Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.93K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 280

2022-05-22 15:13:17
የ6ኛ ዕዝ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሮች የሚሰጣቸውን ግዳጅ በድል ለመወጣት በሚያስችላቸው ዝግጁነት ላይ እንደሚገኙ አስታወቁ።

በ6ኛ ዕዝ የሜካናይዝድ ዋና አዛዥ ኮለኔል ደሳለኝ ፈይሳ በህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት የሜካናይዝድ ክፍሎቻችን የጠላትን አንገት በማስደፋት እና ለተዋጊው የጦር ክፍሎቻችን የተኩስ ድጋፍ በመስጠት አኩሪ ሥራዎችን ሰርተዋል ብለዋል።

የታጠቅናቸውን ከባድ መሳሪያዎች በማጠናከር እና የተለያዩ ስልጠናዎችን በማካሄድ ብቃት ያለው የመሳሪያ ምድብተኞችን በማፍራት በጠላት ላይ የበላይነትን መጎናጸፍ የሚያስችል የዝግጁነት ሥራዎችን በሚፈለገው ልክ ሰርተናልም ብለዋል። በቀጣይ የሚሰጡንን ማንኛውንም ግዳጆች ለመፈጸም የሚያስችል በቂ የሆነ አቅም መገንባት ችለናል ያሉት ኮለኔል ደሳለኝ ፈይሳ የሠራዊቱ ሞራልና ስነ ልቦናዊ ዝግጁነቱም በከፍተኛ ደረጃ መገንባቱን መግለጻቸውን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ አመላክቷል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
15.2K viewsedited  12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 13:28:37
መንግስት፤ ህወሓት “ምርኮኞች”ን ለቅቄያለሁ የሚለው አለም አቀፉን ማህበረሰብ ለማሳሳት ነው አለ!!

የኢትዮጵያ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህወሓት ምርኮኛ ወታደሮችን ለቋል የሚለው ሀሰት ነው ሲል አስተባብሏል፡፡

ሰሞኑን ህወሓት በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ማርኬያቸዋለሁ ያላቸውን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለቅቄያለሁ ማለቱን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ይህ የህወሃት ድርጊት አለምአቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ለመሳብ የተደረገ “ሀሰተኛ ፕሮፖገንዳ” ነው ብሏል፡፡

“መንግስት ጉዳዩን አስመልክቶ እያደረገ ባለው ማጣራት በሽብር ቡድኑ ምርኮኞች ናቸው ተብለው የተለቀቁት አብዛኞቹ ዜጎች የመከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ክልል ለቆ በወጣበት ወቅት በሽብር ቡድኑ ታግተው የቀሩ የሰራዊቱ ቤተሰብ አባላት መሆናቸው ታውቋል።” ከሰራዊት ቤተሰቦች በተጨማሪም ህወሃት በአፋር እና በአማራ ክልል በቆየባቸው ወቅት በግዳጅ ይዞ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽምባቸው የነበሩትን ሰዎች እና “ከልዩ ልዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ለስራ ትግራይ ክልል ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ሲቪል ነዋሪዎችን” ምርኮኛ ማስመሰሉን መንግስት ገልጿል፡፡

መንግስት ህወሓት ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት በማሰብ “የተለያዩ ጸጥታ ሃይሎችን መለዮ በማልበስ በምርኮኛ ስም አሰልፏቸዋል” ብላል፡፡የህወሃት ድጋሚ ጦርነት ለመጀመር ያለውን ፍላጎት የሚሳይ ነው ያለው መግለጫው “በምርኮኛ ስም” ሰርጎ ገቦችን ለእኩይ አላማ ማደራጀቱን ደርሰንበታል ብሏል መንግስት፡፡(የመንግስት-ኮሙኒኬሽን)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
15.5K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 13:10:07
ቴሌግራም https://telegram.me/onlineshoppingce
አድራሻችን:- ቦሌ መድሐኔዓለም ቦሌ መሰናዶ ት/ቤት ፊትለፊት አለምነሽ ፕላዛ ሱቅ ቁጥር 05

+251941661030
14.3K views10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 12:10:09
የእሳት አደጋው በቁጥጥር ስር ውሏል!!

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መሃል መርካቶ ምን አለሽ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በተከሰተው የእሳት አደጋ የንብረት ውድመት ያጋጠመ ሲሆን የእሳትና ድንገተኛ መከላከል ሰራተኞች፣ የአካባቢው በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና የፀጥታ ሃይሎች ባደረጉት ርብርብ የከፋ ጉዳት ሳያስከትል በቁጥጥር ስር ለማዋል ተችሏል።

https://www.facebook.com/100075981277063/posts/157745723434803/?app=fbl

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
15.0K viewsedited  09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 11:33:45
#Alert
በአዲስ አበባ ምንአለሽ ተራ አካባቢ የእሳት አደጋ ተከስቷል!!

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መርካቶ በተለምዶ ምን አለሽ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከባድ የእሳት አደጋ ተከስቷል።

አደጋው የከፋ ጉዳት ሳያደርስ ለመከላከል በርካታ የአካባቢው ወጣቶችና የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ባለሙያዎች ርብርብ እያደረጉ ነው። የአደጋውን መንሰኤና ዝርዝር ጉዳዩን መረጃው እንደደረሰን እናቀርባለን።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
14.4K viewsedited  08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 01:25:19
#ጤናመረጃ

ሙዝ ለጤናችን የሚሰጠን 12 አስደናቂ ጥቅሞች!

ሙዝ በንጥረ ነገር ይዘታቸው ከበለፀጉ ፍራፍሬዎች አንድ ሲሆን በውስጡ በርከት ያሉ እንደ ማግኒዚየም ፣ ፓታሲየም ፣አይረን፣ ዚንክ፣ አዮዲንና ቫይታሚን ኤ፣ቢ፣ኢ፣ኤፍን ይዛል።

1- የሀይል ምንጭ ነው:- ሙዝ በውስጡ ቫይታሚን፣ሚኒራል እና ካርቦሀይድሬት በመያዙ ሀይል ለማግኘት ይጠቅማል፡፡

2- ለምግብ መንሸራሸር ይጠቅማል:- ይህም የሚሆነው ሙዝ በውስጡ የቃጫ ባህሪ(ፋይበርነት) ስላለው ነው፡፡

3- የጨጓራ ህመምን ያስታግሳል:- ጨጓራ ጠንካራ ግድግዳ እንዲኖረው እና በጨጓራ ውስጥ ያለውን አሲድነት በመቀነስ ህመምን ያስታግሳል፡፡

4- የልብን ጤንነትን ይጠብቃል:- ሙዝ በፖታሲየም የበለፀገ ስለሆነ ይህም ለልብ ጤንነት አስፈላጊ ነው፡፡

5- ክብደትን ለመቀነስ ይረዳል:- ሙዝ በውስጡ አነስተኛ ቅባት እንደዚሁም ብዙ ፋይበር ሰለያዘ ክብደትን ለመቀነስ ይረዳል፡፡

6- አኔሚያን ለማከም ይረዳል:- ሙዝ በውስጡ በዛ ያለ የብረት ማእድን ስለያዘ ይህም የቀይ የደም ሴልን ማነስ ይከላከላል፡፡

7- ነብሰጡሮችን ከህመም ይታደጋል:- ነብሰጡር ሴቶችን የሚያጠቃ የጠዋት ህመም የሚባለውን ለማከም ይረዳል፡፡

8- የአይንን ጤና ያሻሽላል:- ሙዝ ቫይታሚን ኤን ስለያዘ የአይን በሽታን ይከላከላል፡፡

9- በወባ ትንኝ የተነደፈን ይፈውሳል:- የተነደፈበት ቦታ በሙዝ ልጣጭ በማሸት ከህመሙ ይፈውሳል፡፡

10. ጥርስን ያነጣል፦ በሙዝ ልጣጭ ጥርስዎን ሁልጊዜ ጥርስዎን ሲፍቁ ለአስደናቂ ፈገግታ ይኖርዎታል።

11. የተጎድ የሰውነት ቆዳን ያስተካክላል፣ የፊት መሸብሸብ እና የቆዳ መሰንጠቅን ይከላከላል።

12. ክንታሮትን ያድናል:- ሙዝ በፓታሲየም የበለጸገ ስለሆነ ክንታሮትን የማዳን አቅም አለው።

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
@ethio_mereja
987 views22:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 23:14:34
"ሺህ ጊዜ ገጥመውን ሺህ ጊዜ እንዳሸነፍናቸው ከዚህ በኋላ ለጠላቶቻችን ያለን ምክር ደጋግማችሁ ማሰብ አለባችሁ! የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እንኳን ዛሬ ትናንትም አልተሸነፈም፡፡"
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) የኢፌዴሪ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

"ዛሬ ትናንት ከነበርንበት በብዙ እጥፍ የተሻለ ቁመና ላይ እንገኛለን፡፡ ባዶ እጃችንን ሆነን በእምነት ፤ኢትዮጵያ አትፈርስም ብለን ነበር፡፡ዛሬ ግን አስተማማኝ መከላከያ ይዘን ኢትዮጵያ ዳግም አትፈርስምብለን መናገር የሚያስችል ሁኔታ ላይ እንገኛለን፡፡ አትፈርስም ስንል የሚተነኩሱ ፤ ባንዳዎችን የሚልኩ ሃይሎች የሉም እያልን አይደለም፡፡

ባንዳዎችም የሚልኳቸው ሃይሎችም ኢትዮጵያን አትሞክሩ ከሞከራችሁ በደማችን በአጥንታችን እኛ ሞተን እናስቀጥላታለን፡፡ ሺህ ጊዜ ገጥመውን ሺህ ጊዜ እንዳሸነፍናቸው ከዚህ በኋላ ለጠላቶቻችን ያለን ምክር ደጋግማችሁ ማሰብ አለባችሁ፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እንኳን ዛሬ ትናንትም አልተሸነፈም፡፡"

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) በዛሬው እለት የመከላከያ ዋር ኮሌጅ በደህንነትና ስትራቴጂ ጥናት ያሰጠለናቸውን መኮንኖች ባስመረቀበት ወቅት የተናገሩት!

https://www.facebook.com/100075981277063/posts/157585320117510/?app=fbl (follow)

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
4.0K viewsedited  20:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 21:34:42
በአዲስ አበባ አዲስ ቤተመንግሥት በ49ቢሊዮን ብር ሊገነባ መሆኑ ተሰምቷል!!

የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት በ49 ቢሊዮን ብር ወጪ በአዲስ አበባ የካ ተራራ ላይ አዲስ ቤተ መንግሥት ሊገነባ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል።

አዲሱ ቤተ መንግሥት በ503 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፍ እንደሆነ ዘገባው ከጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ምንጮች መስማቱን ገልጧል። "ጫካ ፕሮጀክት" የሚል ስያሜ ለተሰጠው የአዲስ ቤተ መንግሥት ግንባታ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች የሚፈናቀሉ ሲሆን ሆኖም ነዋሪዎቹ ቤተ መንግሥቱ የሚታነፅበት አካባቢ ካለው ደረጃ ጋር የሚስማማ ከሆነ በመሬታቸው ላይ የራሳቸውን ንብረት እንዲያለሙ ዕድል ይሰጣቸዋል ተብሏል።

አምስት ወረዳዎችንም የሚነካ ሲሆን በውስጡም የአዳራሽ፣ የሰው ሰራሽ ሀይቅ፣ የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የመንገድ ጨምሮ ሌሎች ግንባታዎችን ያካትታል የተባለ ሲሆን የመንገዶች ባለሥልጣን የካ አካባቢ የግንባታው አካል የሆነ የ20 ኪሎ ሜትር መንገድ ከወዲሁ መስራት ጀምሯል።

ለቤተ መንግሥቱ ግንባታ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ከፊሉን ወጪ ትሸፍናለች ተብሏል።የምኒልክ ቤተ መንግሥትን በአንድ ቢሊዮን ብር እድሳት ላይ ካለው የኢዮቤልዩ ቤተ-መንግስት ጋር ወደ ብሔራዊ ሙዚየምነት ሊቀየር ታስቧል።(ሪፖርተር)

https://www.facebook.com/100075981277063/posts/157584673450908/?app=fbl

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
8.8K viewsedited  18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 20:49:34
ሩሲያ 963 የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ አገደች።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ይፋ ባደረገው እና «ሙሉ» ባለው ስም ዝርዝር ውስጥ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንቶኒ ብሊንከን እና የማዕከላዊ የስለላ ድርጅት (CIA) ኃላፊ ዊልያም በርንስ ይገኙበታል።

ሩሲያ በአሜሪካዊያኑ ላይ ይህንን ርምጃ የወሰደችው የአሜሪካ መንግሥት ባህሪውን እንዲለውጥ እና "አዲስ የጂኦፖለቲካዊ እውነታዎችን" እንዲቀበል ግፊት ለማድረግ ነው ብላለች።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ዛሬ አዲሱን የ40 ቢሊዮን ዶላር የዕርዳታ ድጋፍ ለዩክሬይን ፈርመዋል። የአሜሪካ ኮንግረስ ርዳታውን ካፀደቀ በኋላ የሚቀረው የፕሬዚዳንቱ ፊርማ ብቻ ነበር ።

ከድጋፉ ስድስት ቢሊዮኑ ዶላር የሚውለው ጥይት ለማይበሳቸው ተሽከርካሪዎች እና ለዩክሬን ጦር ኃይሎች የአየር መከላከያ ዘዴዎች ሲሆን ዘጠን ቢሊዮን ዶላር ደግሞ አስቀድሞ ወደ ዩክሬይን የጦር መሣሪያ ለላከው የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ኃይል የተመደበ ነው ተብሏል። ከጦር መሣሪያ ድጋር ባሻገር ዩናይትድ ስቴትስ ለሰብአዊ ዕርዳታ የሚሆን ተጨማሪ ገንዘብ ለዩክሬን መመደባ ተገልጿል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
10.5K viewsedited  17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 20:41:56
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+P7ctetopPExiY2Rk
9.9K views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ