በጉማ አዋርድ ላይ ግንባሯን በጥይት መመታቷንና አፏን በሽቦ መለጎሟን በሚያሳይ ሜካፕ የቀረበችውን ፍላጎት አብርሃምን ከስራ አገደ ንሥር ብሮድካስት ሰኔ 28/2015 ሰኔ 2/2015 ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው 9ኛው የጉማ ሽልማት ላይ የወገኗን መታፈን በሜካፕ ያሳየችው የቴሌቭዥን ፕሮግራም አዘጋጇና ታዋቂ ቲክቶከሯ ፍላጎት አብርሃም/የልጅ ማኛ/ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ከነበራት የኢትዮጵያ አይዶል የዳኝነት ስራዋ ተሰናብታለች። ፍላጎት ከዚህ በፊት በአትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የተሰጥኦ ውድድር /ኢትዮጵያን አይዶል/ ላይ በዳኝነት ስራ ቀረፃዎችን ከውና እንዲሁም ከሚዲያው ጋር ውል ተዋውላ ነበር። ይሁን እንጂ ተቋሙ አዲስ በገነባውና ነገ በሚያስመርቀው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ህንጻ ሰኔ 27/2015 ምሽት በጀመረው የኢትዮጵያን አይዶል ውድድር ላይ በፍላጎት ቦታ ከዚህ ቀደም በውድድሩ የዳኝነት ስራ ላይ ያልነበረው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ተተክቷል። ሚዲያው ፍላጎትን ከዚህ ስራዋ ያገደበትን ምክንያት በግልፅ ማወቅ ባይችሉም ፣ በጉማ አዋርድ ላይ በሜካፕ ባስተላለፈችው መልዕክት ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮቻችን ነግረውናል ሲል ሮሃ ሚዲያ ዘግቧል። ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት Youtube: https://buff.ly/3mOQNyX FaceBook Page 1 : https://buff.ly/3GZyFJA FaceBook Page 2: https://buff.ly/3Ad8zPE Telegram: https://buff.ly/3Tcx06A Website: https://buff.ly/3DETCqV Twitter: https://twitter.com/NISIRInternati1 Instagram: https://www.instagram.com/nisirbroadcast/ ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን። 1.4K views05:33