Get Mystery Box with random crypto!

Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር C
የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር
የሰርጥ አድራሻ: @christian_mezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.45K
የሰርጥ መግለጫ

🗣እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብከዋለን!
ትክክለኛ የሆኑ የወንጌል አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረጉ፦
ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ምስክርነቶች፣ የሪቫይቫል ታሪኮች፣ ዝማሬዎች፣ መንፈሳዊ ዜናዎች፣ እንዲሁም መንፈሳዊነታቸውን የያዙ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ!
ለወዳጅ ጋደኞቻቹ #ሼር በማድረግ ይጋብዙ!
አስተያየት @ChristianMezmur_bot ላይ ፃፉልን✍
ሁሌም ከኛ ጋር ስለሆናቹ እናመሰግናለን!

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-11-27 19:48:01 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፮
@yanetmasra

ትምህርት ጀመርኩ ። ውዬ ብመጣም ተማርኩ ማለት ግን አልችልም እህቶቼ ትምህርት ቤት ስለሚሆኑና እናቴ ብቻዋን ስለምትሆን የእሷ ነገር ይበልጥ እያሳሰበኝ ለአይምሮዬ ፋታ ነሳኝ ። ዱላዋን ተደግፋ እቤት ውስጥ መዘዋወር ብትችልና አንዳንድ ነገሮችን ማድረግ ባያቅታትም  የፈለገችውን ሁሉ ማድረግ ግን ይቸግራታል ጎንበስ ብላ እቃ ማንሳት ፣ ብዙ መዘዋወር ፣ ረጅም ደቂቃ መቆም የማትችለው ነገር ነው ለዚህም አማራጩ መተኛት ነው የተባለ ይመስል ትተኛለች ፤ እሱ ደሞ ይበልኝ ያደቃታል ።

   ከትምህርት ቤት እንደተለቀቅኩ በፍጥነት ወደ ቤት ሄጄ እናቴን አያትና የሊስትሮ እቃዬን ይዤ እስኪመሽ ጫማዎችን እጠርጋለሁ ያገኘሗትን ሳንቲም ለቃቅሜ ወደ ቤት ይዤ እሄዳለሁ ያመጣሁት ብር ጥቂት ነገር ብትሸፍንም የአራት ሰው ፍላጎት ግን ማሟላት አትችልም ሌላው ቢቀር ለኔ ራሱ በቅጡ አይበቃኝም ሆኖም ግን እኔ የምኖረው እነበሱፈቃድ ጋር ስለሆነ የማገኛትን ነገር ለነሱ ከማዋል ውጪ ለራሴ አንድ ሳንቲም አላነሳም ፤ መኖሪያዬን ግን እናቴ ከታመመች በሗላ እነሱ ጋር ማድረግ ብፈልግም የታመመች ሰሞን እዛው ማደር ከጀመርኩ በሗላ ሻል ሲላትና መንቀሳቀስ ስትጀምር " ' ውሻ በቀደደው ጅብ ይገባል '  አሉ በል እዚህች ቤት የምትኖረው መጤ እምነትህን ስትተው ብቻ ነው አለዛ ግን እንዳታስበው ታማለች ፣ ምንም አታመጣም ብለህ እንደሆነ የማመጣውን አምጥቼ ጉድ ነው የማደርግህ ስለዚህ እዛው የለመድክበት ማደር ትችላለህ " አለቺኝ እውነት ለመናገር ቅስሜን ነው የሰበረችው በዛ ሰአት ስለሌላ ነገር ማሰብና መጣላታችንን ሁሉ ዘንግቼ የማስበው ስለእናቴ የጤና ሁኔታ እና መዳን ነበር በዛ ሰአት እንደዛ ስትለኝ ቂም ሁሉ ልቋጥርባት ምንም አልቀረኝ ነበር ።



" ምናለ ግትርነቷን ትታ እንደ እናትና ልጅ ብናወራ የመጣብንን መከራ ተባብረን ብንመካከርና ብንወጣው ጭራሽ በዚህ ሰአት ለምን ደካማ ጎኔን ነክታ ታቆስለኛለች " ብዬ ከልብ ተሰማኝ የዛች ቀን ተናድጄ ስለነበር እስከሚቀጥለው ቀን በማኩረፍ ሳላያት ቀረሁ በንጋታው ግን አላስቻለኝም ማደሩን ብትከለክለኝም ገባ ወጣ ማለቴን ግን አልተውኩም ምናልባት ግዴታ ስለሆነባት ነው መሠል ባታወራኝም እንኳን ጭራሹን እንዳልገባ አልከለከለችኝም  ። እኔም በነገሮች ተወጣጥሬ ከሌላው ጊዜ በተለየ ወደ እግዚአብሔር መጠጋት ቢገባኝም ጭራሹኑ ሳላስበው እራቅኩ የቅዳሜ የፀሎት ህብረት ፣ የቸርች አገልግሎት ላይ መሳተፍ ፣ እሁድ እሁድ የመደበኛ አገልግሎት ላይ መገኘት ቢያንስ ለሁለት ሳምንት እርግፍ አድርጌ ተውኩት ብዙ ጊዜ ከሚገርሙኝ ነገሮች አንዱ በጣም ስንደሰት እና ስንከፋ ወይም በህይወታችን ከባድ ፈተና ሲገጥመን ለምን እግዚአብሔርን እንደምንረሳው ነው  ደካማ ስለሆንን ችግራችን እንዳያጎብጠን  ቶሎ ብለን ልንደገፈው ሲገባ እርስት አድርገነው እኛው አዋቂ የመፍትሄ ባለቤት ሆነን እንገኛለን ብለን ብለን ሲያቅተን እናማርራለን ከሱ ከፍ ሲል ደሞ መጀመሪያ ማድረግ የነበረብንን ገሸሽ ያደረግነውን እግዚአብሔር ሄደን " ጌታ ሆይ አልቻልኩም መሞቴ ነው ስለኔ ግድ አይሰጥህም ወይ " ብለን እንጨቀጭቀዋለን  መፀለያችን ባይከፋም የመጨረሻ መፍትሄ ማድረጋችን ግን አግባብ አደለም እኔም በዛ ምክንያት በራሴ አፈርኩ  " አቤት ጌታ ሆይ ምን ትለኝ ይሆን ? እንዴትስ ትታዘኝ ይሆን ? " ብዬ በመጠየቅ እራሴኑ ታዘብኩት ከዛን በሗላ ግን ከልቤ እኔ ደካማ በመሆኔ ላደርግ የማልችለውን እሱ እንዲያረግልኝ ፣ እንዲደግፈኝ እና እንዲያበረታች ፀለይኩ ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
8.6K views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 19:00:19 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፭
@yanetmasra

በነጋታው ጠዋት የእናቴ አሰሪ የሆነችው ሴትዬ ከባለቤቷ ጋር በግ ይዘው ሊጠይቆት መጡ ። ይመስለኛል የተሠበረ ሰው እንዲጠገን የስጋ ተዋፅኦ የሆኑ ምግቦች መመገብ አለበት ከዛ ስለጤንነቷ ጠይቀው እንዲሻላት የልብ ምኞታቸውን ገልፀው በሌላ ጊዜ እንደሚጠይቋት ተናግረው ወጡ ። አንዳንድ ጎረቤቶቻችንም ከቤታችን አልጠፉም ፤ በጉ ከታረደ  በሗላ ከታረደ በሗላ ለቆንጣ ተዘልዝሎ መዘጋጀት ስለነበረበት ይህን ያደረጉት የበሱፈቃድ እናት ነበሩ ። ለእናቴ ምሳ ሰርተው እንድትበላ አቀረቡላት ፤ ምግብ ግን እስከዚም ሆና ስለነበር ለአመል ይህል ቀመስ ቀመስ አርጋ ብቻ ተወችው ገና ህመሟን በማስታመም ላይ ነበረች ። ህመም ለካ ሰውም  ያስጠላል እንዲሉ ለማናችንም ግድ አልነበራት ፤ ለነገሩ እውነቷን ነው የሰው ልጅ ጤና ከሌለው ምንስ ያስደስተዋል ? ዝም ብሎ የሚያዳምጠው ህመሙን ነው ።
   ከጥቂት ቀናት በሗላ ዱላ መጣላት እና በእሱ እቤት ውስጥ እንድትንቀሳቀስ ተደረገ ብዙ ጊዜ እኔ ነበርኩ እንድትንቀሳቀስ የማግዛት ታድያ በዚህ ምክንያት ከትምህርት ገበታዬ ብዙ ጊዜ መጓደል ጀመርኩ ይሄ ያሳሰባቸው የበሱፈቃድ ቤተሰቦች ብዙ ጊዜ ለትምህርት ትኩረት እንድሰጥ እና የ12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና ወሳጅ እንደሆንኩ አበክረው በመደጋገም ይነግሩኛል ግን ምን ላርግ ማን አጋዥ አለን ? ወይስ እኔ ልማር እናንተ ቅሩና እናታችንን ጠብቁ አልላቸው እህቶቼን በዛ ላይ የሰው ወከባ እየበረደ እየረገበ ጭራሹን ዝር የሚል ጠፋና ከደጅ ሆኗል " ደህና ዋልሽ ? ፣ በጎ ነሽ ?       ፣ እናትህ ተሻላት ? ፣ እግዚአብሔር ይማርሽ ። " የሚሉትን ቃላት ብቻ ሰንዘር ሰንዘር አድርገውልን የሚሄዱት



እግዚአብሔር በደህና ጊዜ የሰጠኝ እነ በሱፈቃድን ነው ።ቤተሰብ ሆነውናል ምንም እንኳን እናቴ እያገገመች ስትመጣ የነሱን መምጣት ባትፈልገውም ከጎዳቸው እያካፈሉ እኔና እህቶቼን የሚመግቡ እነሱ ናቸው ግን የነገሮች አካሄድ እየጣመኝ አልመጣም እናቴ እንደሆነች እደጅ ወጥታ መስራት እንደማትችል ግልፅ ነው ስለዚህ ያለኝ ምርጫ እነበሱፈቃድ ጋር መኖር ከጀመርኩ በሗላ ያቆምኩትን የጫማ መጥረግ ስራ ድጋሚ መስራት ነው ከትምህርት ስመለስ ባለኝ ጊዜ ይህን መስራት አለብኝ ይብቃም ይነስ የቤተሰቦቼን ቀዳዳ በጥቂቱም ቢሆን  ሊሸፍን ይችላል የሰው ፊት ማየት በጣም ከባድ ነገር ነው ። ልክ እንደ እሳት ይለበልባል ። ለነገሩ መስራቴን የውዴታ ግዴታ የሚያደርገው አልሰራም ብዬ ብቀመጥ ማን ይረዳናል ወይ ልመና ወይ ጎዳና ነው እጣችን እቴቴና ጋሼም ካላቸው ቁራሽ ላይ እየቆረሱ ለኛ መስጠት ለነሱ ከባድ እንደሚሆንባቸው አውቃለሁ ምንም እንኳን እነሱ ለመስጠት ባይሰስቱም

   እህቶቼ ቢያዝኑልኝምና ቢረዱኝም እንደኔ ግን ስቃይን እንዲያዩ አልፈልግም ሌላው ቢቀር ትምህርቴን አቁሜ ሌላ ስራም እየሰራሁ ቢሆን ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉና ከሰው በታች የመሆን ስሜት እንዲሰማቸው አልፈልግም ። በእናታችንም ህመም ምክንያት በጣም አዝነውና ተጎድተዋል ምንም እንኳን ባዝንና ብከፋም እነሱን ማበርታት ስላለብኝ የጠነከርኩ መስዬ አጠነክራቸዋለሁ ከፍቅርተ በላይ መሠረት ነገሮችን መቋቋም አትችልም ትንሽ ነገር ያስደስታታል ደሞ ትንሽ ነገር ይሰብራታል  ባይሆን ፍቅር በተፈጥሮዋ አስተዋይ እና ብልህ ስለሆነች ነገሮችን በፅሞና ከማሰቦ በፊት ተስፋ በመቁረጥ ለመሠበር አትቸኩልም ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
7.7K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 19:01:04 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፬
@yanetmasra

እደጅ ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል አንደኛዋ ሴትዬ ወደውስጥ ገብታ ወደኔ ተጠጋች ፤ ከገፅታዋ ልታናግረኝ ፈልጋ መሆኑን ተረድቻለሁ " አንተ ነህ ልጇ  " አለቺን በአገጮ እናቴን እየጠቆመች " አዎ እኔ ነኝ ወንድ ልጇ " አልኳት ከዛ ልታወራኝ ስለፈለገች እደጅ ብቻዬን ይዛኝ ወጣች " ልጄ እኔ የእናትህ አሰሪ ነኝ የኔን ልብስ ለማስጣት ስትንጠራራ ነው የወደቀችው ስለዚህ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ልላችሁ አልችልም እኔም ልጆች እና ቤተሰብ አለኝ በዛ ላይ አባታችሁ እንደሞተም አውቃለሁ ስለዚህ እናታችሁ እስክታገግም የቻልኩትን ላግዛችሁ እጥራለሁ ያው ትረዳኛለህ ብዬ አስባለሁ እኔም የቤት እመቤት ነኝ ከትዳሬ ቀንሼ ነው የማካፍላችሁ ማረግ ከምችለው በላይ ግን ማድረግ አልችልም " አለቺኝ እንዲህም ደግ መሆኗ አስገርሞኛል አያገባኝም ብትል ማን የሚጠይቃት አለ ገፍትራ አልጣለቻት ብቻ " ቀጣዩን እግዚአብሔር ያውቃል ስለመልካም ሀሳብሽ  እግዚአብሔር ይባርክልኝ አመሠግናለሁ " አልኳት " በል እንግዲህ በርታ በል ያለሀት አንተ ነህ የሚረዳም የቅርብ ዘመድ ያላችሁ አልመሰለኝም " አለቺኝ " አዎ ልክ ነሽ የኛ የምንለው የሚረዳን ዘመድ ቀርቶ ወዳጅም የለንም አባቴ ሲቀር ሁሉም ቀርተዋል ከጎናችን ያለው እግዚአብሔር ነው ። አሁን ቁምነገሩ የእናቴ ደህና መሆን ነው ብቻ ጤናዋን ይመልስላት የአካል ጉዳት ከደረሰባት እንዴት ነው የምት... " ቃላቱን መቀጠል ተስኖኝ እንባ ቀደመኝ " እንዴ ኧረ  አታልቅስ በለቅሶ እኮ የሚሆን ምንም ነገር የለም ፤ በርታ ብለህ ተፅናና ደሞ የምን መጥፎ መጥፎ ነገር ማረብ ነው ትድናለች " አለቺኝ ምናለ እንደ አፏ ባደረገልኝ ብዬ ተመኘሁ 



ወደነበሱፈቃድ ጋር ተመልሼ በመሄድ ሁኔታውን ነገርኳቸው በጣም በማዘን " ዩሀንሴ ምንም እንዳትጨነቅ እኛም የምንችለውን ነገር በማድረግ እናግዝሀለን እግዚአብሔር እናትህን እንዲምራት እንፀልይልሀለን " አለቺኝ እቴቴ ፤ የነሱ ማፅናናት ብርታትን ሰጠኝ ማንኛውም ችግር የከፋ ቢሆንም በችግርና በመከራ ሰአት ደሞ ብቻን እንደመሆን ምንም የሚያስከፋ ነገር የለም ። ወደ እናቴ ቤት ስመለስ እቴቴ እና ጋሼ አብረውኝ ሄዱ ።  አንዳንድ የነበሩ ጎረቤቶቻችን በግልምጫ ተቀበሏቸው ፤ የሰው ቤት ነው ብለው እንጂ ከሁኔታቸው አንፃር  ቢያስወጧቸው እራሱ ደስታቸው ነበር ። እናቴ ለራሷ የውስጧን ህመም  እያዳመጠች መምጣታቸውን ብታይም ከቁብም አልቆጠረቻቸው ሁለቱ እህቶቼ ብቻ ፈገግ ብለው ከመቀመጫቸው በመነሳት አክብሮታቸውን ገለፁላቸው ። የእናቴ ነገር ማቃሰት ብቻ ሆነ የተሰበሰቡት ሰዎች የባጥ የቆጡን ያወራሉ የርዕሱ መነሻ የእናቴ መታመም ቢሆንም ስንቱ ቤት ውስጥ ስንቱ ነገር ውስጥ እየገቡ በወሬ አዳረሱት እነ ጋሼን ሰው የሚላቸው ስለጠፋ ካጠገባቸው ተቀምጬ ላወራቸው ሞከርኩ ሀሳቤን ግን መሰብሰብ ተስኖኝ ነበር በቃ እኔ እኔን አልነበርኩም  " እቴት በቃ እናንተ ሂድ ምንም አታደርጉም ባይሆን ነገ ትመጣላችሁ እኔ ግን በዚህ ሰአት ግዴታ መኖር ስላለብኝ እዚህ ነው የማድረው ቢያንስ እስኪሻላት " አልኳት  " እንዴ መጠየቅም አይገባህ ፤ እናትህ አይደለች ሲሆን ሲሆን እኮ አብረህ መኖርም ይገባህ ነበር የተፈጠሩ ክፍተቶች አልደፈን አሉ እንጂ ፤ ደሞ እራትም ያላችሁ አልመሠለኝ ናና ያዘጋጀሁት ነገር አለ ወስዳችሁ ቀማምሱ " አለቺኝ ነገርግን ቀን ላይ የእናቴ አሰሪ የሆነችው ሴት ለእህቶቼ ብላ ምሳ ላይ የሰራችው ምግብ ስላላለቅ ሌላ ስለማያስፈልግ እንዳለና ሳይጨነቁ ወደ ቤት እንዲሄዱ ነገርኳቸው ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
7.4K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-24 19:00:06 የሚጣፍጥ ስቃይ
ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፫
@yanetmasra

አንድ የቀን ክፉ የሆነ ቀን እቤት ሆኜ ሳለሁ ፍቅር እየተንደረደረች መጥታ " እማዬ እማዬ " አለቺኝ እንባ ያረገዘው አይኗ መንታ መንታውን እየወለደ ። ከመቀመጫዬ ተስፈንጥሬ ተነስቼ በእንጥልጥል ያቆመችውን ወሬ እንድትቀጥልልኝ " ምን ሆነች ? " ብዬ አፈጠጥኩባት እየበረረች እንደመጣችው በፍጥነት ከመናገር ይልቅ ተጠምጥማብኝ እዬዬዋን አስነካችው እሶን ላባብል ወይስ የእናቴን ሁኔታ ልወቅ አይምሮዬ ተበረዘ ፤ በጣም ደነገጥኩ ፤ ተረጋግታ እንድትነግረኝ በብዙ ጣርኩ ነገር ግን አንድ ቃል ሳታወጣ ቀረች አማራጭ ሳጣ እዛው ትቻት ወደቤት በፍጥነት ሄድኩ አንድ አራት ሰዎች ቤታችን አካባቢ ይታዩኛል እናቴ ግን አልነበረችም በዛን ሰአት ልቤ ያሰበው በጣም ክፉ ክፉ ነገር ነበር በህይወት የማገኛትም አልመሠለኝ ። በሩ ላይ የተሰበሰቡትን ሰዎች ከመገፍተር ባልተናነሰ ሁኔታ አልፍያቸው ከቤት  ስገባ መኝታዋ ላይ እንደተጠቀለለች እንቅልፍ እንዲወስዳት ትታገላለች በህይወት ስላገኘሗት ደስ ቢለኝም " ግን ምን ሆና ነው ? " ብዬ አጠገቦ የተቀመጡትን ጎረቤታችን ወይዘሮ ብርቄን ጠየቅኳቸው " የምትሰራበት ቤት ጊቢ ውስጥ ከፍ ያለ ድንጋይ አለ እዛ ላይ ወጥታ ልብስ ልታሰጣ ስትል እግሯን ሳት ብሏት ነው መሠለኝ እንዳትሞት እንዳትሽር ሆና ወደቀች ስብርብር  ነው ያለችው የኔ እናት ፤ ወይ ደሀ መሆን ሳያምርብህ እንደባከንክ ኑረህ ዘመንህን መጨረስ ነው ። የእሶስ ከሁሉ ተለየ ገና ባሏን ከማጣቷ በልጅም ሳትባረክ ቀረች ፈተናዋን እያበዛችሁባት ደፋ ቀና እያለች ሰርታ እንኳን እንዳትበላ ተሣስራ መቅረቷ ነው ። በትኩስ ቁስል ላይ ሌላ ቁስል ተደራረበባት ፤ ወይ ፈጣሪዬ እንዴት ታረገኝ ይሆን ? የኛስ መጨረሻ ምን ይሆን አሄሄ "አሉ  በልጅ አልተባረከችም ሲሉ እኔን በነገር ወጋ ሊያደርጉኝ ፈልገው እንደሆነ ሳይገባኝ አልቀረሁም መቼስ እህቶቼን እንዳልሆነ እኔም እሳቸውም የምናውቀው ነገር ነው



ግን የገረመኝ መርዶ እንኳን ሲነገር ቃስ ተብሎ ይሀን ሰው አረጋግቶ ነው እሳቸው ግን የእናቴን ህመም ሲናገሩ ተስፋ በሚያስቆርጥ ሁኔታ እና ቅስሜን በሚሰብር ንግግር ነው ። እንደሳቸው አባባል ዳግመኛ ተነስታ መራመድ የምትችልም አልመሠለኝ ፤ በአንድ በኩል ደሞ የተናገሩት ነገሮ እውነት ከሆነ ቀጣዩ የቤተሰቤ ህይወት ምን ሊመስል እንደሚችል ማሰቡን እራሱ ሳስበው ሰቀጠጠኝ ጠጋ ብዬ እናቴን በአትኩሮት ስመለከታት ጋደም እንዳለች ታቃስታለች ስቃዩ አላስተኛ እንዳላት ከሁኔታዋ ተረዳሁ የለበሰችውን ጋቢ ገለጥ አድርጌ እግሯን ለማየት ስሞክር በነጠላ ጨርቅ ከጉልበቷ አንስቶ እስከ ቁርጭምጭሚቷ በታች ተጠቅልሏል ነፍሴ ከስጋዬ ልቅቅ ያለ መሠለኝ በጣም አዘንኩ ከዛ ፍቅር እያለቀሰች ለምን ልትነግረኝ እንዳልቻለች ተረዳሗት ከዛም የጎረቤታችን ንግግር ምንም እንኳን ባይጥመኝም ይበልጥ ነገሩን ለመረዳት ስል " ታድያ ማነው መውደቋን ያየው ? እዚህስ ማን አመጣት ? ወጌሻ ቤት ሄዳ ነበር  እንዴ ? " አልኳቸው " ያው ስትጮህ የሰሟት አሰሪዋ ናቸው የደረሱላት አሉ ፤ ከዛም አፋፍሰው አካባቢው ካለ ወጌሻ ወሰዶት እና እንደሚሆን አደረጉላት ያው ሲመስለኝ ግን ውልቃት ሳይሆን ስብራት ነው  ፤ ከእንግዲህ በሗላ መራመድ የምትችልም አይመስለኝም ብትራመድ እንኳን ካለዱላ የምትችል ይመስልሀል ? " አሉኝ ይበልጥ ሆዴን አባቡት ከተቀመጥኩበት እጄን ጭንቅላቴ ላይ ጭኜ ፍፁም ፀጥታ በሰፈነበት የውስጤ ጩኸት ብቻ በሚያስተጋባበት ሁኔታ እንባዬን አፈሰስኩት መስራት አለመቻሏ ብቻ ሳይሆን መራመድ ካልቻለች የሚደርስባት የስነልቦና ጉዳት በልጦ ታየኝ ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
7.7K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-23 19:00:41 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፪
@yanetmasra

" ለምን ተገደለ ? " ብዬ ጠየቅኩት ይበልጥ ዝርዝሩን ለማወቅ " ምን መሠለህ አዲስ አበባ መኖር ከመጀመራቸው በፊት ኑሯቸው በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ነበር ተወልደው ያደጉትም እዛው ነው ታድያ አንድ ሚሽነሪ ወደዛ በሄደ ሰአት ወንጌልን መስክሮላቸው ወደ ጌታ ሊመጡ ችለዋል ከአካባቢው ሰው ጋር ተመሣስለው መኖር በከበዳቸው ሰአት ሁሉም አማኝ መሆናቸውን ደረሱባቸው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበራቸው ክብር ሁሉ ተሟጦ ወደ መናቅ ተቀየረ በቤተሰብ ፣ በዘመድ ፣ በሽማግሌ መጤ ሀይማኖትን ትተው የእናት እና የአባታቸውን እምነት እንዲቀጥሉ ተነገራቸው ሆኖም ግን አቋማቸውን ተናግረው ማድረግ እንደማይችሉ እና ላመኑት ወንጌል እንደሚኖሩ ውሳኔያቸውን በነገሯቸው ሰአት ነገሮች ከልምምጥ ፣ ከምልጃ አልፎ ክፋት ላይ ደረሰ አስመርረው ከሀገሩ እንዲለቁ አደረጓቸው መጀመሪያ ግን እንዲሁ እንደዋዛ የለመዱትን ቀዬ ለቀው አዲስ ከተማ መኖር ስለማይሆንላቸው ነገሮች ይረግባሉ ሲሰለቻቸው ይተውናል ብለው በትዕግስት ነገሮችን ማለፍ ጀመሩ ሆኖም ግን አንድ ቀን ቤታቸው ላይ በድንጋይ ወገራ በሚያካሂዱ ሰአት ታዳጊው ልጃቸው ከቤቱ በራፍ ኖሮ ኖሯል የተወረወረው ድንጋይ አናቱን ብሎ ይጥለዋል ደም በብዙ ስለፈሰሰው አጉል ምት ስለሆነ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል ከሀዘን ውጪ የሚያደርጉት ነገር ጠፋ ቤተሰቦቻቸውም በእምነታቸው ምክንያት አንቅረው ስለተፏቸው እናት እና አባት እንዲሁም እህቱ ነበር ለለቅሶ የተቀመጡት ብቻ እሱም ሳይበቃቸው ጉዳታቸውን በመናቅ ሲያንጓጥጦቸው እና ጥላቻቸው ቢበዛ እትብታቸው የተቀበረበትን መንደር ትተው ወደዚህችው አዲስ አበባ መጡ መጀመሪያ ላይ ነገሮች እንዳሰቡት ጥሩ ባይሆንም እያደር ግን



ሠው ሲያውቁ ፣ ሀገሩን ሲለምዱ ስደቱ ቀረ ባይባልም በፊት ከነበረው ግን እየተሻለ መጣ ኑሮአቸውንም እዚህ ካደረጉ በሗላ በብዙ ውጣ ውረድ ቢሆንም እዚህ ደርሰዋል እና የልጃቸው ሰርግ ደሞ ለነሱ ደስታን ካለወሰን አምጥቶ ልባቸውን በሀሴት ቢሞላም ይሀ በቤተሰቡ ተወዳጅ የነበረ መንትያ ወንድሟ ይሄን ቀን ሊያይ ስላልቻለ እና ቤተሰቡን መለየቱ ደስታው ከሀዘኑ ጋር እንዲበረዝ ምክነያት ይሆነዋል " አለኝ የሠማሁት ታሪክ አስገርሞኛልም አስደንቆኛል የሠው ልጅ ተወልዶ እስከሚሞት ድረስ ያለው ታሪኩ ሊገመት የማይችል እንደ መፅሀፍ በየምዕራፉ የተለያየ የህይወት ወጣ ውረድ የሚያጋጥመው ውስብስብ ነገር ነው አሁን ይሄን ታሪክ እንደኔ ያልሰማ ሰው እንባቸው የደስታ ስለሚመስላቸው የቤተሰቡን ሁኔታ ይቀኑበት ነበር ግን በሳቅ የተሸፈነ ጠባሳ በእንባ የታጀበ የተስፋ ጭላንጭል ከፊታቸው መነበቡን ልብ ላለው እና በቅርብ የሚያውቃቸው ሠው ነው ሊረዳው የሚችለው ።

   ሙሽሮቹ የቤተክርስቲያኑን ስርአት ጨርሰው ወደ ግብዥው ቦታ ሲሄዱ እኛም ተከተልናቸው እዛ ያለውን ዝግጁት ጨርሰን ወደ ቤት መመለሳችን አይቀርም እና ወደ ቤት ተመለስን ያየሁት ዝግጅት ሁሉ አስደስቶኛል ከዛ በፊት አይቼ የማላውቀው ስለሆነ መቼም ቢሆን ከአይምሮዬ አይጠፋም እያንዳንዱ ሁኔታ እና ዝግጅት በቅደም ተከተል በአይምሮዬ መዝገብ ላይ አስፍሬዋለሁ ከሁሉም በላይ የሠማሁት ታሪክ ግን ልቤን ነክቶኛል እንደውም በአይምሮዬ ሳስብ የነበረው ስንት አይነት መከራ እና ህይወት በስንቱ ቤት ውስጥ ይኖር ይሆን ወንጌልን ለማስቀጠል ምን ያህል ዋጋ እና ምን አይነት ከሠማሁት እና ካየሁት የተለየ ታሪክ ይኖር ይሆን የኔስ ህይወት ምን አይነት የህይወት አቅጣጫ ይይዛል ? ብዬ ሚሰቤ አልቀረም ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
7.8K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 19:01:22 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፩
@yanetmasra

በወቅቱ አስደናቂ ዝማሬዎች የእግዚአብሔር ክብርን የሚገልጡ የሰዎች ልብ ውስጥ ዘልቀው ገብተው መንፈስን የሚቆጣጠሩ ስለነበሩ ብዙ ምዕመኖች እኔንም ጨምሮ ተባርከንበታል ፤አማኝ ማህበረሰብ ብቻ ሳይሆን የማያምኑትም  ውስጥ ውስጡን የሚያዳምጡ ነበሩ አንዳንዶቹ አላማኞች ችግራቸው አለማመን ሳይሆን የይሉንታ ችግር ነው። ወንጌል ሲመሰከርላቸው እንዲሁም ይበልጥ ስለእውነቱ ያውቁና ለመወሰን ይቸገራሉ ቤተሰቦቼስ ፣ጎረቤቶቿስ፣ትዳሬስ ፣ልጆቼስ ብለው ወደኃላ ያፈገፍጋሉ እነሱ ሰዎች ይበልጥ ክርስቶስን ያውቁ እና የመስቀሉ ስራ የገባቸው አይመስለኝም ምክንያቱም ክርስቶስ ከሁሉም በላይ ነው ሌላው ቢቀር እኛ እንኳን የራሳችን ሳይሆን የእርሱ ነን።

  በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የጴንጤ ሠርግ አየሁ፤ከዛን ቀደም ያየኃቸው ሠርጎች ሁሉ አላማዊ የሆኑ የሚዘፈንበት ፣የሚጨፈርበት ፣የሚጠጣበት ከክርስቶስ በላይ ሙሽሪት እና ሙሽራው ፣ሚዜ እና ቤተሠብ የሚደነቅበት ነበር የጴንጤ ሰርግ ስነስርአት ምን ሊመስል ይችላል የሚለው ሀሳብ ልቤ ጠይቆ ቢያቅም አጋጥሞኝ ስለማያውቅ ላውቀው አልቻልኩም ከዛን ግን ጋሼ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎደኛው ሴት ልጅ ልትዳር ስለነበር የዛ ፕሮግራም ላይ ይዞኝ ተገኘ ይህን ሠርግ ልዩ የሚያደርገው ነገር ቤተክርስቲያንአችን ከተቆረቆረች ጀምሮ ሠርግ ተከናውኖባት  ስለማይታወቅ ይሀ የመጀመሪያ ነበር ታዲያ ሙሽሮቹን ከቤታቸው ጀምሮ አጅበን ወደ ቤተክርስቲያናችን ሄድን  መጀመሪያ በቤት ውስጥ እየተዘፈነ ሳይሆን እየተዘመረ ሙሽሪት ከቤተሰቦቿ ጋር እንዲሁም ከሚዜዎቿ ጋር በመሆን ሙሽራውን እየጠበቀች ነበር



በወቅቱ ያየሁት ሁኔታ በውስጤ ደስታን ፈጥሮልኛል ካሰብኩትም በላይ ደስ የሚል እና ከምድራዊው ሙሽራ በላይ የሠማያዊውን ሙሽራ የሚያከብር ስለነበር ነው በቤተክርስቲይናችን ውስጥ በዝማሬ ፣በቃል፣በፀሎት ስነስርዓት ታጅቦ ሙሽራው እና ሙሽሪት ጋብቻቸውን ፈፀሙ ምንም እንኳን በወቅታዊ ችግር ምክንያት የታሠበውን ያክል ሞቅ ደመቅ ባይልም ቆንጆ በሚባል ሁኔታ ጋብቻቸውን ፈፀሙ እግዚአብሔር ሲረዳ እና የሠርጋቸው ቀን መጥፎ ጠባሳ እንዳያርፍበት ሲጠነቀቅላቸው ምንም አይነት ረብሻ እና ብጥብጥ ያስነሳ ግለሰብም መንግስትም አልነበረም የሙሽሪት ቤተሰቦች ከደስታቸው የተነሳ እንባቸው እንደጎርፍ ያዘንባል ሀዘን ነው እንዳልል በልጃቸው። የደስታ  ቀን መሆኑ ሀሳቤን አከሸፈው የደስታ ነው እንዳልል ከጎናቸው ያሉ ሠዎች ትክሻቸውን መታ መታ እያደረጉ ያፅናኑአቸዋል ቀስ ብዬ አንገቴን ወደ ጋሼ ጠጋ አድርጌ በጆሮው "እንባቸው የደስታ ነው ወይስ የሀዘን ?ሁል ጊዜው ሙሽራ ስትዳር ማልቀስ ወግ ነው እንዴ?"ብዬ ጠየኩት "ደስታም ያስለቅሳል ግን አንዳንዴ  ደስታ እና ሀዘን ይቀላቀላል እና ያስለቅሳል  " አለኝ ትክዝ ተብሎ ፊቱ ላይ የመረበሽ ስሜት ይታይበታል "እንዴት ?" አልኩት ነገሩ ምንም እንዳልገባኝ በሚያሳብቅ አስተያየት። እየተመለከትኩት "አው ምን መሠለህ አሁን የምታገባው ልጃቸው ሀዜብ መንታ ነበራት አባታቸው እንደነገረኝ ከሆነ ከእህቱ ጋር እና ከቤተሠቡ ጋር የተለየ አቅርቦት ነበረው ሆኖም ግን ቤተሠቡ ባልጠበቀው ሁኔታ ከደጃፋቸው ተገደለ ይመስለኛል የእሱ አለመኖር ነው ያስለቀሳቸው "አለኝ ፊቱን ቅጭም አድርጎ .........ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
8.1K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-21 19:00:26 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵
@yanetmasra

"አው ጋሼ እሱንስ ልክ ነህ እግዚአብሔር አለ ነገር ግን መልካም መልካሙን ማሠብ ይሻላል " ብዬ የጀመርኩትን ጥያቄ ዘጋሁ 

  እውነትም ግን ቢታሰርስ ብዬ አሰብኩ ከባድ እንደሚሆንበት አልተጠራጠርኩም እንደውም ምን ትዝ አለኝ በእኛ እድሜ ክልል ውስጥ ያለ ዩሴፍ የተባለ ልጅ መታሰርን እና በቅርብ መፈታቱን ነግሮኝ ነበር ታድያ ምንም ልጅ ቢሆንም ደፋር እና ወንጌልን ሲናገር የማይፈራ ስለነበር እሱን እና የተወሰኑ ጓደኞቹን ለጥቂት ቀናት በእስር አቆይተዋቸው ነበር ታድያ በጣም ክትትል ያደርጉባቸው ነበር ውስጥ አንድ አንድ የሚሰልሉ ሰዎችን በማያውቁበት መንገድ ቢያስገቡም እነሱ ግን መጠርጠራቸው አልቀረም ስለዚህ ፀሎት በሚያደርጉ ጊዜ ከታወቀ ተወስደው መቀጣታቸው እና የእስር ጊዜያቸው መራዘሙ ስለማይቀር መፍትሄ አድርገው የወሰድት እዛው እስር ውስጥ እንዳሉ ዩሴፍ ጮክ ብሎ ጉሮሮውን ሲጠራርግ ሁሉም በአንድ መንፈስ ሆነው በውስጣቸው ፀሎት ያደርጋሉ መልሶም ከጥቂት ደቂቃ በሗላ በተመሳሳይ ሁኔታ ጉሮሮውን የሚጠራርግ አስመስሎ ድምፅ ያወጣል ያኔ ጨረሱ ማለት ነው ሆኖም ግን እንዴት አድርገው እንዳወቁ ባይታወቅም ይህንንም ዘዴ አወቁባቸው ስለዚህ ያላቸው አማራጭ መፀዳጃ ቤት ቤት በሚል ሰበብ ባለቻቸው ጥቂት ደቂቃ መፀለይ ነው እኔን የገረመኝ ምንም ያህል ለወንጌል እንቅፋት ቢሆኑም እግዚአብሔር ግን ከስር ከስር ስራቸውን ስለሚያከሽፍባቸው ማድረግ የፈለጉትን ያህል ሊያደርጉ ቀርቶ አንገቴን ለቢላ እያለ የሚያመልከው መብዛቱ ነው ። አይናቸው እያየ ማስተዋል ስለተሳነው ልባቸው ስለደነደነ እንጂ የአማኙን ጥንካሬ እና የእግዚአብሔርን ድንቅ እና ተአምራት እያዩ እነሱ እራሳቸው ለመዳን ይችሉ ነበር



እስር ቤት ውስጥ መፅሀፍ ቅዱስ ማስገባት በፍፁም አይፈቀድም ውስጥ እንኳን ታስረው ህብረት ማድረግ የቻሉ ሰዎች በቃላቸው ያለን ጥቅስ በመናገር በእርሱ እርስ በእርስ እየተወያዩ እንደሚልዩ ሰምቻለሁ ታድያ በዛን ሰአት መፅሐፍ ቅዱስ ለማግኘት የነበራቸው ርሀብ ልዩ እንደነበር ታስሮ የተፈታው ወንጌላዊ ዘላለም በአንድ ስብከቱ ላይ ከጥቂት ቀናት በፊት አስተምሮ ነበር ታድያ በዚህ ስደት ውስጥ ወንድ ነው ሴት ናት ወጣት አዛውንት የሚባል የቅጣት ድልድል የለም የወታደራዊውን መንግስት ህግ ያልሰማ እና ያልተከተለ ቅጣቱን ይቀበላል ድብደባ ፣ መታሰር እንዳለ ሁሉ ባስ ሲልም ሊገደሉ ይችላሉ ለወንጌለሸ ብለው ተሰደው የሞቱ ስማቸው በዘለአለም ህይወት መዝገብ ላይ መስፈሩ ጥርጥር የለኝም
በወቅቱ ከድብደባ ውጪ የደረሰብኝ ከባድ ነገር ባይኖርም እነሱ እንደሚሉት ማድረግ ካልቻልኩ በወሬ የምሰማውን የእስርቤት ታሪክ በአካል እንደማየው አልጠራጠርም
   ከጥቂት ቀን በሗላ ወደ ክፍል ሀገር እንዲሄዱ የተደረጉ አገልጋዬች በመምታጣቸው ቤተክርስቲያኗ ያዘጋጀችው የምረቃ ዝግጅት በከፊሉም ቢሆን ተካሂዶ እዚህ ለመድረሱ ዋጋ የከፈሉ አሁን ግን በቦታው ስላልተገኙ ሁሉ ተፀልዮ መደበኛ ፕሮግራም ተጀመረ በቋሚነት እሁድ እና ማክሰኞ የወጣቶች ፕሮግራም እንዲሆን ተወሰነ አካሄዱ አስደስቶናል ፤ በሌላ አካልም የደረሰ ጫና እና ግፊት አልነበረም አይሰሙም ብለው ትተውን ይሆን ወይም ደሞ ጊዜውን ጠብቀው የሚያፈነድትን ቦንብ አጥምደውልን ይሆን በጊዜው የታወቀ ነገር አልነበረም  ። እኔም ቤተክርስቲያኗ ፕሮግራሞችን በመደበኛ መልኩ ማስኬድ ከጀመረች ጀምሮ የማደርጋቸው እንቅስቃሴዎች እየጎሉ መጡ ወንጌልን መናገር ስለወንጌል መመስከር ቋሚ ስራዬ ሆነ ....ይቀጥላሉ
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
8.5K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-20 21:24:40
በቁርአን ቃል ጅማሮውን ያገኘው የ2022 ኳታር አለም ዋንጫ የመጀመሪያ ጨዋታ የመጀመሪያ ጎል ኢኳዶሮች ከስቆጠሩ በኋላ ተንበርክከው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ

አዘጋጅ ሃገር የሆነችው ኳታር ከ ደቡብ አሜሪካዋ ኢኳዶር ጋር 1:00 ላይ የተጫወቱ ሲሆን ጨዋታው ከፍፁም ብልጫ ጋር ኢኳዶር 2-0 አሸንፋለች!
ጎሉን ካገቡ በኋላ ደስታቸውን የገለፁበት መንገድ ብዙዎቹን እያነጋገረ ነው እንደ The Sun ያሉ ጋዜጦች ደሞ በፊት ገፃቸው ይዘው ወጥተዋል።

የአለም ዋንጫ ከተጀመረ 92 አመታት ያስቆጠረ ሲሆን በዚህ ሁሉ አመታት አዘጋጅ ሃገር የመጀመሪያ ጨዋታ ተሸንፋ አታቅም ዛሬ ግን ታሪክ ተቀየረ

ኢኳዶር ከ92% በላይ ክርስትና(ካቶሊክና ፕሮቴስታንት)እምነት ተከታይ ናቸው

@christian_mezmur
9.1K viewsedited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-20 19:01:15 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፴፱
@yanetmasra

ቀኑ ደረሰ ፕሮግራሙ የሚደረግበት ቀን ልባችንን ደስታ ቢሞላም ግርግር ሊፈጠር እንደሚችል ማንም ሳይጠረጥር የቀረ አልነበረም ምክንያቱም ሌላው ቢቀር እንኳ ከሠሞኑ ብዙ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ሲያደርጉ ነበር። ከምዕመናን በላይ አገልጋዮች ላይ የበለጠ ጫናው እየጠነከረ መጥቷል እንደውም ምርቃቱ በሚዘጋጅበት ቀን ሊያስሯቸሙ እንደሚያስቡ ጭምጭምታ ስለተሠማ አንዳንዶቹ ከከተማ እንዲወጡ ግፊት ተደርጎባቸው ነበር። ሁሉም ተገኝተው ከተወሰዱ ቤተክርስቲያኑን ሊመራ የሚችል  አልነበረም ታዲያ ያልተጠሩት እንግዶቻችን ግን እንደሚመጡ የምናውቀው የቀበሌ ወጣቶች እና የቀበሌ ወጣት ሊቀመንበር የነበረው እድሜው ከ30ዎቹ መጀመሪያ የሚገመተውን ወጣት ጨምሮ መጡ እንደገቡ ትርምስን ፈጠሩ ' ለቀባሪ አረድት ' እንደሚባል ሁሉ በመምጣታቸው የተገረመም የተደናገጠም አልነበረም የመጡት ግን የመጡት ግን ፍርሃት እና መደናገጥ ይታይባቸዋል ብለው ስላሰቡ ስላልታየብን ተገርመው ነበር ቢሆንም ግን ሠብሠብ አርገው የቀሩትን አገልጋዮች ወደ ቀበሌው ወሰዶቸው ሌሎቻችን ግን እንድንበተን ተደረገ ብዙ ጊዜ ጭቆናውን ባስ እና ጠበቅ የሚያረጉት በአገልጋዮች ላይ ነበር ሲመስለኝ "እረኛውን ምታ መንጋው ይበተናል" የሚለውን መርህ የጨበጡ ይመስላል ታዲያ የዛን ቀን እንደታሰበው ፕሮግራሙ ሳይካሄድ ቀረ እነሱም እዛው እስር ቤት አደሩ ይህን ያደረጉበት ምክንያት በእምነታቸው  የተነሳ ቢሆንም ነገሩን የአብዮቱ  ተቃዋሚዎች ብለው ለማድበስበስ ጥረት አደረጉ እውነታው ግን የአደባባይ ሚስጥር ነው። የቤተክርስቲያን መደበኛ ፕሮግራም ላልተወሰነ ቀናት ማካሄድ ባለመቻሉ ሁሉም አማኝ ቤቱ በሚመቸው መልኩ  ፆምና ፀሎት በመያዝ ለታሰሩት አገልጋዮች



እንዲፀልዩ እና በግላቸውም ቢሆን ወይም ከቤተሠቦቻቸው ጋር በጋራ ህብረት በማድረግ እንዲበረቱ  ተደረገ ፤እኛም በቤት ውስጥ በመሆን ፀሎተችንን ማሠማት ቀጠልን የምድሩ መሪ የራሱን እቅድ የሚያስፈፅም እንጂ የሀይማኖትን እኩልነት የማያራምድ ባለመሆኑ ከዙፋኑ ሆኖ የሚያየን ልቡ ለኛ የሚራራ እውነተኛ ፈራጅ ለሆነው እግዚአብሔር ጩኸታችንን እናሰማ ነበር

   ሳይፈቱ ከአንድ ወር በላይ የቆዩት አገልጋዬች በምን ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ ስለፈለኩ ጋሼ እቤት ሲመጣ " ጋሼ የታሰሩት አገልጋዬች ነገር ከምን ደረሰ ' ቄሱም ዝም መፅሀፉም ዝም ሆነሳ ነገሩ ፤ ሳይፈቱ ለእረጅም ጊዜ ቆዩ ፤ እዛ ውስጥ የተመቻቸው ይመስልሀል ?" አልኩኝ በልቤ ውስጥ የታመቀውን እንቆቅልሽ ቢፈታልኝ በማለት " ወይ ዩሀንስ ተመቻቸው ትላለህ እንዴ የአንበሳ መንጋጋ ውስጥ ገብተው እዛው ያኝኳቸዋል እንጂ ምን ይመቻቸዋል ብለህ ነው ? እንደውም አንድ ሁለት ቀን ሄጄ ላያቸው ሞክሬ ነበር " በምክር እና በማስፈራሪያ አልሆን ሲላቸው የጉልበት ስራም ያሰሯቸው ጀምሯል ባስ ሲልም የድላ ውርጅብኝ ያወርድባቸዋል ዘንድሮስ ለብቻው ነው ሰይጣን ሀይሉን አጠራቅሞ እየተዋጋን ነው ደግነቱ የሚጠብቀን አይተኛም እንጂ እንደሱ ፍላጎት ቢሆን ኖሮ አንድ አማኝ ባልኖረ ነበር እኔንም ቢሆን አልወደድኝም ምን እንደሚሉ ባላውቅም በሄድኩ ቁጥር ገልመጥ ገልመጥ አድርገው በሹክሹክታ የሆነነገር ሲዶልቱብኝ ሰምቻለሁ እኔም የእነሱ እጣ እንደሚደርስብኝ አልጠራጠርም ግን ፈርቼ አይምሰልህ አንዳች ልቤ አይታወክም ቢሆንም ግን አንዳንዴ የቤተሰብ ሀላፊ ስትሆን የነሱ ነገር ያስጨንቅሀል ባለቤቴ ስራ ስለማትሰራ የልጆቹ ህይወት እንዴት ይሆናል የሚለው ነገር ያሰጋኛል በሌላ በኩል ደሞ ከኔ በላይ እግዚአብሔር እንዳለላቸው ሳስብ እፅናናለሁ " አሉኝ ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
8.6K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 21:00:38 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፴፰
@yanetmasra

" ዋናው ሰላም መሆንሽ እና መመለስሽ ነው " አልናት
    ያን ጊዜ ነበር ወፌ ላላ ግርፋት ሲባል የሰማሁት ያው ቤተክርስቲያን በወቅቱ ስላልተቀረቆረ ህብረት የሚደረገው እቤት ውስጥ ፣ ወይም ቅዳሜ ቅዳሜ ወደምንገናኝበት የፀሎት ዝግጅት ላይ ነበር ታድያ በዛን ወቅት የምናውቃቸው ወጣት አገልጋዬች ከፀሎት ህብረት መሪያችን ከአብርሀም ጋር የማይጠፉትን እና እራሱን አብርሀም ጨምር ሊያስሯቸው እንደወሰዷቸው ሠማን በጣም በማዘናችን የተነሳ የተደናገጥነውም ጥቂቶች የምንባል አይደለንም ዋናው ጭንቀታችን መታሰራቸው ብቻ ሳይሆን ከታሰሩ በሗላ ምን ይሆናሉ የሚለው ጥያቄ ነበር ታድያ ለአንድ ሳምንት አስረው ከለቀቋቸው በሗላ የተደረጉትን ከአንድ አንዶቹ ሰማን በፖሊስ ጣቢያው ውስጥ ወፌይ ላላ በተከታታይ ቀናት ውስጥ እንደተገረፉ ሠማን በአንድ ሳምንት ቆይታቸው ውስጥ  ፊታቸው ግርጥት ማለቱ ምን ያህል ስቃይ እንዳሳለፉ ማረጋገጫ ሆነን ለተወሰነ ቀናት ከቤታቸው ሆነው አገግመዋል ታድያ ግን ነገሮች በዚ ሳያበቁ እና ሳይቋጩ ቀሩ እንደውም በሰው ቤት የሚደረገው ህብረት እና ፀሎት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ብዙ ወጣት እና ልጆች ተይዘው እንዲማሩ ለምዕመኑም ሠፊ እንዲሆን በማለት ቤተክርስቲያን የመቆርቆር ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ተሠማ የሁሉም ልብ የመጣው ይምጣ እንጂ ማድረጋችን አይቀርም የሚል ገፅታ ይነበብበታል አንድ በጌታ የሆኑ እድሜያቸው ከ60 አመት በላይ የሚገመቱ አባት መኖርያ ቤታቸው ቤተክርስቲያኗ እንድትቆረቆርበት ሲሉ በፍላጎት ሰጡ ይሄ ደሞ አስደሳች ዜና ነበር የእሳቸው መውደቂያ ያሳሰበው ሠውም ሌላ ቤት እንዳላቸው ሲጠይቁ " ከእንግዲህ ለየትኛው እድሜዬ እኔ ወደ ልጄ ሄጄ ከእርሷ ጋር እኖራለሁ ቤቷ ለኔ ለአባቷ መሠብሰቢያ በቂ ነው ።



ይሄ ውሳኔም እሷን ያስደስታታል እንጂ ፈፅሞ የሚያስከፋት ነገር አደለም " ብለው መለሱ  ከዛን ቀን በሗላ መኖሪያ ቤቱን ወደ አምልኮ ቤት ለመቀየር አንዳንድ ለውጦች ተደረጉበት ሁሉም ያለውን ከጉሮሮው ፣ ከልጆቹ ፣ ካለው ቀንሶ እያዋጣ አብሮ በመስራት እና በመደጎም ቤተክርስቲያኗ ተሰራች እኛም ደሞ ትምህርት በሌለ ሰአት እና ቅዳሜ እና እሁድን እዛው በመዋል አንድ አንድ ነገር እናግዝ ነበር ሁሉም ምዕመን ወጣት ሳይል አዛውንት በደስታ እና በተስፋ ነበር ጉልበቱን የሚያፈሰው " እኛ የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን እቺ ቤተክርስቲያን በተስፋ እና በምኞት ብቻ አትቀርም ተሰርታ ታበቃለች የፈለጉትን ቢያደርጉ ቀሪውን እግዚአብሔር ያውቃል " የሚል አስተሳሰብ በሁሉም ልብ ውስጥ ዘልቆ ገብቶ ነበር ። ወደ መጨረሻው ማገባደጃ ሲደረስ የሁሉም ደስታ ወደር አጣ በየሰው ቤት ማምለክ ቀርቶ በቤተክርስቲያን ማምለክ ልንጀምር ነበር የማስመረቂያ ዝግጅትን ለማዘጋጀት ሁሉም እየተሰናዳ አንዳንድ የሙዚቃ መሳሪያዎችን በውሰት ከሌላ ቦታ ለማምጣት እንዲሁም የሙሉ ጊዜ አገልጋዬች የነበሩ ያላቸው የየራሳቸውን ጊታር ይዘው እንዲመጡ ተደረገ በፀሎት ህብረት ውስት ያሉ የመዘመር ፀጋ ያላቸው ልጆች በእግዚአብሔር ፀጋና በራሳቸው ትጋት ለዝማሬ ይዘጋጅ ነበር የኔ የፀጋ ስጦታ ወንጌል መናገር ነው እና በዕለቱ ከኛ ህብረት ውስጥ ተመርጬ የምስራችን ቃል እንድናገር እድል ተሰጠኝ ይህች ቤተከርስቲያን ድንቅ ነገር እንደሚሰራባት ብዙ ሠዎች ወደ ጌታ መጥተው እንደሚማሩባት እና ለአዲስ ትውልድ መሠረቱ የፀና የማይገለበጥ እምነት እንደሚተላለፍበት የሁሉ ተስፋ ነበር ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
8.5K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ