2023-07-05 08:33:53
በጉማ አዋርድ ላይ ግንባሯን በጥይት መመታቷንና አፏን በሽቦ መለጎሟን በሚያሳይ ሜካፕ የቀረበችውን ፍላጎት አብርሃምን ከስራ አገደ
ንሥር ብሮድካስት
ሰኔ 28/2015
ሰኔ 2/2015 ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው 9ኛው የጉማ ሽልማት ላይ የወገኗን መታፈን በሜካፕ ያሳየችው የቴሌቭዥን ፕሮግራም አዘጋጇና ታዋቂ ቲክቶከሯ ፍላጎት አብርሃም/የልጅ ማኛ/ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ከነበራት የኢትዮጵያ አይዶል የዳኝነት ስራዋ ተሰናብታለች።
ፍላጎት ከዚህ በፊት በአትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የተሰጥኦ ውድድር /ኢትዮጵያን አይዶል/ ላይ በዳኝነት ስራ ቀረፃዎችን ከውና እንዲሁም ከሚዲያው ጋር ውል ተዋውላ ነበር።
ይሁን እንጂ ተቋሙ አዲስ በገነባውና ነገ በሚያስመርቀው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ህንጻ ሰኔ 27/2015 ምሽት በጀመረው የኢትዮጵያን አይዶል ውድድር ላይ በፍላጎት ቦታ ከዚህ ቀደም በውድድሩ የዳኝነት ስራ ላይ ያልነበረው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ተተክቷል።
ሚዲያው ፍላጎትን ከዚህ ስራዋ ያገደበትን ምክንያት በግልፅ ማወቅ ባይችሉም ፣ በጉማ አዋርድ ላይ በሜካፕ ባስተላለፈችው መልዕክት ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮቻችን ነግረውናል ሲል ሮሃ ሚዲያ ዘግቧል።
ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube: https://buff.ly/3mOQNyX
FaceBook Page 1 : https://buff.ly/3GZyFJA
FaceBook Page 2: https://buff.ly/3Ad8zPE
Telegram: https://buff.ly/3Tcx06A
Website: https://buff.ly/3DETCqV
Twitter: https://twitter.com/NISIRInternati1
Instagram: https://www.instagram.com/nisirbroadcast/
ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን።
1.4K views05:33