Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.93K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 281

2022-05-21 20:34:09
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
10.0K views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 19:00:12 በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሲንቀሳቀሱ በነበሩ የአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ!!

በዞኑ በሚገኙ በአቦቴ እና በወረጃርሶ ወረዳዎች በስፋት በመንቀሳቀስ ህበረተሰቡን ሲዘርፉ እና ሲያሰቃዩ በነበሩት የሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ በመወሠዱ በአሁኑ ወቅት በአካባቢዎቹ አስተማማኝ ሰላም መስፈኑ ተገልጿል።

በዞኑ ቀጣይነት ያለው ሰላም ለማስፈን በአካባቢው የተሰማሩት የጥምር ፀጥታ አካላት በሽብር ቡድኑ ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን የገለፁት የጥምር ፀጥታ አካላት አስተባበሪ እና በኮማንዶ ክፍለ ጦር የሬጅመንት ዋና አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ታሄል ሬድ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በተደረገው ሁሉን አቀፍ ዘመቻ በርካታ አመርቂ ድሎች እየተመዘገቡ ይገኛሉ ብለዋል።

ዋና አዛዡ እንደገለጹት፥ እስከ አሁን በተደረጉ ዘመቻዎች እርምጃ የተወሰደባቸው 44፣ የተማረኩ 05፣ ሲሆን 18 የተለያዩ መሳሪያዎች ተማርከዋል፣ የሽብር ቡድኑ ሲጠቀምበት የነበረም 19 ኩንታል እህል በቁጥጥር ስር ውሏል።

በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን የሰጡት ደግሞ 233 መሆናቸውን የጥምር ፀጥታ አካላት አስተባበሪ እና በኮማንዶ ክፍለ ጦር የሬጅመንት ዋና አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ታሄል ሬድ ገልፀዋል።

ከአካባቢው ህብረተሰብ፣ ከአገር ሽማግሌዎችና ከአባገዳዎች ጋር በመሆን በተሰራው የተቀናጀ ትብብር የተገኘው ድል አበረታች ነው ያሉት ደግሞ የወረጃርሶ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አየለ መንግስቱ ናቸው።

ከህብረተሰቡ የተወከሉ የአካባቢው ሽማግሌዎች እና አባገዳዎችን ወደ ጫካ በመላክ ከታጣቂዎቹ ጋር በተደረገው ድርድር እና ውይይቶች በርካታ የአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች በየቀኑ በሰለማዊ መንገድ እጃቸውን በአካባቢው ለተሰማራው ለፀጥታ አካላት እየሰጡ እንደሚገኙ የገለፁት ዋና አስተዳደሪው በአሁኑ ወቅት በአከባቢው አንፃራዊ ሰላም መስፈን መቻሉን ከመከላከያ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
12.4K viewsedited  16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 17:30:50
የከተማ አስተዳደሩ ሕንጻዎች ሊቀቡ የሚገባቸውን 13 የቀለም ዓይነቶች መለየቱን ይፋ አደረገ!!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋ ህንጻዎች ሊቀቡ ይገባቸውል ያላቸውን 13 የቀለም አይነቶችን መለየቱን ገልጿል።

ከተማ አስተዳደሩ የሕንጻዎችን ቀለም በተመለከተ ባወጣው ማብራሪያ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ እንድትሆን እና ዓለም ዐቀፍ ደረጃን የሚመጥን ገፅታ እንዲኖራት ለማስቻል ከሚሠሩ ሥራዎች አንዱ የሕንጻዎችን ቀለምና ቁመት የሚወስን አሠራርን መተግባር መሆኑን አስታውቋል።

እስካሁን ባለው ሂደት የከተማዋ ሕንጻዎች ያለምንም ቁጥጥር ወጥነት በጎደለው መልኩ ሕንጻዎች ቀለም የሚቀቡ ሲሆን እየተቀቡ ያሉ ቀለማት የከተማዋን መልክ ዥንጉርጉር ከማድረጋቸውም በላይ የሚገነቡ ሕንጻዎች ንድፍ በዘፈቀደ በመሠራቱ የተነሳ የከተማዋ ገፅታ በእጅጉ ተጎድቶ እንደሚገኝ አስተዳደሩ በመግለጫው ጠቁሟል፡፡

ይህን ችግር መልክ ለማስያዝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከብዙ ዓለም ዐቀፍ ከተሞች ተሞክሮ በመውሰድ ለከተማዋ የሚስማማ የሕንጻ ቀለማት ደረጃን አጥንቶ ለውይይት አቅርቧል፡፡

በውይይቱ የተሳተፉ በርካታ የዘርፉ ባለሙያዎች ሁኔታውን በተመለከተ ዝርዝር ጥናት በማድረግ ለከተማዋ የሚስማሙ 13 ዓይነት ቀለማት መለየታቸውን አስተዳደሩ ገልጿል።

በሌሎች ሀገራት እንደሚደረገው ሁሉ ለከተማዋ በመለያነት ከተመረጡ 13 ቀለማት መካከል የሕንጻ ባለንብረቶች የሚመርጡትን ወስደው የመጠቀም መብት ያላቸው ሲሆን ይህ አሠራር በሙከራ ደረጃ በተወሰኑ ክፍለ ከተሞች ተጀምሮ ወደ ትግበራ መገባቱንም ከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል፡፡

የተመረጡት ቀለሞች የሚከተሉት ናቸው ከላይ በምስል መልኩ ከዜናው ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.6K viewsedited  14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 17:24:41
Hair Dry Towel 

Quick Dry Hair Towel Cap 
Super Absorption Turban Hair Dry Cap

ዋጋ፦ 200 ብር

ውስን ፍሬ ነው ያለን/ Limited Stock

አድሚኑን ለማናገር @AwasMartAdmin

አድራሻችን:- ቦሌ መድሐኔዓለም ቦሌ መሰናዶ ት/ቤት ፊትለፊት አለምነሽ ፕላዛ ሱቁ 05

ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/onlineshoppingce

+251941661030
ይደውሉ
12.9K views14:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 14:40:30
የዝንጀሮ ፈንጣጣ፡ በ11 አገራት 80 ሰዎች መያዛቸው ተረጋግጧል! - የዓለም ጤና ድርጅት

በ12 ሀገራት በዝንጀሮ በሽታ የተጠቁ ከ80 በላይ ተጠቂዎች መኖራቸው ተረጋገጧል። የዓለም ጤና ድርጅት ሌሎች 50 ተጨማሪ የበሽታው ምልክት የታየባቸው ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

የዓለም የጤና ድርጅት የትኛውንም ሀገር ስም ሳይጠቅስ ተጨማሪ ሰዎች ላይ  ሊገኝ እንደሚችል አስጠንቅቋል።ኢንፌክሽኑ በዘጠኝ የአውሮፓ አገራት እንዲሁም በአሜሪካ ፣ በካናዳ እና በአውስትራሊያ ውስጥ መኖሩ ተረጋግጧል።

የእንግሊዝ ብሄራዊ የጤና አገልግሎት እንደገለጸው ይህ ያልተለመደ የቫይረስ ኢንፌክሽን ቀላል እና አብዛኛው ሰው በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ሊያገግም ይችላል ብለዋል። ቫይረሱ በሰዎች መካከል በቀላሉ የማይሰራጭ ሲሆን ይህም ያለው ስጋት በጣም ዝቅተኛ ያደርገዋል። ለጦጣ በሽታ የተለየ ክትባት ባይኖርም ለስሞል ፖክስ የሚዘጋጀው ክትባት 85 በመቶ መከላከል የሚችል ሲሆን ሁለቱ ቫይረሶች በጣም ተመሳሳይ ናቸው ተብሏል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
15.2K viewsedited  11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 13:26:51
በሺንሽቾ ከተማ የተገነባው ይቻላል ኢንተርናሽናል ሆቴል በደቡብ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በይፋ ተመርቀ።

የሺንሽቾ_ከተማ_ድምቀት፣ የከምባታ ጠምባሮ ዞን አርማ እና ተጨማሪ ውበት ይሆናል የተባለው ይቻላል ኢንተርናሽናል ሆቴል በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

በምርቃት ስነ ሥርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ተስፋዬ ይገዙ እና የከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ መለሰ አጭሶ ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ሀላፊዎች በመገኘት ሆቴሉን በይፋ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
14.9K views10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 13:04:16 ከሞጣ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

የሞጣ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ምክር ቤት በከተማዋ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ለማስተካከል በአሁኑ ሰዓት የጸጥታ መዋቅሩ በሙሉ አቅም እየሰራ ይገኛል፡፡ ስለሆነም መላ ህዝባችን ፦

1ኛ. ማንኛውም ህዝብ/ግለሰብ በቡድን ሆኖ በከተማዋ መንቀሳቀስ ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

2ኛ. ማንኛውም ሰው በህግ የሚፈለጉ አካላትን ደብቆ ወይም አከራይቶ ቢገኝ ተጠየቂ መሆኑን አውቆ ችግር ፈጣሪዎችንና ተፈላጊዎችን አሳልፎ እንዲሰጥ እናሳስባለን፡፡

3ኛ. ለህግ ማስከበር ሲባል ከጥዋቱ 12፡00 ሰዓት በፊትና ከምሽቱ 12፡30 ሰዓት በኋላ ስምሪት ከተሰጣቸው የጸጥታ ሃይሎች ውጭ እንቅስቃሴ ገደብ የተቀመጠ መሆኑን እያሳሰብን ይህንን በሚተላለፉ አካላት ላይ የጸጥታ ሃይላችን እርምጃ ለመውሰድ ይገደዳል፡፡

4ኛ. ስምሪት ከተሰጠው የጸጥታ ሃይል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

5ኛ. የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች ነገር ለማባባስ የሚሰሩና የጸረ ሰላም እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ግለሰቦችን እንዲመክሩ እየጠየቅን የከተማችን ወጣቶችና መላ ህዝቡ ከጸጥታ መዋቅሩ ጎን እንዲቆሙ ጥሪያችንን እያቀረብን ከላይ የተጠቀሱ ክልከላዎችን በመተላለፍ ለሚወሰድ እርምጃ ምክርቤቱ ኃላፊነት አይወስድም፡፡

ግንቦት 13/2014ዓ.ም
የሞጣ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ጸጥታ ም/ቤት
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.8K viewsedited  10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 00:40:44
#ጤናመረጃ

የልብ ድካም ምክንያቶችና መፍትሔዎቹ!

ልብ ድካም ማለት ልብ ሙሉ በሙሉ ስራዋን ማቆም ሳይሆን በውጤታማነት በጤነኛ መንገድ ተግባሯን ማከናወን አለመቻል ማለት ነው፡፡

......
የልብ ድካም ሊያደርሱ የሚችሉ ምክንያቶች!

1.የልብ ደም ቧንቧ መጥበብ፡- ስብ/ኮለስትሮል በደም ስር ውስጥ እየተከማቸ ሲመጣ የሚከሰት ነው።

2.የደም ግፊት፡- የልብ ጡንቻ በመወፈር በሂደት የልብ ግራ ክፍል እንዲሰፋ በማድረግ ልባችን ተግባሩን እንዳያከናውን ያደርገዋል፡፡

3.የልብ በር ችግር
፡- ለአካላችን ደም ለማሰራጨት የሚረዳው የልብ በር ሲጎዳ ልብ ተግባሩን እንዳያከናውን ያደርጋል።

4.የልብ ጡንቻ ችግር፡- የልብ ጡንቻ በተለያዩ ኢንፌክሽኖች፤ አልኮል አብዝቶ በመጠጣትና የተለያዩ መድሀኒቶችን በመውሰድ ሊታመም ይችላል፡፡

5. በአፈጣጠር የልብ አካላት ትክክል ባለመሆኑ፡- የልብ አካላት አፈጣጠር ማለትም የልብ በር፣ የደም ቧንቧ፣ የጡንቻውና ሌሎችም

6. ሌሎች በሽታዎች እንደ የስኳር በሽታ፤ የታይሮይድን እጢ የሚያመርቱ ሆርሞኖች ብዛት፤

....
የልባችንን ጤና እንዴት እንጠብቅ?

ትምባሆ/ሲጋራ አለማጨስ
የአካል እንቅስቃሴ ማድረግ፤ በተለይ በፍጥነት መራመድ፤ ዋና፤ ሩጫና ሌሎችንም ማድረግ፡፡

ቁመታችንና ክብደታችን ካልተመጣጠነ በተገቢው መልኩ ለማመጣጠን ክብደትን መቀነስ፤

አትክልትና ፍራፍሬን ማዘወተርን የምግብ ምርጫችን ማድረግ!
• የምንጠቀመውን የጨው መጠን መቀነስ፤ ጥሬ ስጋ፤ ጮማ፤ እንቁላልና ቅቤን በሚገባ መቀነስ፡፡

የደም ግፊትና ስኳር በሽታ ካለብን በመከታተል መቆጣጠር መቻል የልብ ድካምን ለመከላከል ዋናዎቹ ናቸው፡፡

እባክዎን ይህን ጠቃሚ መረጃ ለሁሉም እንዲደርስ ሼር በማድረግ ይተባበሩ!

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
1.3K viewsedited  21:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 23:51:54
የትግራይ ባለሥልጣናት ከ4 ሺህ በላይ የጦር ምርኮኞችን ዛሬ መልቀቃቸውን አስታወቁ!!

ዛሬ ተሸኙ የተባሉት 4 ሺሕ 208 የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት በተለያዩ ዓውደ ውጊያዎች የተማረኩ እና እስከ 11 ወራት ድረስ በመቐለ የጦር ምርኮኞች ማዕከል የቆዩ ናቸው ተብሏል። የተለየ ወንጀል መፈጸማቸው ከተረጋገጠባቸው እና ጉዳያቸው በሕግ ከሚታይ ውጪ ሌሎች በሺሕዎች የሚቆጠሩ የጦር ምርኮኞች በሒደት እንደሚለቀቁ የመቐለ የጦር ምርኮኞች ማዕከል አስተባባሪ አቶ ብርሀነ ከበደ ተናግረዋል።

የክልሉ መንግስት፣ ምርኮኞቹ ዛሬ በዓለም አቀፉ ቀይመስቀል ማሕበር ትብብር ከትግራይ ውጭ ይሸኛሉ ያለ ቢሆንም ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማኅበር የትግራይ አመራሮች ምርኮኞችን እንለቃለን ባሉት ኦፕሬሽን ላይ ቀይ መስቀል ምንም አይነት ተሳትፎ የለኝም ሲል ለቢቢሲ ገለጿል።

የኢትዮጵያ መንግስት በጉዳዩ ላይ ያለው ነገር የለም።

https://www.facebook.com/100075981277063/posts/157318083477567/?app=fbl

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
2.4K viewsedited  20:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 23:04:57
ጥንቃቄ!! ሼር ይደረግ!

ሮም የገበታ ጨው እና ሴንሆን የማር ምርቶች ከገበያ እየተሰበሰበ ነው!!

የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ሮም የገበታ ጨው እና ሴንሆን የማር ምርቶች ከገበያ እየሰበሰበ መሆኑን ገለጿል፡፡

በባለስልጣኑ ሮም የገበታ ጨው እና ሴንሆን ማር በሚል ስም የተገለፁት የምርት ውጤቶች ተገቢውን የጤና ብቃት ማረጋገጫ ሳያወጡ ምርቶችን ለገበያ በማቅረብ በመስራታቸውና የምርቶቹ ናሙና ተወስዶ በላብራቶሪ ሲመረመር መስፈርቱን የማያሟላና ለጤና ጉዳት የሚያመጣ ሆኖ በመገኘቱ ከገበያ እንዲሰበሰቡ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ምርቱን የሚያመርቱት የድርጅቱ ባለቤቶችም በምርቶቹ ላይ የተሰጣቸው የእርምጃ ውሳኔ ተገቢ መሆኑን አምነው በቀጣይ ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርት አሟልተው አዲስ ምርት አምርተው ወደ ገበያ እንደሚገቡ ከባለስልጣኑ ጋር መግባባት ላይ ደርሰዋል ተብሏል፡፡ ስለሆነም ህብረተሰቡ እነዚህን ምርቶች ለጊዜው ከመጠቀም እንዲቆጠብ ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳስቧል።

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
4.2K viewsedited  20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ