Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.93K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 288

2022-05-14 21:22:46
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት እና ለሳሊኒ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ የክብር ዶክትሬት ሰጠ!!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አዴሲና እና ለጣሊያኑ ሳሊኒ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ፔትሮ ሳሊኒ የክብር ዶክትሬት ሰጠ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደው መርሃ ግብር ለተሸላሚቹ የክብር ዶክትሬቱን አበርክተዋል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት ዶክተር አኪንውሚ አዴሲና በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ በልማትና ሌሎችም ተግባራት የላቀ ሚና የተወጡ ናቸው ተብሏል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ 8ኛው ፕሬዚዳንት በመሆን እየመሩ ያሉት አዴሲና በአህጉሪቷ የድህነት ቅናሳ፣ የትምህርት መስፋፋት፣ የስራ ፈጠራ እና ሌሎችም ተግባራት ላይ ውጤታማ ስራ ማከናወናቸው ይታወቃል።

በመሆኑም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለእኒህ ታላቅ ባለውለታ የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል።

የጣሊያኑ ሳሊኒ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ፔትሮ ሳሊኒ፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲቪል ስራዎች ግንባታ ስኬታማነት ኃላፊነታቸውን በብቃት የተወጡ ናቸው። ኢዜአ እንደዘገበዉ በግድቡ ግንባታ ስኬት የላቀ ሚና ለነበራቸው ለእኒህ ታላቅ ባለውለታ ዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬት ሰጥቷቸዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
8.4K viewsedited  18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 21:22:46
7.6K views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 20:24:32
በርካታ የመኪና ግብይት አማራጭ ያሉትን ይህን ቻናል ይቀላቀሉ፣ ይጎብኙ፣ ይገበያዩ!

http://T.me/EthioCarMarket
2.3K views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 20:24:13
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
2.3K views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 19:51:57
አሸባሪው ህወሓት በአማራ ክልል በወረራ በቆየባቸው ጊዜያት ከ288 ቢሊዮን ብር በላይ ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል

አሸባሪው ህወሓት በአማራ ክልል ወረራ በፈጸመበት ወቅት 288 ቢሊዮን 16 ሚሊየን 448 ሺህ 452 ብር ግምት ያለው ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱን ጥናት አመለከተ።

ቡድኑ በወረራ በቆየባቸው ጊዜያት ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱ ጥናቱ በዝርዝር አመላክቷል።

አሸባሪ ቡድኑ በአማራ ክልል በወረራ በቆየባቸው አካባቢዎች ያደረሰው ጉዳት በተመለከተ ጥናት ሲያደርግ የነበረው ቡድን የጥናቱን ጥቅል ውጤት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

አምስት ወራት በፈጀው በዚህ የጉዳት መጠን ጥናት ውስጥ በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የክልሉ መንግስትና የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ተሳትፈዋል።

በጥናቱ አሸባሪው ህወሃት ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን በዚህም የንጹሃንን ህይወት ማጥፋትን ጨምሮ የተለያየ ደረጃ ያላቸው የሰብዓዊ ጉዳት ማድረሱን ጥናቱ አሳይቷል።

የአሸባሪው ቡድን ታጣቂዎች 1 ሺህ 782 የአስገድዶ መድፈር ጥቃት መፈጸማቸውን የገለጸው የጥናቱ ውጤት፤ በቡድን በመሆን በቤተሰብ አባላት ፊት አስገድዶ የመድፈር ድርጊት በመፈጸም አሰቃቂ ጉዳት ማድረሳቸው ተገልጿል።

ቡድኑ በወረራ በቆየባቸው አካባቢዎች 6 ሺህ 985 የሚሆኑ ንጹሃን ዜጎችን በጦርነቱ ምንም አይነት ተሳትፎ ሳይኖራቸው በጅምላና በተናጥል እንደረሸናቸው ጥናቱ ማረጋገጡን የቡድኑ አባላት ተናግረዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
4.8K viewsedited  16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 14:07:11
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ህገ-ወጥ ሰነድ አዘጋጅተው አሰራጭተዋል ብሎ የተጠረጠራቸውን የፓርቲውን ምክትል ሊቀመንበር ጨምሮ 4 አባላቱን አገደ፡፡

በፓርቲው የሥራ ኃላፊዎችና በአባላቱ ላይ እግድ የጣለው የኢዜማ ብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ነው፡፡ግለሰቦቹ የሳምንት ሥራ መከታተያ ቅፅ በሚል ህገ-ወጥ ሰነድ አዘጋጅተው ግንቦት 2፣ 2014 በብሔራዊ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የዋትስ አፕ ግሩፕ ላይ በመላክ ተጠናክረው መታገዳቸው ሸገር ከፓርቲው ያገኘው መረጃ ያሳያል፡፡የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴውም ከትናንት በስትያ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በጉዳዩ ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

ሰነዱ ፍፁም ስህተት እና የፓርቲው አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ሂደት ዲሞክራሲያዊነትን የሚያቀጭጭ ብሎታል በውሳኔው፡፡በመሆኑም ሰነዱን አዘጋጅተዋል ተብለው የተጠረጠሩት 4 የፓርቲው አባላት በሰነዱ ላይ ያላቸውን ተሳትፎና የህግ ጥሰታቸው ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት ለፓርቲው ህገ ደንብ ትርጉምና ዲሲፕሊን ኮሚቴ ተመርቷል ተብሏል፡፡

ጉዳዩ በኮሚቴው ተመርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥበት ድረስም ፡-

• የኢዜማ የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ሀላፊው አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ
• የፋይናንስ መምሪያ ሀላፊው አቶ አንድነት ሽፈራሁ
• የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ጫኔ ከበደና
• አባል የሆኑት አቶ ኢዮብ መሳፍንት ከሀላፊነታቸው ለጊዜው እንዲታገዱ መወሰኑን ሸገር ራዲዮ ዘግቧል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
4.4K viewsedited  11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 10:20:28
ሕወሓት ሰላማዊ ዜጎችን እያሰረ መሆኑ ተገለጸ

አሸባሪው ሕወሓት አስገድዶ ወደ ግዳጅ ያስገባቸው ምልምሎች መካከል ለመሸሽ የሞከሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እያሰረ መሆኑን ዘመዶቻቸው የታሰሩባቸው ሦስት ሴቶች ገለፁ።

አሸባሪው ሕወሓት ከፍተኛ የፖለቲካ እና ወታደራዊ መሪዎችን ያሳተፈ ቅስቀሳ በማድረግ ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑን የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ ናቸው፡፡

ሱዳንስ ፖስት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሦስት የትግራይ ተወላጆች በኢሜይል መልዕክት አድርሰውኛል ብሎ እንደዘገበው ሕወሓት የሚያደርገው ጦርነት ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጋር ብቻ ሳይሆን የክልሉን ሰላማዊ ዜጎች በማሰር ትርጉም የለሽ ተግባር እየከወነ ነው፡፡

በመቶዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች እና ሰላማዊ ዜጎች የሕወሓትን የሽብር ተግባር ለመቀላቀል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሲታሰሩ ይህ የመጀመሪያ አይደለም ያሉት ነዋሪዎቹ ዓለም ዐቀፉ ማኅበረሰብ ሕወሓት ጦርነት እንዳይቀጥልና ሰላምን እንዲቀበል ጫና ማድረግ እንደሚጠበቅበት ጠይቀዋል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
4.4K viewsedited  07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 10:10:50
የ100 ብር ቅናሽ!!

ለአዳዲስ ደንበኞቻችን በመጀመሪያው የቢዩ ትዕዛዛቸው ላይ የ100 ብር ቅናሽ አድርገናል። Promo code 'beu100'ን በመጠቀም ትዕዛዝዎን በbeU delivery መተግበሪያ ይዘዙ።

100 ብር ቅናሽ ለማግኘት ትህዛዙ ከ200 ብር በላይ መሆን ይጠበቅበታል!

አሁኑኑ ይዘዙ!!!
http://onelink.to/beudelivery16
ወይም ወደ 9533 ይደውሉ

ይከተሉን:
Facebook, Instagram, Twitter
1.3K views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 10:04:43
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
4.6K views07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:54:13
ትሕነግ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ በመሆኑ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ እንዲሆን የአማራ ክልል መንግሥት አሳሰበ!!

ወራሪው የትሕነግ ቡድን በየቀኑ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ እና የትግራይን ሕዝብ ለጦርነት እያነሳሳ መሆኑን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የጸጥታ ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በዝርዝር የገመገመ ሲሆን የአሸባሪው ትሕነግን አደገኛ ቅዠት መመከትና መቀልበስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይቷል፡፡ ምክር ቤቱ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ መሆን እንዳለበትም አቅጣጫ ያስቀመጠም ሲሆን በጉዳዩ ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡

በአንድ በኩል ከፌደራል የጸጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት ከወያኔ የሚሰነዘርብንን ጥቃት ለመከላከል በተጠንቀቅና በዝግጁነት መቆም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በውስጣችን ለወያኔ ሴራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩትን ህገ-ወጦችንና ስርዓት አልበኞችን በመቆጣጠር የክልላችን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ግንባር ቀደም የትኩረት አቅጣጫ እንዲሆኑ የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት ወስኗል።

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል አንደሚከተለው ቀርቧል፡-
https://telegra.ph/የአማራ-ክልል-ሙሉ-መግለጫ-05-13

T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
6.7K viewsedited  18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ