Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja — ETHIO-MEREJA®
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.05K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 278

2022-05-31 14:49:33
ቻይና 30 የጦር አውሮፕላኖችን ወደ ታይዋን የአየር መከላከያ ቀጠና ላከች

የታይዋን መከላከያ ሚኒስቴር በቀጠናው የቻይና ድርጊት 22 ተዋጊ የጦር አውሮፕላኖች፣ የጸረ-ሰርጓጅ መርከብና ቅድመ ማስጠንቀቂያ አውሮፕላኖች መታየታቸውን ገልጿል፡፡ ሚኒስቴሩ የጦር አውሮፕላኖቹ "ፓራታስ" ተብሎ በሚታወቀውና የአየር መከላከያ ስፍራ በሆነው የታይዋን ሰሜን ምስራቅ ክፍል አካባቢ መብረራቸውን አስታውቋል፡፡ይሁን እንጂ አውሮፕላኖቹ የታይዋን አየር ክልል ጥሰው እንዳልገቡ ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው፡፡

ሃገራት የአየር ቀጣናን እንደ ሉዓላዊ ይዞታ ይመለከታሉ፡፡ በተደራጁ የቅኝት መንገዶች የሚጠበቁ የራሳቸው የአየር መከላከያ ቀጣናዎችም አሏቸው፡፡ በዚህም ያለ ፈቃድ የአየር ክልሉን ጥሶ የሚገባም ሆነ የሚያልፍ አይኖርም፡፡

የአሁኑ የቻይና ድርጊት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ቻይና ታይዋንን ከመውረር እንድትቆጠብ የሚል ጠበቅ ያለ ማስጠንቀቂያ ከሰጡ ከጥቂት ቀናት በኋላ በትናንትናው እለት የሆነ ነው፡፡ይህ ብቻ አይደለም አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን ወደ ታይዋን በማቅናት አሜሪካ እና ታይዋን በጸጥታ ጉዳዮች በጋራ በሚሰሩባቸው የትብብር ማእቀፎች ዙርያ ከመከሩ በኋላ የሆነ እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡

የጦር አውሮፕላኖች ወደ ታይዋን የአየር ክልል ዘልቀው መግባታቸው ታይዋንንና የምዕራቡ ዓለም አጋሮቿን ቢያስቆጣም፤ ቻይና ግን ልምምድ ለማድረግ መሆኑ በመግለጽ ላይ ናት፡፡
T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja
14.2K viewsedited  11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 12:36:20
ህወሃት ኤርትራን እየተነኮሰ መሆኑን የኢትዮጵያ መንግስት ገልፀ፡፡

የህወሓት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ቅዳሜና ዕሁድ ዕለት የኤርትራ ሠራዊት በሽራሮ በኩል ጥቃት ከፍቶ እንደነበር ቢገልጹም የኢትዮጵያ መንግስት ግን ቀድሞ ትንኮሳ ያደረገው ህወሃት እንደሆነና በዚህም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል ብሏል፡፡

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ህወሃት የኤርትራ ጦር ጥቃት ከፈተ በሚል የሚያሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም፡፡

የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ቅዳሜና እሁድ ተከስቷል ካሉት ግጭት በተጨማሪ ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ. ም የኤርትራ 57ኛ እና 21ኛ ክፍለ ጦሮች ወደ ትግራይ ክልል ጥቃት ሰንዝረው ነበር ብለዋል፡፡ አቶ ጌታቸው የኤርትራ ጦር ጥቃት መሰንዘሩን እና አዲአዋላ በተባለው አካባቢ በነበረ ውጊያ የህወሃት ታጣቂዎች ጥቃቱ መክተዋል ብለዋል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ ደግሞ በውጊያው በርካቶች መቁሰላቸውንና ለህልፈት መዳረጋቸውን ገልጸው የጦር መሳሪያም ጭምር መማረካቸውን ተናግረዋል፡፡

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚ/ር ለገሰ (ዶ/ር) ግን ትንኮሳ ያደረገው ህወሃት እንደሆነና የተመቱትም ራሳቸው የህወሃት ታጣቂዎች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ ሚኒስትሩ በኤርትራና በህወሃት መካከል ግጭት እንዲፈጠር ያደረገው ህወሃት መሆኑን ገልጸው በዚህ ሁኔታ ህወሃቶች “ሬሳ እንኳን ማንሳት አልቻሉም፤ በጣም ብዙ ሰው ወድሞባቸዋል” ሲሉም ነው የተናገሩት።

ህወሃት ትንኮሳውን የሚፈፅመው ሁለቱን ሀገራት ወደ ግጭት ለማስገባት እንደሆነ የገለጹ ሲሆን ይህ ግን መቼም ቢሆን “አይሳከም”ብለዋል፡፡መንግስት በአካባቢው ያለውን ሁኔታ በተመለከተ መረጃ እንዳለው ያስታወቁት ሚኒስትሩ፤ ሁለቱ ሀገራት መቸም ቢሆን ወደ ግጭት አይገቡም ብለዋል፡፡(አልአይን)

T.me/ethio_mereja
15.6K viewsedited  09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 12:18:43
ምርት እና አገልግሎቶን በቅናሽ ያስተዋውቁ!!

➠ ሱቆች ➠ ሆቴሎች እና ሬስቶራንት
➠ ሽያጭ ➠ ቴሌግራም ቻናል
➠ ድርጅት ➠ የቲቪ ፕሮግራም
➠ ት/ቤቶች ➠ ስልጠናዎች
➠ ሆስፒታል ➠ ክሊኒኮች
➠ websites ➠ Events
➠ባዛሮች ➠ ዝግጅቶች እና ሌሎችንም

የድርጅታችሁን ወይም የሱቃችሁን ህጋዊነት በማረጋገጥ ምርትና አገልግሎቶን እንዲያስተዋውቁ እድሉን አመቻችተናል። በቻናላችን በማስተዋወቅ ለብዙዎች ይድረሱ... ትርፋማ እና ተመራጭ ይሁኑ።

የቀሩት ጥቂት ቦታዎች ናቸው።
ከታች ባሉት ሊንኮች ያነጋግሩን።
@Antenehg1
@ethio_merejabot

----ETHIO-MEREJA-----
14.6K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 12:18:34
በነጻ ተጨማሪ የሕክምና ምክርን ከእኛ ያግኙ

አቺባደም ሆስፒታል

ትክክለኛውን ምርመራ ለማድረግ ወይም ተገቢውን የሕክምና አማራጮችን ለመለየት ከፈለጉ ተጨማሪ የሐኪሞች አስተያየትና ምክርን ማግኘት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በቱርክ የሚገኘው አቺባደም የጤና ክብካቤ ቡድን ይህንን አገልግሎት በነጻ ይሰጣል። የህክምና መረጃዎን በማቅረብ ከአለማችንን የታወቁ የህክምና ባለሙያዎችን አስተያየትና ምክር ማግኘት ይችላሉ።

ለተከታታይ ጠቃሚ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/acibadem_ethiopia ይቀላቀሉ፡፡
14.7K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 23:53:30
#ጤናመረጃ

ጥቁር አዝሙድ ለጤናችን የሚሰጠን አስደናቂ ጥቅሞች


በጥቁር አዝሙድ ውስጥ ለሰው ልጅ ጠቃሚ የሆኑ ከ100 በላይ የተለያዩ የኬሚካል ንጥረ ነገሮች አሉ። እንደ ካልሲየም፣ ፖታሲየም፣ ብረት፣ ዚንክ፣ ማግኒዥየም፣ ሲኒየም፣ ቫይታሚን ኤ፣ ቫይታሚን ቢ፣ ቫይታሚን ቢ2 ና ሲ የመሳሰሉት ፕሮቲኖች መገኛ ነው።

የአለርጂ በሽተኞች አሉታዊ ምልክቶችን ለመቀነስ የሚረዳ እንደ ፀረ-ሂስታሚን በውስጡ ይዟል።መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ከሰውነት ለማፅዳት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።

ለስኳር በሽታ የኢንሱሊን መጠንን ለመቆጣጠር፣ ኮሌስትሮልን፣ የሰውነት ዝውውርን ያሻሽላል እንዲሁም ጤናማ የጉበት ሥራን ያበረታታሉ።

ደረቅ ሳልን ለማስታገስ ከቡና ጋር ቀላቅሎ መጠጣት ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ አለው፣ የፊት መሸብሸብንና ቴታነስን ለመከላከል ጥቁር አዝሙድን ከሞቀ ውሃ ጋር ቀላቅሎ መጠቀም ይመከራል።

እንደ ሣል፣ ትኩሳት፣ አስም፣ የቆዳ ሽፍታ፣ እብጠትና የሆድ ድርቀትን ለማከም አገልግሎት ላይ ይውላል።

የፀጉር መሳሳት እና መላጣነትን ይከላከላል፣ የአይን ኢንፌክሽን፣ ህመም እና ደካማ እይታን ለመከላከል ዘይቱ ይጠቅማል።

በተበከለ ምግብ አማካኝነት የሚከሰትን ድንገተኛ ትውከትን ለማስቆም ይረዳል፣ የጥርስ ህመምን ለማስታገስ ግማሽ የሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ከሙቅ ውሃ ጋር ቀላቅሎ በተጎዳው ጥርስ ላይ በማፍሰስ ህመምን ማስታገስ ይቻላል።

የደም ግፊትን በጣም ይቀንሳል። ዘይቱ ጸረ-አልባሳት ባህሪዎች የደም ግፊትን እና ሌሎች የልብና የደም ቧንቧ በሽታዎችን ለማከም ጥቅም ላይ ይውላል።

በማንኛውም የሰውነት ክፍል ላይ አደገኛ የሆኑ ዕጢዎች መፈጠርን ይከላከላል፣ የወር አበባ ፍሰት እና እንቅስቃሴን ያበረታታል።

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
@ethio_mereja ኢትዮመረጃ
2.0K viewsedited  20:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 23:01:31
ትናንት ከተከሰከሰው የኔፓል አውሮፕላን አደጋ የ21 ሰዎች አስከሬን ተገኘ

ንብረትነቱ የግል አየር መንገድ የሆነ አነስተኛ የመንገደኞች አውሮፕላን በትናንትናው ዕለት 22 ሰዎችን አሳፍሮ በመብረር ላይ ሳላ በተራራማዋ የኔፓል ቦታ የደረሰበት መጥፋቱ ይታወሳል።

ባለስልጣናት እንደተናገሩት የአካባቢው ሰዎች እሳት ማየታቸውን ወደገለጹበት ቦታ የፍለጋ ቡድን ማሰማራታቸውን የገለጹ ሲሆን ዛሬ በወጣው የፍለጋ ሪፖርት መሰረት የ21 ሰዎች አስከሬን መገኘቱን ሮይተርስ ዘግቧል።

የቀሪ 1 ተሳፋሪ አስከሬን በመፈለግ ላይ መሆናቸውን የተናገሩት ባለስልጣናቱ ተጨማሪ መረጃዎችን በቀጣይ እንደሚሰጡም አክለዋል። አውሮፕኑ ለማረፍ አምስት ደቂቃ ሲቀረው ነው ከመቆጣጠሪያ ጣቢያው ጋር ግንኙነት የተቋረጠው።

T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja
3.7K viewsedited  20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 20:26:19
የትግራይ ክልል መንግሥት የኤርትራ ሠራዊት ትናንት እና ከትናንት ወዲያ የሽራሮ ከተማን በከባድ ጦር መሳሪያ ደብድቧል ሲል ዛሬ ማምሻውን በኮምንኬሽን ቢሮው በኩል ባወጣው መግለጫ ከሷል።

በሽራሮው የከባድ መሳሪያ ድብደባው በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል ያለው መግለጫው፣ የትግራይ ኃይሎች በሰጡት የአጸፋ ምላሽ አንድ የኤርትራ ጦር ብርጌድ አዛዥ እና ሦስት የሻለቃ አዛዦች የሚገኙባቸው 120 ወታደሮችን ገድለው 195 ያህሉን እንዳቆሰሉ እና አራት ወታደሮችን እንደማረኩ ገልጧል። በውጊያው አንድ ድሽቃ፣ አምስት የወታደራዊ ሬዲዮ መገናኛዎች እና በርካታ የጦር መሳሪያ መማረካቸውን ጨምሮ አውስቷል።

የክልሉ መንግሥት መግለጫ ባለፉት ሁለት ቀናት የኤርትራ ጦር በሽራሮ በኩል ጥቃት የከፈተው፣ ባለፈው ግንቦት 16 በምዕራብ ትግራይ ዓዲ አውዓላ አካባቢ የከፈተው ጥቃት የትግራይ ኃይሎች በወሰዱት አጸፋ ከሽፎ ጦሩ ክፉኛ በመመታቱ ነው ብሏል። የክልሉ መንግሥት በዚሁ መግለጫው፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የኤርትራን መንግሥት ድርጊት በቃ ለማለት እጅጉን ቢረፍድበትም፣ ፈጽሞ ግን አልመሸበትም በማለት መግለጫውን ቋጭቷል።

ምንጭ ፣ ዋዜማ ራዲዮ
T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja
10.9K viewsedited  17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 20:13:34
#ነዳጅ

የሰኔ ወር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል!!

በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም የቤንዚን፣ የናፍጣ እና የኬሮሲን  የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በግንቦት ወር ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ነገርግን የአውሮፕላን ነዳጅ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በዓለም አቀፍ ዋጋ ተሰልቶ የመጣው ልዩነት ሙሉ በሙሉ ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ ተወስኗል ነው የተባለው፡፡
T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja
10.7K viewsedited  17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 17:55:43
ጋዜጠኛ መዓዛ መሃመድ ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት የሚል ክስ ቀረበባት.

የሮሃ ሚድያ መስራች የሆነችው ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ ላይ ፖሊስ ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት የሚል ክስ አቀረበባት። ሮሃ ሚድያ እንደዘገበው ጋዜጠኛዋ ዛሬ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርባለች። ፖሊስ ባቀረበባት ክስ ላይ መረጃ ለማሰባሰብ የ14 ቀን ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ ጠበቃዎች በበኩላቸው ሰራች የተባለው ወንጀል ተፈፅሞ ቢሆን እንኳን ጉዳዩ ሊታይ የሚገባው በመገናኛ ብዙሀን አዋጅ ነው። በእስር እንድትቆይ ህጉ አይፈቅድም ሲሉ ተከራክረዋል። በተጨማሪም ጋዜጠኛዋ ከወራት በፊት ታስራ ማስረጃ ሊቀርብባት ባለመቻሉ ነፃ መደረጓን ገልፀው አሁንም “ሞጋች ጋዜጠኛ መሆኗ እንጂ የሰራችው ወንጀል የለም” በማለት አስረድተዋል።

ፍርድ ቤቱ ክርክሩን ካደመጠ በኋላ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።
T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja
13.6K viewsedited  14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 16:11:16
የተባበሩት መንግሥታት ሀገራዊ ምክክሩን በመደገፍ ከመንግሥትና ሕዝብ ጎን እንደሚቆም ገለጸ

ሀገራዊ ምክክሩ በሰላም ግንባታው ላይ የሚኖረውን አዎንታዊ ተፅዕኖ በመደገፍ ከኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ጎን እንደሚቆሙ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴቴክን ተናገሩ፡፡

የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዱዓለም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴቴክን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ሀገራዊ ዘላቂ የሰላም ግንባታ ሥራዎች፣ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች እየተደረገ ስለሚገኘው ሰብዓዊ ድጋፍና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ነው ውይይት ያደረጉት፡፡

ልዩ መልዕክተኛዋ ለትግራይ ክልል ሕዝብ እየቀረበ ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ መልካም የሚባል መሆኑን ገልጸው መንግሥት ለሰብዓዊ ድጋፉ ያሳየው ተነሳሽነት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡

በሌሎች ክልሎችም በተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚደረገውን ሰብዓዊ ድጋፍ በማገዝ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር እንሰራለን ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘውን የዘላቂ ሰላም ግንባታ ሂደት በመደገፍና በቀጣይ የሚደረገውን አካታች ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ ለማድረግና ሀገራዊ ምክክሩ በሰላም ግንባታው ላይ የሚኖረውን አዎንታዊ ተፅዕኖ በመደገፍ ከኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ጎን እንደሚቆሙ ገልጸዋል፡፡
T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja
14.4K viewsedited  13:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ