ይወተውተው ጀመር።

በመጨረሻም ነጋዴው በፈገግታ ተሞልቶ "ከረጢቱን ልመልስልህ ስወስን ሁለት እጅግ የከበሩ አልማዞችን እራሴ ዘንድ አስቀርቻለሁ! ከእነርሱ የሚልቅ ሽልማት የለም!" አለው።

የግመል ሻጩ የነጋዴው የእምነት ቃል ሲሰማ እጅግ ተበሳጭቶ በከረጢቱ ውስጥ ያሉትን ውድ አልማዞች የጨርቅ እራፊ ላይ ደፍቶ ይቆጥራቸው ጀመረ። ይሁንና ቆጠራውን እንደጨረሰ በእፎይታ ተሞልቶ "በከረጢቱ ውስጥ ከነበሩት አልማዞቼ መካከል አንድም አልጎደለም። የትኞቹን ውድ አልማዞች ነው ለራሴ አስቀርቻለሁ ያልከኝ?"

ነጋዴውም በኩራት ተሞልቶ "እኔ ዘንድ ያስቀረኋቸው ውድ አልማዞች ታማኝነቴና ለእራሴ ያለኝ ክብር ናቸው!" ሲል መለሰለት።

ሻጩ የሰማውን ነገር ባለማመን ዐይኖቹን አፍጥጦ ነጋዴውን ከመመልከት ውጪ መልስ ሊሰጠው አልቻለም።

                   **
ሁላችንም ወደ እራሳችን መመልከትና እነዚያ ውድ አልማዞች እንዳሉን እንፈትሽ። ሁለቱ ውድ አልማዞች ያሉት ማኛውም ሰው የዓለማችን ባለጸጋው ሰው ነው።
3.5K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 20:47:24
ሰሞኑን 50 ሹፌሮች እና መንገደኞች ታግተው ከ50 ሚልዮን ብር በላይ ሲጠየቅባቸው እነርሱን ለማስፈታት የከተማው ህዝብ መንገድ ዳር አንጥፎ ሲለምን  እነዚህ ሚድያዎች አንድ ነገር እንኳን ትንፍሽ አላሉም ነበር፣ አሁን ግን...

ሳትታገት ታገትኩ ብላ ብር ስለጠየቀች ሴት እንደ ትልቅ ዜና አድርገው አራግበውታል።አሁን ላይ እየተሰራው ካለው ግፍ አንፃር ይሄ እንደዜና  መቅረብ አልነበረበትም ። ነገር ግን መንግስት  በየጊዜው ታግተው የሚሞቱ ሰዎችን እውነት እንዲዳፈን ስለሚፈልግ ይሄን ዜና በሰፊው አራግቦታል።

በኦሮሚያ ብዙ አካባቢ ማገት እንደ ስራ ከተቆጠረ ሰንብቷል ዜጎች የመኖር ዋስተናቸውን አጥተዋል። ገንዘብ መክፈል ያልቻሉ ዜጎች ህይወታቸውን እያጡ ነው።ገንዘብም ከፍለው ህይወታቸውን ያጡም አሉ።ስርዓት አልበኝነት ነግሷል ዜጎች ሰርተው ሀብት የማፍራት መብታቸው ተነፍጓል።ሌላ ሀገር ቢሆን ትልቅ ሽፋን ይሰጠው ነበር። የኛ ሀገር ሚዲያዎች ግን በህዝብ ግብር እየሰሩ የህዝብ ድምፅ ከመሆን ይልቅ ለመጣው መንግስት የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ መሆናቸውን ቀጥለዋል።
5.0K viewsedited  17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 20:37:44 ለቡሄ ያበደ ሆ ሲል ይኖራል!!

ከዕለታት የሆነው ቀን፣ አንድ ስኮትላንዳዊ እና እንግሊዛዊ ዱር ውሥጥ ሲንሸራሸሩ ሳለ አንበሳ መጣባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ስኮትላንዳዊው ያጠለቀውን ትልቅ ቦቲ ጫማ አውልቆ ሸራ ሲቀይር እንግሊዛዊው በመገረም "አሁን ጫማ መቀየር ምን ያደርጋል? አንበሳውን ሮጠህ ልታመልጠው ነው? ይለዋል፡፡

"አንበሳውንማ እንደማልቀድመው የታወቀ ነው፤ ሸራውን ግን የምቀይረው አንተን ለመቅደም ነው" አለው....

አንተን እስኪበላህ እኔ ጊዜ አገኛለሁ አይነት...

ይህችን ጨዋታ ሃገሪቱ ላይ የምትጫወቱ፣ ነገር አቀጣጥላችሁ ሸራ ጫማችሁን አጥልቃችሁ ለመሮጥ የተዘጋጃችሁ ሰዎች ሆይ... አንበሳው እኛን እስኪበላ ጊዜ ታገኙ ይሆናል፤ ነገር ግን... አንደኛ አንበሳ ብቻውን አይመጣም፣ሁለተኛ ቀጣዩ ታዳኝ እናንተ መሆናችሁን በልባችሁ ፃፏት...ለዚህ እኮ ነው የወሎዋ አልቃሽ

አሁን ምን ያደርጋል የሴት ወየው ባይ
ወሎ የመጣው ሞት ሸዋ የለም ወይ?
ያለችው...
አገር አለን ለማለት እየከበደን ነው፤ ነፃነቱ እና ልቅነቱማ ተደበላልቆብናል፡፡

፨፨፨

አንዳንድ ሰው ግን..."መብራት ጠፋብን" እያለ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ቆይቶ፣ ለእሱ ሲበራ ሌላው ሰፈር ግን ሲጠፋ ፍትሃዊ የሚመስለው ለምንድነው?

ሌሊሳ ግርማ እንዳለው የሰው እግር ቆርጦ ከራስ እኩል እንደማድረግ ያለ ‹ፍትህ›

አንዳንድ ተምሬያለሁ የሚል ሰውስ የተማረ ሳይሆን በዩኒቨርሲቲ የፊት በር ገብቶ በኋላ በር የወጣ የሚመስለውስ?

ሃገሪቱ ላይ ያለው ህዝብ ይህን ይመስላል፡፡ እንዲህ ያለህዝብ ያላትን ሃገር ደግሞ ጤነኛ ትሆናለች ብሎ ማሰብ ራሱ ህመም ነው... ዝም ብሎ እጅና እግሯን ጥፍር አድርጎ ሁለት ሰባት ማስጠመቅ ይሻላል፡፡

አሁን በቀደም የመብራት ኃይል ኃላፊው መብራት በተደጋጋሚ የሚያጠፉበትን ምክንያት ጋዜጠኛው ሲጠይቃቸው "አሁን እንደድሮው አይደለም፤ መብራት መጥፋቱ ባይቀርም ምክንያቱ ግን ተቀይሯል" ካሉ በኋላ... "ዘንድሮ መብራት የሚጠፋው አሁን በተያያዝነው የብልፅግና ጎዳና የደም ግፊታቸው የሚጨምር ሰዎች በንዴት ኮረንቲ መያዛቸው አይቀርም፤ እናም መንግስት የእነዚህን ሰዎች ደህንነት ለመጠበቅ ነው መብራት የሚያጠፋው"

ቀጠሉ... 'ይህ በእንዲህ እንዳለ አንዳንድ የኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ልብስ አጥበው የሚያሰጡበት ቦታ ስለሚያጥራቸው ቀን ቀን የኤሌክትሪክ ገመዶቹን እንደልብስ ማስጫ እንዲጠቀሙ መንግስት መብራት በማጥፋት ይተባበራቸዋል"

ጋዜጠኛው ችኮ ነው ጥያቄውን ቀጠለ "እሺ ራሳቸውን በኮረንቲ ማጥፋት የሚፈልጉ ዜጎችን መብት መጨቆን እንዳይሆን... መንግስት ምን ያመቻቸው ነገር አለ? ብሎ ጠየቀው

ማለዳን መናፈቅ
መምህርት ዕጸገነት ከበደ

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
5.5K views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 15:46:32 ጊዜ እንዳለኝ እያሰብኩ ነበር — እንደምኖር።

በመጻሕፍት መደርደሪያዬ እኔን መጠበቅ ያደከማቸው ያልተነበቡ መጻሕፍት ተገጥግጠዋል።

አንድ ቀን እንደማነባቸው ተስፋ ሳደርግ ምጽዓት ደረሰ —ሀገሬ። በሲዖል ውስጥ መጽሐፍ ማንበብ አይቻልም። አንደኛ ሀገሩ የእሳት ነው። በእሳት ሀገር ወረቀት ቀለም ይዞ አይቆይም። ይነዳል፥ አመድ ይሆናል። ብዙ ጩኸት አለ —ሰቆቃ። እና አይመችም። ዙሪያው ገደል ነው። ልብ ዝቅ ያደርጋል።

ቀን በቀን መጻሕፍቴን እየተሰናበትኩ ነበር። ምን ትርጉም አለው? ሳልፈልግ አእምሮዬ እንደተረበሸ ከተማ ሐሳብ ይጎሎጉላል።  በሥነ ሥርዓት ላጠነጥን እሞክራለሁ —መሥመር ላስይዝ። ግን አልችልም ይሳከርብኛል። አንጎሌ፥ ሰውነቴ ይሰንፋል። 

የምናደርገው ነገር ትርጉም መስጠት ያቆመበት በሚመስልበት ጊዜ ላይ ነን። እዚህ ሀገር ልጅ እንወልዳለን። የምናወርሰው ሀገር ግን ሲዖል ነው። ምሽቶች ባሎቻቸው ድንገት በወጡበት ይቀራሉ። ይታፈናሉ፥ ይታገታሉ። ልጆች ያልጠገቡትን፥ በውል ያለዩትን አባቶቻቸውን ባልጠበቁት ቅጽበት ይሰናበታሉ። ለሀገራቸው ውለታ የዋሉ ዋርካ ሰዎች በልጅ እግሮች ይገደላሉ። ደም ይፈሳል —በየመንገዱ፥ በየጫካው።  አድባራት አንድ ባንድ ይፈርሳሉ። ማንም ምንም ማምጣት የሚችል አይመስልም። ድንገት ኢምንትነት እንዲሰማህ ትሆናለህ።

ሞት እየጠራህ ትማራለህ? ሞት እያነፈነፈህ ታከማቻለህ? በደጅህ ሞት እያደባ ታገባለህ? ሀገር እየተቃጠለ ትሰርጋለህ? ቆንጆ ቆንጆ ልጆች የጥይት እራት እንዲሆኑ ትወልዳለህ? መሣሪያ የታጠቀ ወንበዴ ቤትህን እየሠረሠረ ታንቀላፋለህ? ዳሩ ብትነቃስ ምን ታደርጋለህ? የዓለም ምጽዓት አንተ ጋር እስከሚደርስ ብትተኛ አይከፋም፥ ብትማር፥ ብትቆጥብ፥ ብታገባ፥ ብትወልድ።

ሀገሩ የባለጌ ነው። ማን ጌታ እንደሆነ አይታወቅም። በመንገድ ስታልፍ ረግጦህ የገላመጥከው ሰው ዘመደ ብዙ ነው። የጦር መሣሪያ አለው። ባታውቀውም የጎበዝ አለቃ ነው። ትንሽ መንግሥት ነው። ሕይወትህን ከአፈር ይደባልቀዋል። ያየህ እስከማይገኝ ድረስ ድራሽህ ይጠፋል። ወዝህ ያስቀናው ሰው ዳር ሊያስይዝህ ይችላል።

ሀገርህ ከየት እስከየት እንደሆነ አታውቅም። እግርህ ከቤት ወጣ እንዳለ የጠላት ሀገር ነህ። በካርታ ባይከለልም የተበጀ ድምበር አለ። ድንገት  ትጨመደዳለህ፥ እጅ ትሰጣለህ። ብትማረክም ትገደላለህ። ከቀን ውሎህ ተርፈህ፥ በሰላም ወጥተህ ከገባህ እድለኛ ነህ።  ከሄድክበት ስትመለስ ቤትህን በገነባህበት ስፍራ ላታገኘው ትችላለህ። ማንንም መርዳት አትችልም። ግፍና መከራ ተንከባሎ በሁሉም ቤት ይደርሳል። እስከዚያው ግን ተራው ያንተ ከሆነ ያንተ ነው። ትከሻህን ማስፋት፥ መቻል፥ መቀበል ይጠበቅብሃል። እውነት አይመስልም አይደል? ትላንት በእቅፍህ የነበረ ሰው እንደወጣ ሲቀር? ደብዛው ሲጠፋ?? ግን ይህ የብቻህ እውነት ነው። ይህ የብቻህ ሕመም ነው —ጽና።


እ. . .


ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን በሌላ አውድ የጻፈው አንድ ግጥም አለ። ያለ ዐውዱ እዚህ ጋር እንድጠቀመው ይፈቀድልኝ፦

“...ተገልለህ ርቀህ
እውነት ይተዉኛል ብለህ
እንዴት ተስፋ ታደርጋለህ?! . . . .
ተስፋ አድርገህስ ምን ልትሆን ፡ ወይስ ተስፋው ምን ሊሆንህ ?
እንቅልፍ እንጂ እሚያስወስድህ።”


እሱባለው አበራ

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
5.7K viewsedited  12:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 14:24:21 [ተስፋ በመቁረጥ ተስፋ መቀጠል] እንዳለ ገጣሚው መዘክር ግርማ...!

-/ ተስፋ በተስፋ ይተካል:: በማይቀየር  እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆነ ነገር ላይ ተስፋ መቁረጥ... ሊቀየር በሚችልና በቁጥጥራችን ውስጥ በሆነ ጉዳይ ተስፋ ለመቀጠል/ለማድረግ ያግዛል:: [ አዲስ ተስፋ ለመቀጠል በአሮጌው ተስፋ መቁረጥ ያስፈልጋል::]... ትውልድ ያለ ዕዳው እየተቀጣ ነው:: አባቶቹ ባለራዕይና ንቁ አልነበሩም:: ለሃያላን ስሁት ህልም የተገበረ የመስዋእት በግ ሆኑዋል:: ይህን ለመቀየር ረፍድዋልና ተስፋ መቁረጥ አለበት... ይህን የሚነግሩት ደፋር ብእርና አንደበት ያላቸው ቀንዲሎችም ያስፈልጉታል:: አዎ! ተስፋ መቁረጥ ከባድ ነው: ዙሪያን ጨለማ: መንገድን ግራ ያስመስላል ያኔ ግን የራስ ህልም ይወለዳል: አዲስ ተስፋ ይቀጠላል:: መጀመሪያ ተስፋ እንቁረጥ! አባቶቻችን አያቶቻችንን አይመስሉም:: ቅዠት እንጂ ህልም አልነበራቸውም::


[ናትናኤል ዳኛው]
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
5.5K views11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-14 07:28:26 ቅደም ተከተልን የማወቅ ጥበብ

“የሚያጣድፍ ነገር ሁሉ አስፈላጊ ነገር አይደለም” - Stephen Covey

አንድ ቀን አንድ የማኔጅመንት ሳይንስ ሊቅ ለተማሪዎቹ ንግግር በማድረግ ላይ ነበር፡፡ ይህ ሰው ለእነዚህ በጣም ለተነሳሱና ብሩህ አእምሮ ላላቸው ተማሪዎች በመናገር ላይ እያለ አንድን ነገር አደረገ፡፡ አንድ ባሊ አመጣና ጠረጴዛው ላይ ካስቀመጠ በኋላ ድንጋዮችን በማምጣት ባሊውን አፉ ድረስ ጢም አድርጎ በድንጋይ ሞላው፡፡ ይህንን ካደረገ በኋላ፣ “ይህ ባሊ ሙሉ ነው የሚል እጁን ያውጣ” አለ፡፡

በክፍሉ ያሉ ተማሪዎች በሙሉ እጃቸውን አወጡ፡፡ “እርግጠኛ ናችሁ?” አላቸው፡፡ “አዎን” በማለት እርግጠኝነታቸውን አረጋገጡለት፡፡ ከዚያም ከጠረጴዛው ስር አስቀምጦት ወደነበረው ሌላ ባሊ አጁን ዘርግቶ አነሳውና በውስጡ ያለውን ጠጠር ወደዚያ ድንጋይ ሞልቶበት ወደነበረው ባሊ አፈሰሰው፡፡ ጠጠሮቹ ሹልክልክ እያሉ ባገኙት ቀዳዳ ሁሉ ገቡ፡፡

“አሁንስ ባሊው ሙሉ ነው የምትሉ ስንት ናችሁ?” አለ መልሶ፡፡ አሁን አሰልጣኙ ምን ሊል እንደፈለገ በመጠኑ እየገባቸው ስለመጣ በማንገራገር የተደባለቀ ምላሽ ሰጡት፡፡ አንዳንዶቹ፣ “አሁን ሙሉ ነው” ሲሉ፤ ሌሎቹ ደግሞ፣ “አሁንም አልሞላም” አሉ፡፡ አሁንም በመቀጠል እጁን ወደ ጠረጴዛው ስር ሰደድ በማድረግ ሌላ ባሊ አነሳ፡፡
ይህኛው ባሊ በአሸዋ የተሞላ ነው፡፡ ወዲያውኑ አሸዋውን ወደዚያ ድንጋይና ጠጠር ሞልቶበት ወደነበረው ባሊ አፈሰሰው፡፡ አሸዋዎቹ ሹልክልክ እያሉ ባገኙት ቀዳዳ ሁሉ ገቡ፡፡ ለሶስተኛ ጊዜ፣ “አሁንስ ባሊው ሙሉ ነው የምትሉ ስንት ናችሁ?” አሁን ተማሪዎቹ በሙሉ በአንድ ቃል፣ “ባሊው አሁንም አልሞላም” ብለው መለሱለት፣ አካሄዱ ገብቷቸው፡፡ አሰልጣኙ እንደገና ሌላ ውኃ የሞላበት ባሊ ከጠረጴዛው ስር በማንሳት ድንጋይ፣ ጠጠርና አሸዋ ሞልቶበት ወደነበረው ባሊ አፈሰሰውና በባሊው ውስጥ ሌላ ምንም ነገር መጨመር እስከማይቻል ድረስ ሞላው፡፡

የመጨረሻው ትምህርታዊ ጥያቄ እንዲህ የሚል ነበር፡፡ “ከዚህ ምሳሌ የምናገኘው ዋና ቁምነገር ምንድን ነው?” አላቸው፡፡ አንዱ ሰልጣኝ አጁን አውጥቶ፣ “ምንም እንኳ ጊዜህ በብዙ ነገር ቢጨናነቅ፣ አሁንም ሌላ ነገርን አጨናንቀህ ማድረግ እንደምትች ነው” አለው፡፡

አሰልጣኙም፣ “ተሳስተሃል! የዚህ ምሳሌ ዋነኛ ትምህርት በመጀመሪያ ትልልቆቹን ድንጋዮች ባሊው ውስጥ ባትጨምር ኖሮ ትንንሾቹን ጠጠሮች፣ አሸዋውንና ውሃውን መጨመር አትችልም ነበር፡፡ ትልልቆቹ ድንጋዮች የሚወክሉት በሕይወትህ ያሉትን ዋና ዋና የሕይወት አላማዎችና ግቦች ነው፡፡

ቤተሰብህ፣ ጤንነትህ፣ የትምህርትህ አቅጣጫ፣ ዋነኛ ሕልሞችህና የመሳሰሉት … ዋና ዋና ከሚባሉት “ድንጋዮች” መካከል ይገኛሉ፡፡ በመጀመሪያ በእነዚህ ነገር ካልተደላደልክና የሕይወትህን አቅጣጫ ካልሞላኸው፣ በጥቃቅን ነገሮች ተጨናንቀህ ሕይወትህን ታባክናለህ፡፡

አንዳንድ ሰዎች ጊዜን በአግባቡ የመጠቀምን ጥበብ ማዳበር በራሱ እጅግ አድካሚ ስራ ነው  ብለው  ያስባሉ፡፡ ነገር ግን ሁኔታው የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ ዛሬ የሕይወቴን ዋና ዓላማ በመለየትና ቅድሚያን ለእርሱ በመስጠት መልክ የያዘ ሕይወት ለመኖር ማቀድ ካልቻልኩ ነገ በዚህና በዚያ የባከነውን ጊዜዬን መለስ ብዬ ከማየትና ከመቆጨት ውጪ ምንም ነገር ለማድረግ ያስቸግረኛል፡፡

“የጊዜ አጠቃቀም ጥበብ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተቀነጨበ፡፡

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
12.6K views04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 09:10:26 በዋናው ነገር ላይ ማተኮር!
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)

አንድን እጅግ በጥበብ የላቀን ሰው አገኘሁትና ባለችኝ የጋዜጠኝነት ሙያ ተጠቅሜ መጠየቅ የምችለውን ያህል ለመጠየቅ ሞከርኩ፡፡

ጠቢቡ - “ና ጠጋ በል … ጥያቄ ልትጠይቀኝ እንደፈለግህ ታስታውቃለህ” አለኝ፣ የልቤን ፍላጎት ገምቶ፡፡

እኔ - “ጊዜ ካለህ” አልኩት፡፡

ጠቢቡ (ልብን በሚሰርቅ ፈገግታ) - “ለማወቅ ለሚፈልጉ ሰዎች ሁሉ ጊዜ አለኝ” ብሎ መለሰልኝ፡፡

ይህ ጥበበኛ እንዴት ለሰው ሁሉ ጊዜ ሊኖረው ቻለ? እያልኩ ሳወጣና ሳወርድ በፈገግታና በትእግስት ይጠብቀኝ ነበር፡፡

እኔ፡- “ስለ ሰው ፍጥረት ከሚያስገርሙህ ነገሮች መካከል ጥቂቱን ንገረኝ” አልኩት፡፡

ጠቢቡ -

•  “ልጆች ሳሉ መሰልቸታቸውና ትልቅ ለመሆን መሮጣቸው … ካደጉ በኋላ ደግሞ ልጅ መስሎ ለመታየት መሯሯጣቸው ያስገርመኛል …

•  ገንዘብ ለማካበት ጤንነታቸውን ማጣታቸው … ጤናቸውን ለመመለስ ደግሞ እንደገና ያንኑ ገንዘብ ማፍሰሳቸው ያስደንቀኛል …

•  ስለ ነገ በመጨነቅ ዛሬን ለመኖር አለመቻላቸውና ከዛሬም ሆነ ከነገ ሳይሆኑ መንከራተታቸው ያስገርመኛል …

•  ልክ እንደማይሞት ሰው መኖራቸውና ልክ እንዳልኖረ ሰው ተጽእኖ ቢስ ሆነው መሞታቸው ያስገርመኛል፡፡

ይህን ጠቢብ ዝም ብለው ሌሎች ሃሳቦች እንደሚጨምር እየተሰማኝ በማቋረጥ፣ “ሌላ ጥያቄ ልጠይቅህ?” አልኩት፡፡

ጠቢቡ፡-
ደስ በሚያሰኝ ፈገግታ ፈቃደኝነቱን ገለጠልኝ፡፡

እኔ፡- “የሰው ልጅ ሁሉ አባት ብትሆን ለሰው ልጆች እንዲያደርጉ ከምትመክራቸው ነገሮች መካከል ጥቂቶቹን ንገረኝ” አልኩት፡፡ 

ጠቢቡ (ረዥም ጺሙን ዳበስ ዳበስ በማድረግ ካሰበ በኋላ)፡-

•  ማንም ሰው እንዲወዳቸው ማስገደድ እንደማይችሉ፣ ነገር ግን ማድረግ የሚችሉት የሚወደድ ማንነትን ማሳደግ ብቻ እንደሆነ እንዲያወቁ እመክራቸው ነበር፡፡

•  መልካም ማንነትንና የተመሰከረለት ማህበራዊ ሕይወት ለመገንባት አመታት እንደሚፈጅ፣ ለማፍረስ ግን አንድ ደቂቃ እንደሚፈጅ እንዲያውቁ አስተምራቸው ነበር፡፡

•  የሕይወታችቸውን አቅጣጫ የሚወስነው ያላቸው ንብረትና ሃብት ሳይሆን በሕይወታቸው ያስጠጓቸው የወዳጆች አይነት እንደሆነ እንዲገነዘቡ አሳስባቸው ነበር፡፡

•  ታላላቅ ሕልሞችን ለማለምና ከግባቸው ለማድረስ የሚያስፈልገው ታላቅ ሰው መሆን ሳይሆን ከግብ ለመድረስ የቆረጠ ማንነት እንደሆነ እንዲያውቁ የተቻለኝን አደርግ ነበር፡፡

•  ሃብታም ሰው ብዙ ገንዘብና ቁሳቁስ ያለው ሰው ሳይሆን የሚያስፈልገውን ነገር ያወቀ ሰው እንደሆነ እንዲያውቁልኝ እጥር ነበር፡፡

•  ራሳቸውን ከሌላው ጋር ማነጻጸርና ማወዳደር እንደማይገባቸውና ከእነርሱ የሚያንስ ሰው እንዳለ ሁሉ የሚበልጥም ሰው የመኖሩን እውነታ እንዲቀበሉት አስረዳቸው ነበር፡፡

•  አመለካከታቸውን መቆጣጠር እንዳለባቸው አለዚያ አመለካከታቸው እነሱን እንደሚቆጣጠራቸው እንዲማሩ እሞክር ነበር፡፡

•  እጅግ በጣም የሚወዷቸውና የሚያከብሯቸው ነገር ግን ያንን በቅጡ ለመግለጽ የማይሆንላቸው ብዙ ወዳጆች እንዳሏቸው አስረዳቸው ነበር፡፡ 

•  እውነተኛ ጓደኛ ማግኘት እጅግ ከባድ እንደሆነ፣ ያንን ያገኘ ግን የሕይወቱን አብዛኛውን ችግሩን እንዳቃለለ እንዲያውቁ እመክራቸው ነበር፡፡

•  የቅርብ ወዳጆቻቸውን ለማቁሰል ሰከንድ እንደሚበቃ ለመፈወስ ግን አመታት እንደሚፈጅ እንዲገባቸው እጣጣር ነበር፡፡

•  ሰዎችን ለመቆጣጠር በመሞከር እንደሚያጧቸው፣ ምርጫቸውን በማክበር ነጻነታቸውን በመስጠት ግን ለዘለቄታው ወዳጆች እንደሚያደርጓቸው እንዲገነዘቡ ለማድረግ እሞክር ነበር፡፡

•  የውስጥ ሰላም ለማግኘት ከሰዎች ይቅርታን ማግኘት ብቻ ሳይሆን ራሳቸውንም ይቅር ማለት እንደሚገባቸው እንዲያስታውሱ አሳስባቸው ነበር፡፡

•  ከመናገር በሚቆጠቡበት ነገር ላይ ጌታ፣ በልቅነት ለሚናገሩት ንግግር ደግሞ ባሪያ ሆነው እንደሚኖሩ አሳውቃቸው ነበር፡፡

•  እውነተኛ ደስታ የውሳኔ ጉዳይ እንደሆነ፣ በማንነታቸውና ባላቸው ነገር ደስተኛ መሆን፣ አለዚያ በቅንአትና በፉክክር ወጥመድ ውስጥ እንደሚገቡ አስገነዝባቸው ነበር፡፡

•  በአጭሩ በዋናው የሕይወት ነገር ላይ ያተኮረ ዝንባሌ ቢኖራቸው እመክራቸዋለሁ፡፡

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
4.2K views06:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 12:06:24 ሶፋ ወይስ አልጋ?

አስፈላጊው ነገር ላይ የማተኮር ምስጢር
!

“ወሳኙና ትኩረታችንን ልንጥልበት የሚገባው ነገር ሰው የሚያይልንና የሚያደንቅልን ነገር ላይ ሳይሆን ለሕልውናችንና ለእድገታችን አስፈላጊ የሆነው ጉዳይ ላይ ሊሆን ይገባዋል”

የትኩረት አስፈላጊነት የገባቸው ሰዎች የሰዎችን አድናቆት ከማግኘት የዘለለ የሕይወት ዘይቤ ያዳበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ሰዎች አይተውላቸው “ደስ ይላል” ብለው የሚያደንቁላቸውን ነገራቸውን የማስዋብን አስፈላጊነት ባይክዱም ከዚያ የበለጠ ትኩረት የሚገባው ነገር ግን ለእድገታቸውና ለሕልውናቸው ወሳኝ የሆነው ነገር እንደሆነ ጠንቅቀው ያውቃሉ፤ ትኩረታቸውም በዚያ ላይ ነው፡፡  

አንድ ሰው በሚኖርበት ማሕበረሰብ አካባቢ አንድን ጥናት ማድረግ ፈለገ፡፡ ከጥናቱ ሊያገኝ የፈለገው እውነታ ይህንን ይመስላል፡፡  በአንድ በኩል ትኩረታቸው ከላይ ለሰዎች የሚታየውን ብቻ ቀባ ቀባ ማድረግ የሆነና ለታይታ ብቻ የሚኖሩ ሰዎችን የሕይወት ሁኔታ ማወቅ ፈለገ፡፡ በሌላ ጎኑ ደግሞ ለታይታ ብቻ ሳይሆን በትክክለኛውና በሕይወት ላይ ለውጥ በሚያመጣው ነገር ላይ የሚያተኩሩ ሰዎችን ሁኔታ መገንዘብ ተመኘ፡፡ ይህንን ሁኔታ በቀላሉ ለማወቅ የሚችልበትን ዘይቤ ሲፈልግ አንድ ነገር ብልጭ አለለት፡፡

በየሰፈሩ እየተዘዋወረ ፈቃድን ባገኘበት ቤት ሁሉ እየገባ አንድን ጥያቄ መጠየቅ ጀመረ፡፡ ጥያቄው አጭርና ግልጽ ነበር፡- “በቤትዎት ካለው ሶፋ እና አልጋ በዋጋ የትኛው ይበልጣል? እነዚህንስ እቃዎች ሲገዙ ብዙ ትኩረት የሰጡበት የትኛውን ነው? ብዙ ዋጋ ላወጡበት እቃስ ያንን ያህል ዋጋ እንዲያወጡ ያነሳሳዎት ምንድን ነው?” የሚል ነበር፡፡ እነዚህን ሶስት ጥያቄዎች ከጠየቀ በኋላ የሰዎቹን የአኗኗር ሁኔታ በቀስታ ያጤን ነበር፡፡ በመቶ የሚቆጠሩ ቤቶችን በመጎብኘት ይህንን መጠይቅ ለማቅረብና መረጃ ለመሰብሰብ ወደ አንድ አመት ፈጅቶበታል፡፡ በመጨረሻ ያገኘው መልስ ሲጨመቅ አስገራሚ ስእል አመላከተው፡፡

በዚህ ጥናታዊ መጠይቅ ላይ ከተሳተፉት ሰዎች አብዛኛዎቹ ለገዙት አልጋ ካወጡት ዋጋ ይልቅ በብዙ እጥፍ የከፈሉት ለሶፋቸው ነበር፡፡ ከዚህ በላይ ግዢውን ሲፈጽሙ ብዙ አማራጭ ለማግኘት ጊዜን የወሰዱትና ብዙ ሰው ያማከሩበት እቃ ሶፎውነበር፡፡ አልጋ ለመግዛት ካወጡት ገንዘብና ለምርጫ ካሳለፉት ጊዜ ይልቅ በሶፋ ላይ የበለጠ ገንዘብና ጊዜ የማውጣታቸውን ምክንያት ሲጠየቁ የሰጡት መልስ ሲጨመቅ፣ “ሰዎች ሲገቡ የሚያዩት ሶፋውን ስለሆነ ነው፣ አልጋውንማ ማን ያየዋል?” የሚል ነበር፡፡

ግኝቱ ይህ ነው፡- አንድ ሰው በቀን ውስጥ በአማካኝ ሰባት ወይም ስምንት ሰዓታትን በአልጋው ላይ ያሳልፋል፡፡ በቀን በሶፋው ላይ ተቀምጦ የሚያሳልፈው ጊዜ ግን በአማካኝ ከሶስትና ከአራት ሰዓት በላይ አይሆንም፡፡ ስምንት ሰዓታት ሰውነቱን ጥሎበት የሚያሳልፈው ይህ አልጋ የተሰኘው ነገር በአካላዊ ጤንነቱ ላይ ይህ ነው የማይባል ስፍራ አለው፡፡ በተጨማሪም ከማይመች አልጋ የሚመጣ የእንቅልፍ ማጣት ችግር ለቀን ተግባር ስኬታማነት ወሳኝ መሆኑም እሙን ነው፡፡

አስፈላጊ ከሆኑት  በሕልውናችንና በስኬታማነታችን ላይ ዘላቂ ተጽእኖ ከሚያመጡት የሕይወታችን ጉዳዮች ላይ ትኩረታችንን ማንሳት ብዙ አሉታዊ ተጽእኖዎች አሉት፡፡ እንዲህ አይነቱ አካሄድ ከታይታ ወደማያልፉ ነገሮች እንድንዞርና ብዙ ውድ ነገሮቻችንን እንድናባክን አሳልፎ ይሰጠናል፡፡ ለምሳሌ ጊዜአችንን፣ ገንዘባችንንና ሃሳባችን በተለያዩ ጊዜአዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የመበታተን የሕይወት ዘይቤ ውስጥ እንገባለን፡፡ ትኩረቱን ከጊዜአዊውና ለታይታ ከሆነው ነገር ላይ በማንሳት ወደ አስፈላጊውና ወደ ዘላቂው ነገር ያዞረ ሰው ለጊዜው ሰዎች አይተው የሚያደንቁለት ነገር ባይኖረውም እንኳ ለነገ እንደሚሰራ ያውቀዋል፡፡

የሚታየውንና ጥቅሙ ውስን የሆነውን የኑሮአችንን ሁኔታ ከማይታየውና ጥቅሙ እጅግ የላቀ እንዲሁም ደግሞ ዘላቂ ከሆነው ሁኔታ ለመለየት ልናስታውሳቸው የምንችላቸው እውነታዎች አሉን፡፡ ምናልባት ለረጅም አመታት ከለመድነው የኑሮ ዘይቤ ለመላቀቅ ከባድ ቢሆንም እንኳ የማይቻል አይደለምና ዛሬውኑ ጉዞውን መጀመር እንችላለን፡፡

1.  ከስውር የዝቅተኝነት ስሜት ተላቀቅ:- ለታይታ ለመኖር የመጣጣር አንዱ ምንጭ የዝቅተኝነት ስሜት ነው፡፡ ከሌሎች በታች የሆንን ሲመስለንና በዚህ ስሜት በስውር ስንጠቃ አውቀነውም ሆነ ሳናውቀው ራሳችንን ከሌላው ለማስተካከል ወይም የበለጥን እንደሆንን ለማሳየት ስንጣጣር እንታያለን፡፡

2.  የትርጉም ማስተካከያ አድርግ:- ትክክለኛ ኑሮ ማለት እኛ ሲመቸን እንጂ በእኛ ሁኔታ ሌላው ሲገረም ማለት አይደለም፡፡ ዘላቂ ስኬት ማለት እኛ ተመችቶን ለሌላው ስንተርፍ እንጂ ኑሮአችን ወድቆ በውጫዊው “ውበታችን” ሌላው ሲገረም ማለት አይደለም፡፡

3.  የእቅድ ሰው ሁን:- ከሰው ጋር መወዳደርን አቁምና ለራስህና ለቤተሰብህ መሻሻል ካወጣኸው እቅድ አንጻር መሮጥ ጀምር፡፡ ትክክለኛ ስኬት ማለት የት መድረስ እንደሚፈልጉ ማወቅና በዚያ አቅጣጫ በመገስገስ፣ በሂደቱም መርካት ማለት ነው፡፡

ዶ/ር እዮብ ማሞ
8.6K views09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 21:33:58 ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው...(1ኛ ዮሐ.3፡15)

“ብሔርተኛ የሆነ አምባገነናዊ አገዛዝ ለጊዜው ምክንያታዊነት በጎደለው ስሜታዊና ግልብ በሆነ አስተሳሰብ ዜጋውን ወይም “ብሔር” ብሎ ከፋፍሎ ያደራጃቸውን በመንዳት የተሳካለት ይምሰለው እንጂ፣ አገዛዙን ለማስቀጠል ሲል የሚፈጽማቸውን ግፎች በሂደት ሕዝቡ እየተገነዘበው ስለሚሄድ ምንም ዓይነት ሴራ ቢጠቀም አገዛዙ ያሰበው እቅድ ዘለቄታ ሊኖረው አይችልም፡፡

በአንድ ሀገር ውስጥ ብዙሃን ይሁን አናሳ ቁጥር ባለው “በብሔር” ማንነት
ላይ የተመሠረተ ማንኛውም አገዛዝ የሳይንሳዊ ፖለቲካዊ ስርአት ሳይሆን በአዕምሮ ቅዠት ህመም የተጠቃ፣ ፋሽስታዊ አምባገነን፣ ኢ-ሰብአዊ፣ ስርአተ አልበኛ፣ የወሮበላና የደንቆሮ ገዢ ቡድን ነው፡፡ በአጠቃላይ “የብሔርተኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ በፖለቲካ ሳይንስ የተቃኘ ሕዝባዊ አስተዳደር ሳይሆን፣ ከአዕምሮ ቅዠት ህመም የመነጨ የድንቁርና አገዛዝ ነው::

በአሁኑ ዓለም የመልካም አስተዳደር ሳይንሳዊ ፖለቲካ ማለት፣ የአንድ ሀገርን ብዙሃን ሕዝብ አዕምሮ ከፖለቲካዊ ቁጭት፣ ጥላቻና በቀል ነጻ በማድረግ በኑሮ ደረጃዉ እያሳደገ የማስቀጠል ብቃት ነው፡፡


በአንድ ሀገር መንግሥታዊ አገዛዝ ላይ ብዙሃኑ ሕዝብ አዕምሮ ውስጥ ቁጭት፣ ጥላቻና በቀል ከተፈጠረ ሀገሪቱ የብዙሃን ሕዝብ ድጋፍ የተቸረው የአገዛዝ ሥርዓት ባለመሆኑ ሀገሪቱ ያልተረጋጋችና ልማቷም ዘለቄታ የሌለዉ ስለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ይህም ቁጭት፣ ንዴትና ጥላቻ እያደገ በመሄድ በዋናነት በአፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያን የመሳሰሉትን ሀገራት ሁልጊዜ ወደ እርስ በርስ ጦርነት እየከተተ ዜጋውን ወደተሻለ ኑሮ እንዳያድግ የሚገድብ ነው፡፡

ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው...(ኛዮሐ.3፡15)፡፡ አንድ ሰው ግድያ ከመፈጸሙ በፊት የሚፈጠረው የጥላቻ አስተሳሰብ ይቀድማል፡፡ የጥላቻውም አስተሳሰብ በሂደት በግድያ ድርጊት ይፈጸማል፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ ብዙሃኑ ሕዝብ በፊት ስለሚገድለው ሰው በአዕምሮው ውስጥ  ቁጭት፣ ንዴትና ጥላቻን የሚፈጥር መንግሥት ካለ አምባገነን አገዛዝ እንጂ፣ መንግሥታዊ ስርአት አይደለም፡፡ ስርአት ማለት ማንም ሰው እንደፈለገው የማይቀያይረው፣ በሳይንሳዊ እውቀት የተደራጀ፣ ህግንና ደንብን በመከተል የታለመለትን ግብ የያዘ ተቋም  ነው፡፡

“የብሔርተኛ” አምባገነናዊ አገዛዝ ሳይንሳዊ የፖለቲካ ስርአት ሳይሆን፣ በባህሪው በቀሪው ዜጋ አዕምሮ ውስጥ ሁልጊዜ ቁጭት፣ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ ንዴትና ጥላቻን የሚፈጥር የስርአተ አልበኛና የአሸባሪነት አገዛዝ ነው፡፡ የብዙሃኑ ህዘብ አዕምሮ ለቁጨት፣ ለንዴትና ለጥላቻ የሚዳርግ አገዛዝ ይዋል ይደር እንጂ፣ አንድ ቀን በብዙሃኑ ህዝብ አመጽ በውርደት መወገዱ እንደማይቀር የአሁኑ ዓለም ታሪካዊ ሃቅ ነው፡፡ በአሁኑ ዓለም “በብሔር” ማንነት ላይ የተመሠረተ ፋሽስታዊ አገዛዝ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚዊ እንዲሁም በኃይማኖታዊ ጉዳዮች ላይ እንኳ ሳይቀር የበላይነቱን በማረጋገጥ ሰውን ከሰው የሚለይ፣ የሚያገልና አድልኦን የሚፈጽም ሳይንሳዊ ያልሆነ አገዛዝ ነው፡፡ ስለሆነም በብዙሃኑ ሕዝብ ዘንድ ምንጊዜም ቢሆን ተቀባይነት ስለሌለው ሁልጊዜ ሰላምና መረጋጋትን በማሳጣት ለአብዮት የሚዳርግ ነው፡፡

በ”ብሔር” ማንንነት አዕምሮ በተቃኘ ፋሺስታዊ አገዛዝ ውስጥ ሁሉም ባይቀበለውም ነገር ግን እጅግ አብዛኛው ዜጋ በ”ብሔር” ማንንነት አዕምሮ ቅዠት ህመም ይለከፋል፡፡ የ”ብሔርተኛ” ፋሽስታዊ አገዛዝ የስልጣኑን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሲል የሚያራምዳቸው መሠረታዊ ሴራዎች አሉት፡፡ እነዚህ ሴራዎችም በህዝብ አዕምሮ ውስጥ ቁጭት፣ ንዴትንና ጥላቻን በአገዛዙ ላይ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ በመሆኑም ይህ ቁጭት፣ ጥላቻ ይዋል ይደር እንጂ “በብሔር” ማንነት ተከፋፍሎ የነበረውን ሕዝብ ወደ መተባበበር ይገፋፋውና አገዛዙን ለማስወገድ የሞት ሽረት ትግል ውስጥ ሳይወድ በግዱ ይገባል፡፡

ሰብስቤ አለምነህ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
8.0K views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ