Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 132.13K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 283

2022-05-16 19:39:28
በርካታ የመኪና ግብይት አማራጭ ያሉትን ይህን ቻናል ይቀላቀሉ፣ ይጎብኙ፣ ይገበያዩ!

http://T.me/EthioCarMarket
10.5K views16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:36:05
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
10.3K views16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 18:47:59
በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኙ 26 ኢንዱስትሪዎች ከደረሰባቸው ውድመት አገግመው ወደ ሥራ ገቡ!!

የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ማስፋፊያና ፕሮሞሽን ባለሙያ ተስፋዬ ይመር በከተማው በክልል እና በፌዴራል ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሁም በባንኮችና በመሠረተ ልማት አቅራቢዎች ድጋፍ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል ብለዋል፡፡

ከእነዚህ መካከል 10 የሚሆኑት ኢንዱስትሪዎች ከክልል የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክክር ጉባኤ በኋላ ወደ ሥራ የገቡ መሆናቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

በአሁኑ ወቅት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ምርታቸውን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬን በጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ እንዲሁም በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች በዘጠኝ ወራት ውስጥ 19 ሚሊየን 806 ሺሕ 957 ከ80 ዶላር ማግኘት መቻሉን ባለሙያው ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥ በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ከኢንዱስትሪ መንደር ውጭ በምርት ላይ የሚገኙት አምስት የጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ ኢንዱስትሪዎች 8 ሚሊየን 698 ሺሕ 27 ከ54 የአሜሪካ ዶላር ማስገኘታቸውን ተናግረዋል።

በግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በምርት ላይ የሚገኙ አምስት ድርጅቶች 11 ሚሊየን 108 ሺሕ 930 ከ26 የአሜሪካ ዶላር አስገኝተዋልም ብለዋል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
11.4K viewsedited  15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:58:47
ዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ለማድረግ ሥምምነት ፈረመ

ዓለም ባንክ በኢትዮጵያ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር (300 ሚሊዮን ዶላር) ድጋፍ ለማድረግ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ሥምምነት ተፈራረሙ።

ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ከኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና የኤርትራ ዳይሬክተር ኦስማኔ ዶኔ ጋር ተፈራርመዋል።
የድጋፍ ሥምምነቱ በጦርነቱ በአማራ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በግጭት የተጎዱ አካባቢዎችና ማህበረሰብ ለመልሶ ግንባታና መልሶ ማቋቋም ሥራዎችን በአስቸኳይ ለመደግፍ ያለመ ነው መባሉን ኢዜአ ዘግቧል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
13.1K viewsedited  13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:55:32
1,040 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ተመለሱ!

በዛሬው ዕለት በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ 1 ሺሕ 40 ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ከተመላሾች ውስጥም 303 ሴቶች ሲሆኑ 90 የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጁላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉም ተጠቁሟል፡፡እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ሥራ ቁጥራቸው ከ23 ሺሕ 640 በላይ ኢትዮጵያዊያንን መመለስ እንደተቻለ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
12.8K viewsedited  13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 14:48:44
ለሰርግ ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ሀናን


ሃናን ትባላለች የ25 አመት ወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነች፣ ከእጮኛዋ ጋር ኒካ ለማሰር ስላሰቡ አዲስ አበባ በመምጣት ለሰርጋቸው የሚያስፈልጋቸው እቃዎች ለመግዛት በአንድ ሆቴል 8ኛ ፎቅ ማረፊያቸውን አደረጉ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ከታዲያስ አዲስ ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል።

በሆቴሉ እንዳሉ በመካከላቸው አለመግባባት ተፈጥሮ ይጨቃጨቃሉ እሱ ክፍሉን ጥሎ ወጣ ከቆይታ በኋላ የሆቴሉን ባልደረባ "እስቲ ሂድና ቼክ አድርጋት ቅድም ተበሳጭታ ነበር" ብሎ ይልከዋል፣ እሱም ሄዶ ሲመለከት ከ8ኛ ፎቅ ራሷን ወደ 3ኛ ፎቅ ወርውራ ህይወቷ እንዳለፈ ታውቋል ሲል ፖሊስ ተናግሯል።

ፖሊስም ምርመራውን መቀጠሉን ገልፇል::
#ነብስ_ይማር

T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
14.9K viewsedited  11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 14:24:29
ከ3 ሺሕ በላይ ጥይት ከነተጠርጣሪዎቹ በቀጥጥር ስር ዋለ!!

የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሔራዊ መረጃ ደኅንነት ባደረጉት ክትትል በአንድ የእንጨት ሥራ ድርጅት ውስጥ ተደብቆ የተቀመጠ ከ3 ሺሕ በላይ ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ሁለቱ ተቋማት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አዲሱ ገበያ ቀለበት መንገድ አካባቢ በሚገኝ አንድ የእንጨት ስራ ድርጅት ውስጥ ተደብቆ የተቀመጠ ጥይት ስለመኖሩ ከሕዝብ የደረሳቸውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ሲከታተሉ ቆይተው ግንቦት 8 ቀን 2014 ዓ.ም በህግ አግባብ በድርጅቱ ውስጥ ባደረጉት ብርበራ በ4 ማዳበሪያ ተጠቅልሎ በድብቅ የተቀመጠ 1 ሺሕ 98 የብሬን እና 2 ሺሕ 162 የክላሽ ጥይት ተይዟል፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 2 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝም ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ኅብረተሰቡ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ሊያስከትል የሚችለውን ሀገራዊ ጉዳት ተገንዝቦ የዚህ ህገ ወጥ ተግባር ተሳታፊዎች በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ እየሰጠ ያለውን ጥቆማ እና መረጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
14.1K viewsedited  11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 14:05:10 "ከጦር መሳሪያ ምዝገባው በኋላ የተደራጀ ስልጠና ይሰጣል" - የአማራ ክልል

አማራን ሕዝብ ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ የተደራጀ ሥልጠና ሊሰጥ መሆኑ ተገልጿል!!

የጥፋት ሀይሉን ዓላማ ለማክሸፍ ከመንግሥት የጸጥታ ኀይል በተጨማሪ ማንኛውም የጦር መሳሪያ ያለው ምዝገባ ካካሔደ በኋላ የተደራጀ ሥልጠና እንዲወስድም ይደረጋል ብለዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
13.1K viewsedited  11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 13:58:18
የአማራ ክልል ዜጎች የጦር መሳሪያ እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቀረበ!!

ከግንቦት 9/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት የጦር መሳሪያ ምዝገባ እንደሚካሄድ የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታውቋል።

ከዚህ በፊት ያልተመዘገበ ማንኛውም የጦር መሳሪያ የታጠቀ ግለሰብ በአካባቢው በሚገኙ የምዝገባ ማዕከላት በመገኘት እንዲያስመዘግብ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አሳስቧል።

የቢሮው ኃላፊ ደሳለኝ ጣሰው፤ የጦር መሳሪያ ምዝገባው የአማራን ሕዝብ ደኅንነት ለማስጠበቅ አጋዥ ኃይል ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል፡፡

አሸባሪው ትሕነግ የጥፋት መንገድ ተጋሪዎች የአማራን ሕዝብ አንድነት ለመሸርሸር በብሔርና በሃይማኖት ሽፋን የተለያዩ አጀንዳዎችን እየዘረጉ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው የሽብር ቡድኑ አሁንም ወደ ዳግም ጦርነት ለመግባት ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ በተጨባጭ እያሳየ ነው ብለዋል። የጥፋት ኃይሉን ዓላማ ለማክሸፍ ከመንግሥት የጸጥታ ኃይል በተጨማሪ ማንኛውም የጦር መሳሪያ ያለው ምዝገባ ካካሔደ በኋላ የተደራጀ ሥልጠና እንዲወስድም ይደረጋል ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
13.8K viewsedited  10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 11:21:47
የሰብአዊ እርዳታ የጫኑ ተጨማሪ 85 ተሽከርካሪዎች መቀሌ መድረሳቸው ተገለጸ!!

የዓለም ምግብ ፕሮግራም 85 የሰብአዊ አርዳታ የጫኑ ተስከርካሪዎች ትላንት መቀሌ መድረሳቸውንና ተጨማሪ 130 የሰብአዊ እርዳታ የጫኑ ተስከርካሪዎች ወደ ትግራይ እየተጓዙ መሆናቸውን አስታወቀ፡፡

ወደ ትግራይ ክልል የሚላከው የሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለጸው የዓለም ምግብ ፕሮግራም የሰብአዊ እርዳታ የጫኑ ከባባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይና አፋር ክልል እየገቡ መሆናቸውንና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አካላት የማዳረስ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አመልክቷል፡፡

ወደ አፋር እየተጓጓዘ የሚገኘው እርዳታ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን በቀጣዮቹ ቀናትም እስከ 36 ሺሕ ለሚደርሱ ሰዎች ድጋፉን ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑ ተነግሯል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
15.1K viewsedited  08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ