Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 132.13K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 284

2022-05-15 22:32:42
በሱማሊያ ማምሻውን በተካሄደው ሁለተኛ ዙር ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ፉክክር የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ 110 ድምጽ እና የወቅቱ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ፎርማጆ 83 ድምጽ በማግኘት በማግኘት አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው ለሦስተኛው ዙር ምርጫ አልፈዋል።

በመጀመሪያው ዙር በ65 ድምጽ በአንደኛ ደረጃ ሲመሩ የነበሩት የፑንትላንዱ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ እና የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ሐሰን ካይሬ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ በማግኘት ከፉክክሩ ውጭ ሆነዋል። ሁለተኛውን ዙር ፉክክር በቀዳሚነት ያሸነፉት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ከአሁኑ ፕሬዝዳንት ፎርማጆ በፊት አገሪቱን የመሩ ናቸው።[ዋዜማ ራዲዮ]
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
5.7K viewsedited  19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 20:58:38
"መንግሥት ከሕወሓት የሚቃጣ የትኛውንም ዓይነት ጥቃት ለመመከት በየትኛውም ጊዜ ሙሉ ዝግጁነት፣ ዐቅም እና ብቃት አለው":-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ለገሰ ቱሉ መንግሥታቸው ከውስጥም ከውጪም የሚቃጣ የትኛውንም ዓይነት ጥቃት ለመመከት ዝግጁ ነው ብለዋል። ፖለቲካዊ ይዘት ባላቸው መገፋፋቶች ምክንያት እየጠፋ ያለን የሰው ሕይወትና የንብረት ውድመትን ለመግታት ብሎም አገራዊ አንድነትን ለማስከበር በሁሉም ክልሎች የተቀናጀ ያሉት እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ሕወሓት አሁንም የአፋር እና የአማራ ክልል ወረዳዎችን በኃይል እንደያዘ መሆኑን የገለፁት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ መንግሥት ወደ ትግራይ የሚልከውን የሰብዓዊ እርዳታ እንደማያቋርጥ አስታውቀዋል። ይሁንና በመጪው ክረምት የትግራ ሕዝብ የመኸር አዝመራ ግብዐት ካላገኘ ይበልጥ ለረሃብ ሊጋለጥ ይችላል የሚል ሥጋት በመንግሥት በኩል እንዳለ ጠቅሰው ሕወሓት ጦርነትን ከመጎሰም እንዲቆጠብ አሳስበዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
10.4K viewsedited  17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 20:56:57
በርካታ የመኪና ግብይት አማራጭ ያሉትን ይህን ቻናል ይቀላቀሉ፣ ይጎብኙ፣ ይገበያዩ!

http://T.me/EthioCarMarket
9.5K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 20:44:22
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
9.8K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 19:08:27
ወልድያ ከተማ የ"መቀመጭት" ተራራን በአቡነ ኤርምያስ ስም መሰየሙን አስታወቀ!!

ወልድያ ከተማ አስተዳደር የ"መቀመጭት ተራራን" "አቡነ ኤርምያስ ተራራ" ብሎ መሰየሙን አስታውቋል። የተራራውን ስያሜ የሰጠው ከተማ አስተዳደሩ አቡነ ኤርምያስ ያደረጉትን ውለታ በማሰብ እና ለአቡኑ ተያያዥ የልማት የቤት ሥራዎች ለመስጠት መሆኑን ገልጿል።

የዕፅዋት ሳይንስ መድኃኒት ቅመማ ጋር ተያይዞ ለምርምር የሚሆኑ ሀገር በቀል ዕፅዋቶች በስፋት የሚገኙበት ተራራ በመሆኑ የጥንት መጻሕፍትን በመተርጎም የሚመራመሩ ሊቃውንትን በተራራው በማሰማራት የምርምር ማዕከል እንደሚያደርጉት ታላቅ ተስፋ ስለተጣለባቸው ስያሜው የተሰጠበት አንደኛው ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
12.4K viewsedited  16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 18:29:03
የቻይናው ባሉን የዓለም በከፍታ የመብረር ክብረ ወሰንን ሰበረ!!

የቻይናው ተንሳፋፊ ባሉን ከምድር 9 ሺህ 32 ሜትር ከፍታ ላይ መንሳፈፍ በመቻሉ ነው የዓለም የከፍታ ክብረ ወሰንን የሰበረው።

በጉዙፍነቱ ምክንያት “ተንሳፋፊው መርከብ” ተብሎ የሚጠራው እና‹‹ጂሙ ቁጥር 1›› በሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ባሉን 2.625 ቶን የሚመዝን ሲሆን ሂሊየም በተሰኘ ጋዝ ተሞልቶ በአየር ላይ በሰከንድ 30 ሜትር የሚቀዝፍ እንደሆነ ተነግሯል።

ከ8 ሺህ 840 ሜትር በላይ ከሚረዝመው እና በቻይና እና በኔፓል ድንበር አካባቢ ከሚገኘው ኮሞላግማ ተራራ ጫፍ ከሚገኘው የምርምር ጣቢያ የተለቀቀው ባሉኑ ከ9 ሺህ ሜትር በላይ በመንሳፈፍ ነው ክብረ ወሰኑን ለመስበር የቻለው።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
13.3K viewsedited  15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 14:35:26
ዛሬ ምሽት ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ይታያል!!

በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች ዛሬ ምሽት እና ነገ ማለዳ ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ እንደሚታይ ቢቢሲ ዘግቧል።

ከግርዶሹ ደቂቃዎች በፊት ጨረቃ ብርቱካናማ ቀይ መልክ ይዛ ወይንም “ደም ለብሳ” የምትታይ ሲሆን ክስተቱ ከፕላኔታችን አስደናቂ እይታዎች አንዱ የሆነው የጨረቃ ግርዶሽ በሰማይ ላይ ይሆናልም ተብሏል።

ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ የሚፈጠረው ምድር በፀሐይ እና በጨረቃ መካከል በምትሆንበት ጊዜ የሚከሰት ነው።

ክስተቱ በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገራት ሰኞ ማለዳ እንደሚታይ የሚጠበቅ ሲሆን በአሜሪካ ደግሞ በአንፃሩ ዛሬ እሁድ ምሽት ላይ ያያሉ ነው የተባለው።

ጨረቃ ከምህዋሯ በጣም ቅርብ በሆነ ቦታ ላይ እንደምትሆንና ከወትሮው በበለጠ ተልቃና ገዝፋ እንደምትታይም ይጠበቃል ተብሏል። በመሆኑም ማንኛውም ሰው የጨረቃ ግርዶሹን ክስተት በዓይን ማየት የሚችል ሲሆን አቅርቦ ማሳያ (ባይኔኩላር) ወይም አነስተኛ ቴሌስኮፕ በመጠቀምም የሚፈጠረውን የቀይ ቀለም የበለጠ ለማየት ይችላል ነው የተባለው።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
752 viewsedited  11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:42:03
በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይጀመር ኢሰመኮ አሳሰበ!!

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን “በፌደራል መንግስት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል” ዳግም እየተካረረ የመጣው የጦርነት ስጋት እንዳሳሰበው ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ተቋሙ በመግለጫው እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይጀመር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አሳስቧል። ከ19 ወራት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በርካቶች ለተለያዩ አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደተጋለጡ ያወሳው ኢሰመኮ አሁንም ዳግም ወደ ጦርነት ለመግባት እያደገ የመጣው መካረር ሊቆም እንደሚገባ ገልጿል።

ጦርነቱ በአፋር፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ለከፋ እንግልት እንዲዳረጉ፣ የሚወዷቸውን ሰዎች እንዲያጡ፣ ህይወታቸውን በእርዳታ ላይ እንዲመሰረቱ፣ መሰረታዊ የዜጎች አገልግሎቶችን እንዲነፈጉ እና የሌሎችን ጉዳቶችን እያስተናገዱ እንደሚገኙም ተቋሙ ከዚህ በፊት ባደረኳቸው ተደጋጋሚ ምርመራዎች አረጋግጫለሁ ብሏል።

የፌደራል መንግስትን ጨምሮ የሰሜን ኢትዮጵያ ሶስቱ ክልሎች ዋነኛ ትኩረት ሊሆን የሚገባው በጦርነቱ ለተጎዱ ዜጎች ያለምንም ገደብ የሰብዓዊ መብት ድጋፎች እንዲደርሱ ማድረግ እንደነበርም ኢሰመኮ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። እንዲሁም በጦርነቱ ምክንያት የምርት እጥረቶች እና የዋጋ መናር ተከስቶ ዜጎች በአስከፊ ሁኔታ ህይወታቸውን እንዲገፉ ተገደዋል ያለው ኢሰመኮ ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ መፈለግ ይገባል ብሏል።

በመሆኑም በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ወይም ኢጋድ አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ የበኩላቸውን እንዲወጡ ኢሰመኮ አሳስቧል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
5.8K viewsedited  09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 11:34:28
Welcome to Invicta Report. Home of Political Incorrectness.

The latest news, war coverage, economy, culture, science and what the Mainstream Media doesn't want you to know. News you don't get anywhere else.

Channel: t.me/InvictaReport
Chat: t.me/InvictaGroup 
7.0K views08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 11:19:26
የገርጂ ዘመናዊ መኖሪያ መንደር በተለያዩ አካላት ተጎበኘ!!

በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው እና የአልሙኒየም ፎርምወርክ የግንባታ ቴክኖሎጂ ውጤት የሆነው የገርጂ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደርን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጣሰው ወልደሃና (ፕ/ር) እና ባለሀብቱ ነጅብ አባቢያ ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም ኮርፖሬሽኑ በግንባታ ቴክኖሎጂ እና አስተዳደር እያሳየ ባለው የላቀ አፈጻጸም የመኖሪያ መንደሩን በ18 ወራት ግንባታውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ መቃረቡ ተገልጿል።

ይህም በሀገሪቱ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ተስፋ ሰጪ መሆኑ ተነግሯል፡፡

በዚህ ፕሮጀክት ጥራትን፣ ቅልጥፍና እንዲሁም ዘመናዊነትን አጣምሮ እጅግ ዘመናዊ መኖሪያ መንደር በአጭር ጊዜ መገንባት መቻሉ ኮርፖሬሽኑ ብቃት ባላቸው እና የፕሮጀክት አስተዳደር እውቀት ባካበቱ አመራሮች እየተመራ መሆኑን ማሳያ መሆኑን የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
7.3K viewsedited  08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ