Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.93K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 282

2022-05-20 22:30:57
የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ም/ቤት ከከተማው ወቅታዊ ሁኔታ ተከትሎ የከተማውን ጸጥታና ሰላም ለማስከበር የተሰጠ መግለጫ

1.የትኛውም ተሽከርካሪ ከተፈቀደለትና ስምሪት ከተሰጠው ውጭ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ ንጋቱ 11:30 መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

2. ማንኛውም ግለሰብ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በኋላና ከንጋቱ 11:30 በፊት ከተፈቀደለት አካል ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

3.ማንኛውም የጦር መሳሪያ ስምሪት ከተፈቀደለት የጸጥታ አካል ውጭ ማንኛውም ግለሰብ የጦር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

4.የጸጥታ መዋቅሩ በሚያከናውኗቸው ህግን የማስከበር ስራዎች ተባባሪ የማይሆን ለማደናቀፍ የሚሞክር ማንኛውም ግለሰብ አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።

5.ከከተማ አስተዳደሩ የጸጥታ አካላት ውጭ የመንግስትም ሆነ የግል ታጣቂዎች በከተማዋ የጦር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

6.መጠጥ ቤቶች፣ግሮ ሰሪዎች የትኛውም የመዝናኛ ድርጅት ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት መስጠት የተከለከለ ነው።ሲሰጥ የተገኘ ድርጅት አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑ።

7.በከተማችን በ4ቱ ቀበሌ በህገወጥ የመሬት ወረራ የተሳተፉ እስከ 12/09/2014 ዓ/ም ድረስ እራሳችሁ አፍርሳችሁ እንድትቆዩ።የማያፈርስ ካለ ህጋዊ እርምጃ በጸጥታ መዋቅሩ የሚወሰድበት መሆኑ።

8.የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ሃሰተኛ መረጃ ማሰራጨት፣የግለሰቦችን ሰብዕና የሚያጎድፍ እንዲሁም ውድ ሂወቱ እየገበረ ላለው የጸጥታ መዋቅሩን ስም ማጠልሸት የተከለከለ ነው።

9.ከተማ አስተዳደሩ የህገወጥ ንግድን ለማስቆም እያደረገ ባለው ተግባር እንቅስቃሴ ውን ለመግታት ያልተገባ እቅስቃሴ ማድረግ የተከለከለ ነው።

10.ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

ኢትዮመረጃ - ሼር
5.8K viewsedited  19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 21:57:14
የአዲስ አበባ ት/ት ቢሮ የ2014 ዓ.ም የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የትምህርት ካላንደርን አሻሽሏል።

የ2014 ዓ.ም የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የትምህርት ከላንደርን ማሻሻልን በተመለከተ!

1. የ8ኛ ክፍል ከተማቀፍ ፈተና ከሰኔ 27-29/2014 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።

2. የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ከሰኔ 20-23/ 2014 ዓ.ም ድረስ ይሆናል።

3. የትምህርት ቤት የመዝጊያ ስነ-ስርዓት እና ውጤት ማስረጃ የሚሰጥበት ቀን ሐምሌ 5 ቀን 2014 ዓ.ም ይሆናል፡፡

ምንጭ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ት/ት ቢሮ
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
7.8K viewsedited  18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:56:27
"ከሰሞኑ በአማራ ክልል በህገወጥ የጦር መሳሪያና ገንዘብ ዝውውር፤ በቡድን ተደራጅቶ ግለሰቦች ያፈሩትን ሃብትና ንብረት በመዝረፍና በማውደም ላይ የተሰማሩ፤ በነፍስ ግድያ የሚጠረጠሩ፣ አንዱን ህዝብ ከሌላው ጋር በማጋጨት ክልሉ እንዳይረጋጋ በሚያደርጉ ቡድኖች ላይ መጠነ ሰፊ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል፡፡ " - መንግስት

መንግስት፣ በሁሉም ክልሎች እየተካሄደ በሚገኘው ኦፕሬሽን በርካታ ግለሰቦችና ቡድኖች ከነ ትጥቆቻቸዉ፤ ከዘረፉት ንብረትና ቀጣይ ሊፈፅሙ ያቀዷቸዉ ጥፋቶችን ካሰፈሩባቸው ሰነዶች ጋር በቁጥጥር ስር እንዲዉሉ እየተደረገ ነው። ጉዳያቸውም ተገቢውን ሂደት ጠብቆ እየተጣራ ለፍርድ እንዲቀርቡ እየተደረገ ይገኛል ብሏል፡፡

መንግስት ፣ በፋኖ ስም የሚነግዱ የዝርፊያ ቡድኖች በህዝባችን ላይ ከፍተኛ ክህደት የፈፀሙ ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች እና የተላላኪዎቻቸው ዓላማ ማስፈፀሚያ መሆናቸው ነው ያለ ሲሆን መላው ህዝባችን ይህንን እኩይ ሴራ በመገንዘብ መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በመደገፍ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ይጠይቃል ብሏል።

የሚዲያና የጋዜጠኝነት ካባ ደርበው ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወሰደውን የማያዳግም እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል፡፡(የመንግስት ኮሙኒኬሽን)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
10.4K viewsedited  17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:42:45 መንግሥት የሀገርን ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ መፍትሔው የህግ የበላይነትን ማስከበር ነው አለ!!

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ከሰሞኑ አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ውስጥ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ኃይሎች እየወሰዱት ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ ህገወጥነትና የሰላም መደፍረስ እንዲሁም ስርዓት አልበኝነትን ለመቆጣጠር መሆኑን አስታውቋል፡፡

በኦሮሚያና በአጎራባች ክልሎች የሸኔ የሽብር ቡድን ከሌሎች የጥፋት ኃይሎች ጋር በመተባበር ህዝባችን ላይ እያደረሰ የነበረውን ጥቃት ለመቀልበስ መንግስት የተሳካ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች በአልሸባብ የሽብር ኃይል ላይ እየተወሰደ የሚገኘውም እርምጃ ውጤታማ በሆነ መንገድ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብሏል፡፡

ከሰሞኑ ደግሞ በአማራ ክልል በህገወጥ የጦር መሳሪያና ገንዘብ ዝውውር፤ በቡድን ተደራጅቶ ግለሰቦች ያፈሩትን ሃብትና ንብረት በመዝረፍና በማውደም ላይ የተሰማሩ፤ በነፍስ ግድያ የሚጠረጠሩ፣ አንዱን ህዝብ ከሌላው ጋር በማጋጨት ክልሉ እንዳይረጋጋ በሚያደርጉ ቡድኖች ላይ መጠነ ሰፊ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል፡፡

በአዲስ አበባና በዙሪያው ኦሮሚያ ከተሞች በቡድን ተደራጅተው በልዩ ልዩ የዝርፊያ ወንጀሎች ላይ የተሰማሩ፣ የጦር መሳሪያና የገንዘብ ዝውውር አቀባባይ በሆኑ ቡድኖችና ግለሰቦች፤ እንዲሁም በወያኔ ሰርጎ ገቦች ላይም መንግስት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል ብሏል፡፡

በሁሉም ክልሎች እየተካሄደ በሚገኘው ኦፕሬሽን በርካታ ግለሰቦችና ቡድኖች ከነ ትጥቆቻቸዉ፤ ከዘረፉት ንብረትና ቀጣይ ሊፈፅሙ ያቀዷቸዉ ጥፋቶችን ካሰፈሩባቸው ሰነዶች ጋር በቁጥጥር ስር እንዲዉሉ እየተደረገ ነው። ጉዳያቸውም ተገቢውን ሂደት ጠብቆ እየተጣራ ለፍርድ እንዲቀርቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡

በተለይም በፋኖ ስም የሚነግዱ የዝርፊያ ቡድኖች በህዝባችን ላይ ከፍተኛ ክህደት የፈፀሙ ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች እና የተላላኪዎቻቸው ዓላማ ማስፈፀሚያ መሆናቸው ነው ብሏል፡፡

መላው ህዝባችን ይህንን እኩይ ሴራ በመገንዘብ መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በመደገፍ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ መንግስት ይጠይቃል፡፡

መንግስት በበኩሉ በህገወጥ ተግባር ላይ በመሳተፍ፤ ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር ሆነ ብለው፤ አቅደዉ በሚሰሩ አካላትና ግለሰቦች እንዲሁም የሚዲያና የጋዜጠኝነት ካባ ደርበው ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወሰደውን የማያዳግም እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
10.2K viewsedited  17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:42:37
9.1K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:11:17
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+P7ctetopPExiY2Rk
10.1K views17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:02:55
Double A፣ ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር ተመልሷል

የ“Double A QR Ethiopia” የሞባይል መተግበርያን በስልክዎ  በመጫን በትክክለኛው የ Double A  ወረቀት ካርቶን ላይ የሚገኘውን የ  QR ኮድ የሞባይል መተግበሪያውን ተጠቅመው ስካን በማድረግ ፡-
 የተለያዩ ስጦታዎችን ለምሳሌ፦ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣የውሃ ማጣሪያ፣ ማይክሮዌቭ/የምግብ ማሞቂያ ማሽን፣ የጁስ መፍጫ እና የመሳሰሉትን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ይሸለሙ::

የ QR ነጥብ መሰብሰቢያ ፕሮግራማችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ! ደጋግመው QR ስካን ሲያርጉ ፤ ተጨማሪ ሽልማቶችን ያገኛሉ፡፡

መተግበርያውን ለማውረድ እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ።

Link: https://bit.ly/3KGYCxC  Or

https://da-cloud.advanceagro.net/index.php/s/WYovIsmE4u2Kz6y

ለተጨማሪ መረጃ: https://DoubleArewards.com/Ethiopia
10.6K views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 17:52:53
ፍርድ ቤቱ በብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ ላይ የ10 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ::

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀድሞው የክልሉ ልዩ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄ/ል ተፈራ ማሞ ላይ የ10 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።

ዛሬ ጠዋት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብለው የነበሩት ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ዛሬ ከሰዓት መልስ መቅረባቸውን ጠበቃቸው አቶ ሸጋው አለበል ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል። ህገ መንገስቱን በኃይል በመናድ ወንጀል በሚል ፍርድ ቤት መቅረባቸውንም ነው ጠበቃው ተናግረዋል፡፡

ፖሊስ ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ለ14 ቀናት ታስረው እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱን የጠየቀ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ 10 ቀን ብቻ በመፍቀድ ለግንቦት 22 ቀን 2014 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱንም አቶ ሸጋው ተናግረዋል። የቀድሞው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄ/ል ተፈራ ማሞ ባሳለፍነው ሰኞ በአዲስ አበባ ባልታወቁ ሰዎች መታፈናቸው መገለጹ ይታወሳል።

ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ የፌደራል መንግስት ከህወሃት ጋር ባደረገው ጦርነት በፌደራል መንግስት ጦር እዝ ስር በመሆን ውጊያ ሲመሩ፣ ሲዋጉና ሲያዋጉ መቆየታቸው አይዘነጋም።

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.3K viewsedited  14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 17:41:59
"በአማራ ሕዝብ ላይ እየተደረገ ያለው መንግስታዊ አፈና በእጅጉ የጠበቅነውን የአገራዊ ምክክር የትብብር ቀና እርሾዎችን እየደፋ ነው። በዚህ መንገድ ግን መቼውንም ስለጋራ ነገ ማሰብ ከባድ ይሆናል። አዝናለሁ!"

-የእንደራሴዎች ም/ቤት አባል የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ታደለ-
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
12.2K viewsedited  14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 17:11:30
ፊንላንድና ስዊድን ኔቶን ለመቀላቀል መወሰናቸውን ተከትሎ ሩሲያ የአፀፋ እርምጃ መውሰድ ጀመረች!!


የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር ሰርጊ ሾይጉ በሰጡት አስተያየት፤ ፊንላንድ እና ስዊድን የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን (ኔቶ) ለመቀላቀል መወሰናቸው በሩሲያ ድንበር አካባቢ ወታደራዊ ስጋቶች እንዲጨምሩ ያደርጋል ብለዋል። ይህንን ተከትሎም ሩሲያ አስፈላጊ የሆኑ የአፀፋ እርምጃዎችን መውሰድ እንደጀመረች መግለጻቸውን ኢንትራፋክስ የዜና ኤጀንሲ ዘግቧል።

በዚህም ሩሲያ በምእራብ ወታደራዊ ቀጠና ላይ ተጨማሪ 12 የጦር እዞችን በማቋቋም ምለሽ እንደምትስጥም ነው የመከላከያ ሚኒስትሩ ያስታወቁት። ፊንላንድ እና ሰዊድን ባለፍነው ረቡዕ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን (ኔቶ) ለመቀላቀል በይፋ ማመልከታቸው ይታወሳል።

ፊንላንድ እና ስዊድን ውሳኔ ተከትሎ በኋላም የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፒቲን በሰጡት አስታያት ሀገራቱ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ)ን ቢቀላቀሉም ለሀገራቸው ስጋት እንደማይሆን ገልጸዋል። ፑቲን ሁለቱ ሀገራት ድርጅቱን መቀላቀላቸው ለሩሲያ ስጋት ባይሆንም ምላሽ ሊያሰጥ እንደሚችል መናገራቸውም ይታወሳል። የፖለቲካ ሰዎች የስዊድን እና ፊንላንድ ኔቶን መቀላቀል አሁን በዩክሬን ያለውን ጦርነት ወደ ሌሎች ሀገራት ሊያዛምተው እንደሚችል እየተነበዩ ነው።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
12.7K viewsedited  14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ