Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Students Books(Grade 9-12 )

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_students_only — Ethio Students Books(Grade 9-12 ) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_students_only — Ethio Students Books(Grade 9-12 )
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_students_only
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 282
የሰርጥ መግለጫ

በቻናላችን የሚገኙ ጠቃሚ ነገሮች
✅ entrance exam
✅extreme book & referance book
✅Textbook ( 9-12 )
✅Teachers Guide (9-12)
✅worksheet ( 9-12)
✅students info እና ለሎችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇
@Ethio_Students_only
For comment @EthioStudentsOnly_bot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-10 10:28:11
በትግራይ ክልል ከ1 ሺሕ 200 በላይ ትምህርት ቤቶች መደበኛ ትምህርት መጀመራቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ከሚያዝያ 23 ጀምሮ በ1 ሺሕ 218 ትምህርት ቤቶች መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት መጀመራቸው ተገለጸ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ኪሮስ ጉዑሽ (ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ ከሚገኙ 1 ሺሕ 466 ትምህርት ቤቶች መካከል 1 ሺሕ 218 ትምህርት ቤቶች ላይ ከሚያዚያ 23 ጀምሮ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ተጀምሯል፡፡

ትምህርት በመጀመሩ በተማሪዎችና አስተማሪዎች መካከል ናፍቆትና የትምህርት ጥማት መስተዋሉን ገልጸው ይህም በትምህርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረ ጠቁመዋል፡፡
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.4K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 10:20:09
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በ2015 የመውጫ ፈተና ለሚፈተኑ ተመራቂ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ/online የታገዘ ሞዴል የሙከራ ፈተና መሰጠቱን የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ሰለሞን ጉንታ ገልጸዋል።

የሙከራ ፈተናው ተማሪዎችን ለአገረ-አቀፍ የመውጫ ፈተና በሚያግዛቸው መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን ያመላከቱት ዲኑ፤ ፈተናው ከተመረጡ ትምህርት ዓይነቶች (Core Competence) መውጣቱ ተማሪዎችን ለፈተናው በተገቢው ያዘጋጃቸዋል ብለዋል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ በመታገዝ የተሰጠውን ሞዴል ሙከራ ፈተና በኮሌጁ ዘጠኝ የትምህርት ክፍሎች በቅድመ ምረቃ መደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር በ2015 ዓ.ም የሚመራቂ 182 ተማሪዎች መፈተናቸውን ዶ/ር ሰለሞን ተናግረዋል።

በቀጣይ ለኮሌጁ የተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብር ቅድመ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች በበይነ መረብ በመታገዝ ሞዴል የሙከራ ምዘና የሚሰጥ መሆኑን በመጠቆም።

የኮሌጁን ተማሪዎች ለመውጫ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወኑን የገለጹት የኮሌጁ ዲን፤ በቀጣይ ጊዜ ተፈታኝ ተማሪዎችን የበለጠ ለማዘጋጀት በትጋት እንሰራለን ብለዋል።

በመጪው ሀምሌ ወር በሀገር አቀፍ ደረጃ በኦንላይን የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና 310 ያህል የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ኮሌጅ ተማሪዎች ፈተናውን የሚወስዱ መሆኑን ነው ዶ/ር ሰለሞን ያሳወቁት።

በኮሌጁ ፈተናውን ከሚወስዱ አጠቃላይ ተፈታኞች መካከል 182 የመደበኛ እንዲሁም 128 የተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብር ተማሪዎች ሲሆኑ፤ በጾታ ስብጥር 256 ወንድ እንዲሁም 54ቱ ሴቶች ናቸው። #WSU
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.2K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 19:02:51
#የሐዘን_መግለጫ!

●●●●●

የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪያችን የነበረው ተማሪ አበባው ስንሻው መጸዳጃ ቤት ውስጥ ገብቶ የመጸዳጃ ቤቱን በር በመቆለፍ በራሱ ቀበቶ ራሱን አጥፍቶ በመገኘቱ ዩኒቨርሲቲያችን የተሰማዉን ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል። ተማሪው እዚህ አሳዛኝ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ ያበቁትን ጉዳዩች ተጨማሪ ማጣራት የሚያስፈልግ ቢሆንም ፈተና ከበደኝ በሚል ሲጨናነቅ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ስለሆነም ለቤተሰቦቹ ፣ ለጓደኞቹና ለዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብ በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን!

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
3.1K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 18:48:11
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ 6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ቀናት ይፋ አደረገ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የ 8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ 6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተናግረዋል::


አያይዘውም ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የተናገሩ ሲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ ከከተማና ክፍለ ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን የሞዴል ፈተናዎችን እንዲሰጡ አሳስበዋል ::


በ 2015 ዓ. ም 75,100 የ8ኛ እንዲሁም 75,078 የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.8K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 18:36:39
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አንድ ተማሪ ተገድሎ ተገኘ


ዛሬ ግንቦት 01/2015 በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ አንድ ተማሪ ተገድሎ መገኘቱን እና በዚህም ምክንያት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ስጋት መፈጠሩን የተቋሙ ተማሪዎች ነግረውናል።

በጉዳዩ ዙሪያ ለቲክቫህ መረጃ የሰጡት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ድርቧ ደበበ (ዶ/ር)፤ "ፖሊስ ጉዳዩን የያዘው መሆኑንና ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ" ገልጸዋል።

ሟቹ ተማሪ "ቅዳሜ ዕለት የታየ መሆኑን ለሦስት ቀናት ጠፍቶ መቆየቱን" ኃላፊዋ አመልክተዋል።

የተማሪውን ተገድሎ መገኘት ተከትሎ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ አለመረጋጋት መፈጠሩንና የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችም ከፀጥታ አካላት ጋር መጠነኛ ግጭት ውስጥ ገብተው እንደነበር ከተማሪዎቹ ሰምተናል።አሁን ላይ አለመረጋጋቱ በፀጥታ አስከባሪዎች ቁጥጥር ስር እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል።

ዩኒቨርሲቲው በበኩሉ የተማሪው ማንነትና የግል ማህደር በማጣራት ላይ መሆኑንና በቀጣይ መረጃ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

በዚህ ዓመት ብቻ የተቋሙ ተማሪ ተገድሎ ሲገኝ ይህ የመጀመሪያ አለመሆኑንም ተማሪዎቹ ጨምረው ጠቁመዋል
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.6K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 19:18:49
#WachemoUniversity

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ቅዳሜ ዕለት ተፈጥሮ የነበረው "መጠነኛ አለመረጋጋት" ወዲያውኑ መፈታቱን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በአንድ ተማሪ ላይ አካላዊ ጉዳት መድረሱን ተከትሎ፤ በግቢው ውስጥ ቅዳሜ ቀን 11:00 አካባቢ "መጠነኛ አለመረጋጋት" ተፈጥሮ እንደነበር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ሀብታሙ አበበ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

በተጨማሪም ሁለት ተማሪዎች ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደው ህክምና እንዲያገኙ ተደርጎ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ መደረጉን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል፡፡

የተፈጠረው መጠነኛ አለመረጋጋትም ወዲያውኑ እንደተፈታ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል፡፡

ከአለመረጋገቱ ጋር ባልተያያዘ በተቋሙ ለሁለት ቀናት ተቋርጦ የነበረው የአዲስ መስመር የውሃ አቅርቦት በዕለቱ ጠዋት (ቅዳሜ ሚያዝያ 28/2015 ዓ.ም) በድጋሜ ሥራ መጀመሩን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል፡፡

ተቋሙ በቂ የውሃ አቅርቦት (ነባር እና አዲስ) የውሃ መስመር እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ ተፈጥሮ የነበረው አለመረጋጋት ከውሃ አቅርቦት ጋር የተያያዘ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
3.1K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 19:18:49
ከ215 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መመዝገባቸውን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡
ካለፈው ዓመት ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከወትሮው በተለየ መልኩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሰጠት ተጀምሯል፡፡ በአማራ ክልል የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ ከ215 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ አድርገዋል ነው የተባለው፡፡
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ከመጋቢት 20/2015 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም ድረስ ተካሂዷል፡፡ የተፈታኞች ምዝገባ በትምሕርት ቤቶች በበይነ መረብ ብቻ እንደተካሄደ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የፈተናና ምዘና ቡድን መሪ አቶ ዝጋለ ማሩ በተለይም ለአሚኮ ገልጸዋል፡፡
በክልሉ ውስጥ 579 2ኛ ደረጃ ትምሕርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን የተማሪዎች ምዝገባ ያካሄዳሉ ተብሎ ታቅዶ ነበር ያሉት አቶ ዝጋለ 575 ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን ማድረግ ችለዋል ነው ያሉት፡፡ ሰሜን ጎንደር እና ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር የሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች በአካባቢው ከተፈጠረው ጦርነት ጋር በተያያዘ የተማሪዎች ምዝገባ ማድረግ አልቻሉም ብለዋል፡፡


መረጃው የአሚኮ ነው።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.6K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 19:18:49
ከትምህርት ተቋማት መረጃ ለማሰባሰብ የሚረዳ ድረ-ገጽን መሠረት ያደረገ ዲጂታል መተገበሪያ ተግባራዊ ተደረገ

የትምህርት ተቋማት መረጃ ለማሰባሰብ የሚረዳ ድረ-ገጽን መሠረት ያደረገ ዲጂታል መተገበሪያ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን፤ በአጠቃቀሙ ላይ በተግባር የተደገፈ ሥልጠና መሠጠቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

ስልጠናው የተሰጠው ከመምህራን ኮሌጆች ለተውጣጡና ከመረጃ ጋር ተያያዥነት ላላቸው የትምህርት ባለሙያዎች መሆኑም ተነግሯል።

በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት መረጃ አስተዳደር ሥርዓትና ኣይሲቲ ሥራ አስፈጻሚ ሰብስብ ለማ ዲጂታል መተግበሪያው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን ከተቋማቱ ጋር በበይነመረብ (በኦንላይን) የሚያገናኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም መረጃዎችን በየፈርጁ እንዲሁም በተቋም ደረጃ እና በአገር አቀፍ ደረጃ በፍጥነት ተንትኖ መረጃው ለሚፈለገው ዓላማ በግብዓትነት እንዲውል የሚያስችልና ለአጠቃቀም ቀላልና ቀልጣፋ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

ቴክኖሎጂው ከዚህ በፊት የነበረውን መረጃን በወቅቱና በጥራት ሰብስቦና ተንተኖ ለሚፈልገዉ ግብዓት እንዲውል ማቅረብ ያለመቻል ዉስንነቶችን በሚቀርፍ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

የዲጂታል መተግበሪያው ለሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም ሆነ ወደ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ መረጃ ለሚልኩ ተቋማት በየጊዜው የተላከውን መረጃ ተንትኖ የሚያስቀመጥበት በቂ የማከማቻ ቦታ ያለው መሆኑም ተገልጿል።

በመረጃዎች ላይ ማስተካከያ ካለም ማስተካከያ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነና፤ የተደረገው ማስተካከያንም በቀጥታ በአገር አቀፍ ደረጃ ተንትኖ የሚያስቀምጥ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚዉ መግለጻቸውን አዲስ ማለዳ ከሚኒስቴሩ መሥሪያ ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.5K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 10:39:07
በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የእንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ሊደረግ ነው።

በኢትዮጵያ በቂ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራን ባለመኖራቸው፣ በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ሊያስተምሩ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ተማሪዎችን ብቻ ሳይሆን መምህራንን ጭምር የሚያሠለጥኑ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ በኢትዮጵያ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተመድበው የእንግሊዝኛ ቋንቋ የሚያስተምሩበት ሁኔታ እየተመቻቸ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በተለይ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

"የእንግሊዝኛ ቋንቋ የአፍ መፍቻቸው የሆኑ ሦስት ሺህ የሚሆኑ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ በአገር ቤት ያሉ መምህራንንና ተማሪዎችን እንዲያስተምሩ በየትምህርት ቤቱ አንድ ለመመደብ አቅደናል" ሲሉ አስረድተዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ባደረገው ጥሪ መሠረት በውጭ አገር ያሉ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ልጆቻቸውን ወደ አገር ቤት ልከው ትምህርት እንዲሰጡ ለማድረግ እንዲመዘገቡ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል፡፡

ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ስምምነት በማድረግ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የእንግሊዝኛ ቋንቋን በነፃ የሚያገኝበት ማስተማሪያ ‹‹ፖርታል›› እንደተዘጋጀም ገልጸዋል። #ሪፖርተር
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
3.1K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 19:32:57 የ2024 ዲቪ ሎተሪ እድለኞች ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ ይፋ እንደሚደረጉ አሜሪካ አስታወቀች


የዲቪ 2024 ማመልከቻ የሞሉ ዜጎች መመረጣቸውን እና አለመመረጣቸውን ከፊታችን ቅዳሜ ሚያዚያ 28/2015 ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ አሜሪካ አስታውቃለች።

አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ በትዊተር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት፤ ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ዲቪ ሎተሪ አሸናፊዎች መታወቃቸው ገልጿል።

በዚህም መሰረት፤ አመልካቾች በዲቪ ሎተሪ ድረገጽ ላይ በመግባት ያመለከቱበትን ልዩ ቁጥር ወይም ኮድ በማስገባት አሸናፊ መሆናቸውንና አለመሆናቸውን ማረጋገጥ ይችላሉ ተብሏል።

ኤምባሲው አክሎም፤ የዲቪ ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው የምንደውለው በሚል የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ ያሳሰበ ሲሆን፤ የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስለመመረጣቸውና አለመረጣቸው አመልካቾች በድቪ ሎተሪ ድረገጽ ow.ly/9E7A50O7plm ላይ በመግባት፤ በራሳቸው እጃቸው ላይ ባለው ሚስጢራዊ ቁጥር ማረጋገጥ ብቸኛው መንገድ እንደሆነም አመላክቷል።

በተጨማሪም የ2023 ድቪ ሎተሪ አሸናፊዎች፤ እስከ ቀጣዩ መስከረም 2016 ድረስ ብቻ እንደሚስተናገዱ ኢምባሲው አስታውቋል።

አሜሪካ በዓለም ላይ በየዓመቱ 50 ሺሕ ሰዎችን በ”ዳይቨርሲቲ ቪዛ“ ወይም ድቪ ሎተሪ አማካኝነት ወደ አገሯ የምታስገባ ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ የአፍሪካ፣ እስያ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ ዜጎች ይገኙበታል።
እሁድ ይለቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ቤተሰቦቻችን።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
4.1K viewsE, 16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ