Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Students Books(Grade 9-12 )

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_students_only — Ethio Students Books(Grade 9-12 ) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_students_only — Ethio Students Books(Grade 9-12 )
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_students_only
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 282
የሰርጥ መግለጫ

በቻናላችን የሚገኙ ጠቃሚ ነገሮች
✅ entrance exam
✅extreme book & referance book
✅Textbook ( 9-12 )
✅Teachers Guide (9-12)
✅worksheet ( 9-12)
✅students info እና ለሎችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇
@Ethio_Students_only
For comment @EthioStudentsOnly_bot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-17 18:45:50
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማጣራት እንዲደረግባቸው በተለያዩ ተቋማት ከቀረቡለት የትምህርት ማስረጃዎች ውስጥ እስካሁን 21 ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ማግኘቱን አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ተቋማት የግለሰቦች የትምህርት ማስረጃ ተገቢነት ተጣርቶ እና ተረጋግጦ እንዲገለጽ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት በ42 የትምህርት ማስረጃዎች ላይ በሁለት ዙር ባካሄደው የህጋዊነት ማረጋገጫ ሥራ 21ዱ ሐሰተኛ ሆነው መገኘታቸውን የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አሳውቋል።

ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ስም ተጭበርብሮ በተሰራ ማሕተም፣ በአመራር የስምና የማዕረግ ቲተር እንዲሁም በሐሰተኛ ፊርማ ተመሳስሎ የተሠራ መሆኑ ተመላክቷል።

ግለሰቦቹ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በመጠቀም በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ተቀጥረው በመስራት የማይገባቸውን ጥቅም እያገኙ መሆኑም ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው የሐሰተኛ ትምህርት አጣሪ ግብረ ኃይል አቋቁሞ ሰፊ የማጣራት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
1.6K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 18:00:59
የድሬደዋ ዩንቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ከትምህርት ሚኒስቴር የተሠጡ አቅጣጫዎች በሚል ያጋራው መረጃ

1, የሬሜድያል ተማሪዎች ፈተና ሰኔ መጨረሻውዎቹ የሚሠጥ ይሆናል።

2, የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ሀምሌ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንት ውስጥ የሚሠጥ ይሆናል።

3,  በ2ተኛ ወሰነ ትምህርት ያልተመዘገቡ እና ለምርቃት ብቁ ያልሆኑ የመጨረሻ ዓመት ተማሪዎች ቀጣይ አመት ፈተናው የሚወስዱ ይሆናል።(የዓመቱ መጀመሪያ ላይ)

4, የምርቃት ፕሮግራም በተመለከተ በተቋማት የሴኔት ውሳኔ ማድረግ የሚቻል ይሆናል።

5,  የፈተናው አጠቃላይ የጥያቄ መጠን እንደ ትምህርት አይነቱ  ከ 100-150 ነው።

6, ማለፊያ ነጥብ 50% እና ከዚያ በላይ ነው።

7, ፈተናው የሚሠጠው በ online  ነው።

8,  የፈተናው ይዘት ሙሉ ምርጫ ነው።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
1.6K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 19:47:14
#REMEDIAL #UEE #EXIT

በርካታ ተማሪዎች የሪሜዲያል ማጠቃለያ ፈተና ፣ የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና እና የዩንቨርሲቲ መውጫ ፈተና የሚሰጥበትን ትክክለኛ ቀን ጠይቀውናል። atc_news ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች አካዳሚክ ካላንደር ባገኘው መረጃ መሰረት

፨የሪሜድያል ፈተና ከሰኔ 25-30/2015 ድረስ ይሰጣል።

፨የ2015 የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ከሀምሌ 05-14/2015 ድረስ ይሰጣል።

፨የ2015 ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከሀምሌ 17-27/2015 ድረስ ይሰጣል።

====================

ፈተናዎቹ በዩንቨርሲቲዎች በሚሰጡበት ጊዜ ተፈታኝ ያልሆናቹህ መደበኛ ተማሪዎች ከግቢ የምትወጡበት እና ወደ ግቢ የምትመለሱበትን ቀን ከዩንቨርሲቲዎቻቹህ updated academic calendar ላይ ተመልከቱ
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.6K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 19:10:43 በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የስራ ፈጠራ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተጀመረ፡፡


በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተዘጋጀው ይህ ስልጠና የአስር ቀናት ቆይታ ይኖረዋል፡፡ ስልጠናው በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የስራ ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡
ስልጠናው በዘርፉ የተሰማሩ ወጣቶችን በማነቃቃት በስራ ፈጠራው ዘርፍ የሚታዩ ተግዳሮቶችን ከመቅረፍ ባሻገር መሠረታዊ የእውቀት እና ክህሎት ክፍተቶችንም እንደሚሞላ ይጠበቃል፡፡
ስልጠናውን በይፋ ያስጀመሩት  ከኢንስቲትዩቱ ምርምር እና ልማት ዘርፍ የተወከሉት አቶ የኋላእሸት መገርሳ ናቸው፡፡ ስልጠናው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የስራ ፈጠራ ዙሪያ የሚታየውን የግንዛቤ ክፍተት በመሙላት ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው አቶ የኋላእሸት ጠቁመዋል፡፡
በተለይም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ስታርት አፕ (ጀማሪ ተቋማትን) የተመለከቱ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች በስፋት አለመኖራቸውን የገለጹት ተወካዩ ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጀው ይህ እድል መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ መልካም አጋጣሚ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ሰላሳ ሁለት ተሳታፊዎችን በመያዝ የተጀመረው መርሓ ግብር፤ ሰልጣኞች በዘርፉ የሚኖራቸውን የስራ ፈጠራ ሀሳቦች ወደተግባር እንዲቀይሩ የሚያስችል እድልም መመቻቸቱ  ከመድረኩ ተመላክቷል፡፡
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.2K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 19:09:07
#WolloUniversity
New #Updated Academic Calendar

ወሎ ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል፣ በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና በመውጫ ፈተና ምክንያት የ2015 ዓ.ም አካዳሚክ ካሌንደርን ማሻሻያ አድርጓል።

በተሻሻለው አዲስ ካሌንደር መሰረት

፨ከሰኔ 25-30/2015 ድረስ የሪሚዲያል ፈተና ይሰጣል።(Tentative)

፨ሰኔ 29 እና 30 የዩንቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎች ለኢንትራንስ ፈተና ሲባል ግቢው ለቀው እንዲወጡ ይደረጋል።

፨ከሀምሌ 05-14/2015 ድረስ የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ይሰጣል።(Tentative)

፨ሀምሌ 15 እና 16/2015 የግቢው ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ወደ ግቢ ይገባሉ።

፨ከሀምሌ 17-27/2015 ድረስ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ይሰጣል።

በዚህ አካዳሚክ ካሌንደር መሰረት የወሎ ዩኒቨርስቲ የተመራቂ ተማሪዎች የመመረቂያ ቀን መስከረም 19-20/2016 እንደሆነ ተገልጿል።


ዝርዝር መረጃ ለምትፈልጉ ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.3K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 18:16:16 ለፈገግታ የኔልሰን ማንዴላ የዪኒቨርስቲ ሂወት ታሪክ በElshio_acadame እና Ethio_Students_only በመተባበር
__
ኔልሰን ማንዴላ በዪኒቨርስቲ ውስጥ የህግ ትምህርት በሚማሩበት ጊዜ ነጭ ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው፡፡ ስሙም ፒተር ይባል ነበር፡፡
አንድ ቀን ማንዴላ በአንድ ምግብ ቤት
ምግባቸውን እየበሉ ሳለ ፕ/ሮ ፒተር በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ ። ዘረኛው
ፒተርም ''አቶ ማንዴላ! አሳማ ና 'ርግብ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" ሲላቸው ብልሁ
ማንዴላ "አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ እሄዳለሁ" ብለዋቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ ።
በዚህ የተናደዱት ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣ ያስባል አንድ ቀንም ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ
"ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳወች ብታገኝ በአንደኛው ቦርሳ 'ገንዘብ' በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ 'ጥበብ' ቢኖረው የትኛውን ትወስዳለህ''? ብሎ ጠየቀው ማንዴላም "ገንዘብ እወስዳለሁ"…ብሎ መለሰለት ፡፡ ፕሮፌሰሩ በድል አድራጊነት "አንተ ሞኝ እኔ አንተን ቢያረገኝ 'ጥበብ' ያለበትን ቦርሳ "ምወስደው ነበር አለው" ሲለው ማንዴላ ፈገግ እያለ " ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው "አለው ።
በዚሁሉ ነገገር የተበሳጨው ፕ/ሮ ፒተር የማንዴላን ፈተና ወረቀት ላይ "ደደብ" የሚል ፁሁፍ ይፅፋል። ሌሎች ተማሪወች የታረመላቸውን
የፈተና ወረቀት ሲያዩ ማንዴላ "ደደብ" የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አዩና ተገረመ ወደ ፕ/ሮ ፒተር ሄዶ
"ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥከ ው ውጤቴን እረስተኸዋል" ብሎት እርፍ ፡፡
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.3K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, edited  15:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 10:24:00 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይሰጣል?

በርካታ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከፈተና ቀን ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ጥያቄዎችን እየላኩልን ይገኛሉ።

ፈተናው በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ እስከአሁን የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ትክክለኛና ቁርጥ ያለ ቀን ይፋ አልተደረገም።

የፈተናው ቀን ይፋ የሚደረገው በማዕከል በኩል ከትምህርት ሚኒስቴር / ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ሲሆን ይህም ለህዝብ በይፋ በመገናኛ ብዙኃን ይነገራል።

በመሆኑም ተማሪዎች ለፈተናው ጥቂት ጊዜ የቀረው መሆኑን በመገንዘብ ዝግጅት ማድረጋችሁን እንድትቀጥሉ እንላለልን።

በሌላ በኩል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የተፈታኞች የበይነ መረብ ምዝገባ /online Registration/ አፈጻጸም ግምግማ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡

በተጨማሪም በተዘጋጀው የፈተና አስተዳደር መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን የበይነ መረብ ምዝገባው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የተደረገበትና ስኬትማ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የፈተና አስተዳደር መመሪያ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከውይይቱ የተገኙ ሀሳቦችም በሰነዱ ተካተው በድጋሚ ለውይይት እንደሚቀርብና ሲጸድቅ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግሯል።

የመውጫ ፈተና

ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በተመሳሳይ በማዕከል ተዘጋጅቶ በኦንላይን የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል።

ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከዚህ ቀደም በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ በመንግሥት ኃላፊዎች መገለጹ ይታወሳል።

ይህም ፈተና የሚሰጥበትን ቀን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር ዝርዝር መረጃ የሚያወጣ በመሆኑ፤ እስከዛው ዝግጅታችሁን አጠናክሩ።

@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
2.7K viewsAnwar, 07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 19:05:53 #MoE

"በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ 49 ሺ ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ዘመቻ ከአንድ ወር በኋላ ይጀመራል" - የትምህርት ሚኒስቴር፡፡

የትምህርት ምዘና ጥናት ውጤቶችን ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ አውደ ጥናት በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በመድረኩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ የትምህርት ጥራት ውጤት ምዘና እንዲሁም የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ምዘና ጥናት ይፋ ሆኗል።

በናሙና በተወሰዱ ትምህርት ቤቶች በተደረገው ምዘና ዝቅተኛ ውጤት መገኘቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሥርዓቱን አሁን ባለበት ሁኔታ ይዞ መቀጠል አይቻልም ያሉት ሚኒስትሩ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት 49 ሺ ትምህርት ቤቶች የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በመሆኑም ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ዘመቻ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር ይፋ አድርገዋል፡፡ በዘመቻው ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና ማህበረሰቡ ተሳታፊ እንደሚሆኑ አመልክተዋል፡፡

ርዕሰ መምህራንን ለማብቃት የሚያስችል ማዕከል እየተቋቋመ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ #EPA   #MoE
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.9K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 17:59:09
Exit Exam model Questions.

Chemical Engineering.
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
2.6K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 14:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 19:15:28
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ መመዘኛ ፈተና (IELTS Test) በተቋሙ ዋና ግቢ መስጠት ሊጀምር ነው።

ዩኒቨርሲቲው ከብሪቲሽ ካውንስል ጋር በመተባበር ፈተናውን መስጠት እንደሚጀምር ገልጿል።
@Ethio_Students_only
@Ethio_Students_only
@Elshio_Academy
1.1K viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ