Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.93K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 287

2022-05-15 18:29:03
የቻይናው ባሉን የዓለም በከፍታ የመብረር ክብረ ወሰንን ሰበረ!!

የቻይናው ተንሳፋፊ ባሉን ከምድር 9 ሺህ 32 ሜትር ከፍታ ላይ መንሳፈፍ በመቻሉ ነው የዓለም የከፍታ ክብረ ወሰንን የሰበረው።

በጉዙፍነቱ ምክንያት “ተንሳፋፊው መርከብ” ተብሎ የሚጠራው እና‹‹ጂሙ ቁጥር 1›› በሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ባሉን 2.625 ቶን የሚመዝን ሲሆን ሂሊየም በተሰኘ ጋዝ ተሞልቶ በአየር ላይ በሰከንድ 30 ሜትር የሚቀዝፍ እንደሆነ ተነግሯል።

ከ8 ሺህ 840 ሜትር በላይ ከሚረዝመው እና በቻይና እና በኔፓል ድንበር አካባቢ ከሚገኘው ኮሞላግማ ተራራ ጫፍ ከሚገኘው የምርምር ጣቢያ የተለቀቀው ባሉኑ ከ9 ሺህ ሜትር በላይ በመንሳፈፍ ነው ክብረ ወሰኑን ለመስበር የቻለው።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
13.3K viewsedited  15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 14:35:26
ዛሬ ምሽት ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ይታያል!!

በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች ዛሬ ምሽት እና ነገ ማለዳ ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ እንደሚታይ ቢቢሲ ዘግቧል።

ከግርዶሹ ደቂቃዎች በፊት ጨረቃ ብርቱካናማ ቀይ መልክ ይዛ ወይንም “ደም ለብሳ” የምትታይ ሲሆን ክስተቱ ከፕላኔታችን አስደናቂ እይታዎች አንዱ የሆነው የጨረቃ ግርዶሽ በሰማይ ላይ ይሆናልም ተብሏል።

ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ የሚፈጠረው ምድር በፀሐይ እና በጨረቃ መካከል በምትሆንበት ጊዜ የሚከሰት ነው።

ክስተቱ በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገራት ሰኞ ማለዳ እንደሚታይ የሚጠበቅ ሲሆን በአሜሪካ ደግሞ በአንፃሩ ዛሬ እሁድ ምሽት ላይ ያያሉ ነው የተባለው።

ጨረቃ ከምህዋሯ በጣም ቅርብ በሆነ ቦታ ላይ እንደምትሆንና ከወትሮው በበለጠ ተልቃና ገዝፋ እንደምትታይም ይጠበቃል ተብሏል። በመሆኑም ማንኛውም ሰው የጨረቃ ግርዶሹን ክስተት በዓይን ማየት የሚችል ሲሆን አቅርቦ ማሳያ (ባይኔኩላር) ወይም አነስተኛ ቴሌስኮፕ በመጠቀምም የሚፈጠረውን የቀይ ቀለም የበለጠ ለማየት ይችላል ነው የተባለው።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
752 viewsedited  11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:42:03
በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይጀመር ኢሰመኮ አሳሰበ!!

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን “በፌደራል መንግስት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል” ዳግም እየተካረረ የመጣው የጦርነት ስጋት እንዳሳሰበው ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ተቋሙ በመግለጫው እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይጀመር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አሳስቧል። ከ19 ወራት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በርካቶች ለተለያዩ አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደተጋለጡ ያወሳው ኢሰመኮ አሁንም ዳግም ወደ ጦርነት ለመግባት እያደገ የመጣው መካረር ሊቆም እንደሚገባ ገልጿል።

ጦርነቱ በአፋር፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ለከፋ እንግልት እንዲዳረጉ፣ የሚወዷቸውን ሰዎች እንዲያጡ፣ ህይወታቸውን በእርዳታ ላይ እንዲመሰረቱ፣ መሰረታዊ የዜጎች አገልግሎቶችን እንዲነፈጉ እና የሌሎችን ጉዳቶችን እያስተናገዱ እንደሚገኙም ተቋሙ ከዚህ በፊት ባደረኳቸው ተደጋጋሚ ምርመራዎች አረጋግጫለሁ ብሏል።

የፌደራል መንግስትን ጨምሮ የሰሜን ኢትዮጵያ ሶስቱ ክልሎች ዋነኛ ትኩረት ሊሆን የሚገባው በጦርነቱ ለተጎዱ ዜጎች ያለምንም ገደብ የሰብዓዊ መብት ድጋፎች እንዲደርሱ ማድረግ እንደነበርም ኢሰመኮ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። እንዲሁም በጦርነቱ ምክንያት የምርት እጥረቶች እና የዋጋ መናር ተከስቶ ዜጎች በአስከፊ ሁኔታ ህይወታቸውን እንዲገፉ ተገደዋል ያለው ኢሰመኮ ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ መፈለግ ይገባል ብሏል።

በመሆኑም በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ወይም ኢጋድ አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ የበኩላቸውን እንዲወጡ ኢሰመኮ አሳስቧል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
5.8K viewsedited  09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 11:34:28
Welcome to Invicta Report. Home of Political Incorrectness.

The latest news, war coverage, economy, culture, science and what the Mainstream Media doesn't want you to know. News you don't get anywhere else.

Channel: t.me/InvictaReport
Chat: t.me/InvictaGroup 
7.0K views08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 11:19:26
የገርጂ ዘመናዊ መኖሪያ መንደር በተለያዩ አካላት ተጎበኘ!!

በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው እና የአልሙኒየም ፎርምወርክ የግንባታ ቴክኖሎጂ ውጤት የሆነው የገርጂ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደርን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጣሰው ወልደሃና (ፕ/ር) እና ባለሀብቱ ነጅብ አባቢያ ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም ኮርፖሬሽኑ በግንባታ ቴክኖሎጂ እና አስተዳደር እያሳየ ባለው የላቀ አፈጻጸም የመኖሪያ መንደሩን በ18 ወራት ግንባታውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ መቃረቡ ተገልጿል።

ይህም በሀገሪቱ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ተስፋ ሰጪ መሆኑ ተነግሯል፡፡

በዚህ ፕሮጀክት ጥራትን፣ ቅልጥፍና እንዲሁም ዘመናዊነትን አጣምሮ እጅግ ዘመናዊ መኖሪያ መንደር በአጭር ጊዜ መገንባት መቻሉ ኮርፖሬሽኑ ብቃት ባላቸው እና የፕሮጀክት አስተዳደር እውቀት ባካበቱ አመራሮች እየተመራ መሆኑን ማሳያ መሆኑን የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
7.3K viewsedited  08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 11:00:59
በደንዲ ሃይቅ ላይ ዘመናዊ የኢኮ-ቱሪዝም ሎጅ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል በሆነው የደንዲ ሃይቅ ላይ ዘመናዊ ኢኮ-ቱሪዝም ሎጅ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ከአዲስ አበባ 127 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው ደንዲ ሃይቅ ዘመናዊ የኢኮ-ቱሪዝም ሎጅ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጣልያኑ "ዊ ቢውልድ" ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፔትሮ ሳሊኒ የመሰረት ድንጋዩን አስቀምጠዋል።

በመርኃ ግብሩ ላይ የወንጪ ደንዲ ኢኮ-ቱሪዝም ፕሮጀክት አስተባባሪና የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች መገኘታቸውን አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
7.0K viewsedited  08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:58:58
#ArtLand_gifts Best Gifts


የወደዱትን "ፎቶ ወይም ምስል" እንጨት(MDF), postcard እና ቆዳ(ሌዘር) ላይ እንሰራለን

"እማይረሱ ስጦታዎችን ለሚወዷቸው"

contact us: 0931465618
For Order @Artlandgifts

ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ደንበኞቻችን በፖስታ ቤት እንልካለን

Join our telegram channel
@artlandengraving
@artlandengraving
6.3K viewsedited  07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:58:40
#አምራቾች_ነን
የተለያየ ዲዛይን ያላቸው #ኮፊ_ቴብሎች እና እጅግ ውብ የሆኑ #የቡና_ረከቦቶች በጅምላም በችርቻሮም ማቅረብ ጀምረናል

ስራዎቻችንን ለማየት የቴሌግራም ቻናላችንን ሊንክ ይጫኑ
https://t.me/webnewood

#ለተረካቢዎች በሚፈልጉት ብዛት በአጭር ቀጠሮ እናስረክባለን
0983915600 ይደውሉ
#በተጨማሪም ሙሉ የእንጨት ስራዎችን በጥራት እንሰራለን
የእንጨት በሮች
ኪችን ካቢኔት
አልጋዎች
የግድግዳ ቁምሳጥኖች እና ሌሎች
6.3K views07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:16:29
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
334 views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 23:35:19
የተለያዩ ኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!!

ባሳለፍነው ሳምንት 131 ሚሊየን 481 ሺሕ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የገቢና የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል 40 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች እና 90 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች መያዛቸውን ነው የገለጸው፡፡

የገቢ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር ረገድ ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዙት ሞያሌ፣ ድሬዳዋ፣ ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ሲሆን በቅደም ተከተላቸው 14 ነጥብ 7 ሚሊየን፣ 9 ነጥብ 7 ሚሊየን እና 5 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ መቻላቸው ተገልጿል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌዴራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ኅብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ ነው የተያዙት፡፡

የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 15 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።

ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድኃኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች እንደሚገኙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ሥራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ የክልልና የፌዴራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ሕዝብ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
2.3K viewsedited  20:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ