Get Mystery Box with random crypto!

Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር C
የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር
የሰርጥ አድራሻ: @christian_mezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.45K
የሰርጥ መግለጫ

🗣እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብከዋለን!
ትክክለኛ የሆኑ የወንጌል አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረጉ፦
ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ምስክርነቶች፣ የሪቫይቫል ታሪኮች፣ ዝማሬዎች፣ መንፈሳዊ ዜናዎች፣ እንዲሁም መንፈሳዊነታቸውን የያዙ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ!
ለወዳጅ ጋደኞቻቹ #ሼር በማድረግ ይጋብዙ!
አስተያየት @ChristianMezmur_bot ላይ ፃፉልን✍
ሁሌም ከኛ ጋር ስለሆናቹ እናመሰግናለን!

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-10-28 19:01:18 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፱
@yanetmasra

ለተወሰነ ቀን እቤት ውስጥ ተኝተው ከረሙ እስኪያገግሙ ድረስ እደጅ መውጣት የማይታሰብ ነገር ነበር ቢሆንም ግን ሊፀልይላቸው የሚመጣ እና በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ፀልዩልኝ እያለ የሚመጣ ሰው የዋዛ አልነበረም በጣም ቢገርመኝም አንድ የተረዳሁት ነገር ቢኖር መቼም ቢሆን ወንጌል እንደማይቆም ነው ምንም ቢፈጠር ቢገደሉ ፣ ቢታሰሩ ፣ ቢደበደቡ እውነት ግን እያደረች ራሷን ትገልጣለች አንድ ቢታመም አንዱን ይተካል ፤ አንዱ ቢሞት እግዚአብሔር አንዱን ይሾማል የሰዉ ቁጥር በዛም አነሰ እግዚያብሄር ግን መወደሱ እና መመለኩ የማይቀር ነገር ነው

   ነገሮች እያየናቸው እየከፉ መጡ ከትላንት ዛሬ ፣ ከዛሬ ነገ መከራው አንድ ደረጃ እየባሰ መጣ እኔና በሱፈቃድ ሳንቀር ትምህርት ቤት ያሉ ተማሪዎች ይዝቱብን ጀመር አንድ ቀን በጃቸው ከገባን እንደማይለቁን እርግጠኛ ነበርኩ በወቅቱ ያዘንኩት ለበሱፈቃድ እናት ነው አሁን እኛንም ከደበደቡ እንዴት አድርገው ሶስት ህመምተኛ ብቻቸውን ያስታምማሉ ብዬ ተጨነቅኩላቸው እግዚአብሔር ፀሎቴን የሰማኝ መሰለኝ የበሱፈቃድ አባት አገግመው ከቤት እስኪወጡ ድረስ ምንም ሳንሆን ቀረን አንድ ነገር ቀለለ ኡፎይ ከማለታችን ሌላው ችግር መምጣቱ የማያባራ ሆነ አንዱን መሰናክል አለፍን ብለን ሳንጨርስ ሌላው ደሞ ሊተበትበን ይመጣል ቤተሰቡ አንድ በአንድ መጠቃት ጀመረ ፤ ቀጣዩ ተጠቂ ሆነው የተገኙት ደሞ የበሱፈቃድ እናት ናቸው የሠፈሩ ሴቶች ተማክረው ከእድሩ አስወጧቸው ከሀዲ ከኛ ጋር ህብረት የለውም ብለው ተነሱባቸው በእምነታቸው ብቻ ከማህበራዊ ህይወት እንዲገለሉ ተደረጉ ማንም ቢሆን ከሳቸው ጋር ህብረት ማድረግ የሚፈልግ ጠፋ ታድያ



እንዲ እንዲሆን ያደረገችው አንደኛዋ እናቴ መሆኗን ስሰማ ከልብ አዘንኩ የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶኝ አይናቸውን ማየት ከበደኝ ይባስ ብለው ደሞ " ይኸው ሰው ሁሉ እምነቱን እንዲበርዝ እየበከሉ ነው የኔንም ምንም የማያውቀውን ልጄን ጴንጤ አደረጉብኝ ዝም ካላችሁ ነገ ከነገ ወድያ ወደናንተ ቤት ሰተት ብሎ እያንኳኳ ይመጣል ካሁኑ ልጆቻችሁንና ቤተሰባችሁን ካሁኑ ካላራቃችሁ እንዲሁም ከማንኛውም ማህበራዊ ግንኙነት ካልገደብናቸው መጨረሻችን አያምርም እያደር ባዶ  ያስቀሩናል " ብላ አሳመፀች ሰውም ያጉረመርምባቸው ጀመር " ልክ ነው ካሁኑ እርምጃ ካልወሰድን እዬዬው ነገ ቤታችን ሰተት ብሎ ይገባል " ብለው ከእድሩ አስወጧቸው ሰድበው ፣ አንጓጠው በክብራቸው ተዘባብተውባቸው መለሷቸው እንዲህ ከተባሉ በሗላ አብርያቸው መኖር ከበደኝ ሳወጣና ሳወርድ ቆይቼ " በኔ ምክንያተሸ ችግር ውስጥ እንድትገቡ አልፈልግም እናቴ ስላደረገችው ነገር በጣም ይቅርታ እኔ በሷ ቦታ ሆኜ ይቅርታ እጠይቃለሁ ከዚ በሗላ ግን አትደግመውም አሁን እናንተ ጋር ስለምኖር በንዴት ነው ልጄን ጴንጤ አደረጉብኝ ብላ በክፋት የተነሳችባችሁ ከዚ ቤት ግን ከወጣሁ ምንም ልትላችሁ ስለዚህ ከዚ በሗላ ከናንተ ጋር መኖር አልችልም ስለሁሉም አመሠግናለሁ አልኳቸው እሳቸውም " ስለምን መውጣት ነው የምታወራው ወጥተህስ የት ለመሄድ ነው በዛ ላይ ያንተ ጥፋት ባልሆነ ነገር ራስህን መውቀስና ይቅርታ መጠየቅ አስፈላጊ አደለም እናትህ አለማወቋ ነው እንድትሰድበኝ ያደረጋት በዛ ላይ እሷ ሳትሆን በውስጧ ያለው እርኩስ  መንፈስ ነው እንዲ እንድትናገር የሚያደርጋት እኔ ቂም አልይዝባትም አንተም ብትሆን እወጣለሁ የሚለውን የጅል ሀሳብ ከአይምሮህ አውጣ" አሉኝ ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
4.7K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 08:21:33 ዝማሬ “ ከሰማይ የመጣ"
ዘማሪት Azeb Hailu
የተለቀቀው October , 2022
Size 6MB
ርዝመት 6Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
5.1K viewsedited  05:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 08:20:49
ዝማሬ “ ከሰማይ የመጣ"
ዘማሪት Azeb Hailu
የተለቀቀው October , 2022
Size 77MB
ርዝመት 6Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
4.8K viewsedited  05:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 21:00:57 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፰
@yanetmasra

ኑሮን ከነበሱፈቃድ ጋር አሀድ ብዬ ጀመርኩት የኑሮ ዘይቤያቸውን ፣ የቤተሰቡን ባህሪ ሁሉ ተላመድኩት ከጥቂት ጊዜ በሗላ እንደ እንግዳ ሳይሆን እንደ ነባር ቤተሰቡ አባል ሆንኩ ቤተሰቦቼ ጋር ሄጄ እንዳላገኛቸው እናቴ ፍቃደኛ ባለመሆኗ እህቶቼን ብቻ ከደጅ አገኛቸዋለሁ እኔ በመውጣቴ ምክንያት መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ እንዳያቆሙና የመንፈሳዊ ህይወታቸው ጉዞ እንዳይቋጭ ፈርቼ ነበር ምክንያቱም ችላ ማለት ነገሮችን እርግፍ አድርገን እንድንተው ምክንያት ይሆናል ታድያ እኔ የለሁም ብላችሁ ማንበብ እንዳትተው አጥኑ ብዬ በብዙ መከርኳቸው ንግግሬ ከመማፀን አይተናነስም በተለይ ደሞ ፍቅርተ ታላቅ ስለሆነች ሀላፊነቱን እንድትወስድ ጫናውን በሷ ላይ አደረኩ ደስ የሚለው ነገር ግን የኔ አለመኖር እንዳሰብኩት ክፍተት አልፈጠረም መፅሀፍ ቅዱሴን እቤት ትቼው ስለወጣሁ እናታችን ሳትኖር ተደብቀው እንደሚያነቡና በቀላሉ እንዳታገኘው ሸሽገዋት እንደሚያስቀምጡት ነገሩኝ ይህን ስሰማ ከልቤ ተደሰትኩ እግዚአብሔር እሱን አጥብቀው የሚፈልጉበትን ፍላጎት በልባቸው ስላስቀመጠ አመሠገንኩት ከመሠረት በላይ ደሞ ፍቅርተ በጣም ጠንካራ ሆናለች የእግዚአብሔርን ነገር አጥብቃ ይዛለች ለሱም ደሞ ማሳያ የሚሆነው በፀባይዋ በጣም ብዙ ለውጥና መሻሻል እያየሁባት ስለሆነ ነው ፤ መሠረትም የእሷን ፈለግ እንደምትከተል እምነቴ ነው እናም ይህን ከነገሩኝ በሗላ እኔ እነበሱፈቃድ ጋር ሁለት መፅሀፍ ቅዱስ ስላለ የኔን ለነሱ ልተውላቸው ወሰንኩ ግን ደሞ እናቴ ካየች ከኔ የከፋ ነገር እነሱ ላይ ልታደርግባቸው እንደምትችል አውቅ ስለነበር እጅግ በጣም እንዲጠነቀቁ አበክሬ ነገርኳቸው ምክንያቱም የሚመጣባቸውን ችግር በዛ እድሜያቸው ለዛውም ሰው ሳይኖራቸው ይቋቋሙታል ብዬ በፍፁም አላስብም ደሞ ታላቃቸውም ስለሆንኩ ይሆን ወይም አባት ስለሌለን ጉዳት ላይ እንዳይወድቁ በጣም እሳሳላቸዋለሁ



እኔም ብሆን መጠለያና ቤተሠብ ባገኝም ባጠቃላይ ግን ክርስቲያን የሆነው ህብረተሰብ ላይ የሚደረግበት ጥላቻ እየነገሠ መጣ አንድ ቀን ሀገር ሰላም ብለን በተቀመጥንበት ሰአት አገልጋዬች ላይ ድብደባ እንደተፈፀመ ሰማን በወቅቱ ደሞ የበሱፈቃድ አባት አቶ ታራኩ አገልጋይ ስለሆኑ ለአገልግሎት ወጥተው ነበር እሳቸው አንድ ነገር ሆኑ ብለን ልባችን ተንጠለጠለ ግን ስለተከሰተው ነገር እንቅጩን የሚነግረን ሰው ጠፋ ወይ ተመተዋል ፣ ወይ አልተመቱም ፣ እዚ ጋር አየናቸው የሚለን ጠፋ ብዙ ከተጨነቅን በሗላ ግን አመሻሽ ላይ የቤቱ በር ተንኳኳ ሶስታችንም ከተቀመጥንበት ተስፈንጥረን ተነሳን ተሽቀዳድመን በሩን ስንከፍተው ጓደኞቻቸው ተሸክመዋቸዋል ፊታቸውን ሳየው በህይወት ያሉ አልመሠለኝም ነበር ክፉኛ ተጎድተዋል በሱፈቃድ ሲመታ ከደነገጥኩት በላይ ድንጋጤ ተሰማኝ ትልቅ ሰው ሲደበደብ ይበልጥ ስለሚያሳዝን ይሆን ባላውቅ ልቤ ተሰበረ አይኖቻቸው አብጠው ፣ ድምፃቸው ስልል ብሎ ሲያቃስቱ ሁኔታቸው አስፈራኝ በወቅቱ በሱፈቃድ እና እናቱ እራሳቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር ከድንጋጤያቸው የተነሳ እንደውም ሳይሞቱ ሊያለቅሱላቸው ቃጥቷቸው ነበር የተሻልኩ ሆኜ የተገኘሁት እኔ ነበርኩ እራሴን አረጋግቼ እነሱን ተረጋጉ ማለት ጀመርኩ ቢረጋጉ ብዬ ፤ ነገር ግን አቶ ታሪኩን ያመጡ ወዳጆቻቸው ተቆጥተው ከስንት ሰአት በሗላ ተረጋጉ የተደበደቡትም ምዕመኑን ሰብስበው ሲያስተምሩ ስለተገኙ መሆኑን ነገሩን ከሌሎቹ በላይ የእድል ነገር ሆኖ እሳቸው ላይ በረቱባቸው እሳቸው ግን ክፉ ነገር አልተናገሩም እንኳን ሊራገሙና ሊሳደቡ ቀርቶ እኛንም ከክፉ ንግግርና ከአስተያየት እንድንቆጠብ ተቆጡን "የሚረግሟችሁን መርቁ ተብሏል ስለዚህ እየረገሙን እንመርቃቸዋለን ፤ እየሰደቡን እንወዳቸዋለን አሳዳጆቻችንን የሚያሳድድ ጌታ ብቻ ነው ስለዚህ በእርሱ ስራ ጣልቃ አትግቡ " አሉን እኛም ውስጣችን ቢከነክነንም ዝም አልን ።


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
5.2K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 19:01:34 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፯
@yanetmasra

የሚባለው ነገር እውነት ነው የምናውቀውንና የተገራንበትን ነገር ነው በህይወታችን የምናንፀባርቀው

    ቀን ቀንን እየተካ ወራቶችም ሲያልፉ ከቤት የመባረሬ ነገር እርግጥ ሆነ የእናቴ አንጀት ጨክኖ እንድወጣ ወሰነብኝ የተባልኩትን ከመቀበል ውጪ አማራጭ አልነበረኝም ያለቺኝን ጥቂት ልብስ ሰብስቤ ወደበሱፈቃድ ጋር ለመሄድ ተነሳሁ ካሁን ካሁን ተመለስ ትለኛለች ብዬ በብዙ ጠበቅኳት እሷ ግን ወይ ፍንክች ልቧ ደነደነ ይልቁንስ እህቶቼ በሀዘን ተሞሉ አይናቸው እምባ ቋጠረ እነሱን ባየሁ ቁጥር ውስጤ እርብሽብሽ ይላል በጣም ተላምጃቸዋለሁ ከዚህም የተነሳ አቅራቦታችን እየጨመረና ከበፊቱ አብልጬ እየወደድኳቸው ያለሁ መሰለኝ ከመሄዴ በፊት መለስ ብዬ ስምያቸው ለመሠናበት እንኳን እድሉን ሳላገኝ ቀረሁ ያጋደለውን በር ይለይልህ ብላ ጠረቀመችው እኔም የተዘጋ በር ማየቱ ሲሰለቸኝ እግሮቼን ለመንገድ አዘጋጀሗቸው ዘርጋ ዘርጋ እያረኩ ቅርዝዝ ብዬ እነበሱፈቃድ ደጃፍ ደረስኩ ዘው ብሎ መግባቱ ነውር መሠለኝ አለመግባትን መወሠን ደሞ መሄጃ ማደሪያ በሌለኝ ቦታ ወይ የጅብ እራት መሆን አልያም እጣዬ በረንዳ መሆኑ ታወሰኝ በመግባትና ባለመግባት መካከል ላይ ቆሜ ባለሁበት ቁጭ አልኩ የበሱፈቃድ እናት ውሀ ለመድፋት ከቤታቸው ወጣ ሲሉ ከተቀመጥኩበት አዩኝ " ዩሀንስ ምነው በር ላይ ተቀመጥክሳ አትገባም እንዴ ? ደሞ በእጅህ የያዝከው የምን ልብስ ነው ? "አሉኝ የምላቸው ጠፍቶኝ መሬት መሬት እያየሁ እንዳቀረቀርኩ ቀረው ያኔ የውሀ መድፊያውን እቃ አስቀምጠው ወደኔ ተጠጉ ፤ ቀርበውም በእጃቸው እራሴን እየዳሰሱ  " ዩሀንስ ምን ሆነሀል  ? እስቲ ንገረኝ እኔ እናትህ ማለት አደለሁ ለምን ትደብቀኛለህ ? አሉኝ እኔም " እናቴ ከቤት አባረረቺኝ ጴንጤ ሆንህ ብላ ፤ መሄጃ ስላልነበረኝ ወደናንተ መጣሁ ግን ደሞ ለመግባት ፈራሁ " አልኳቸው ለሰከንድ እንኳን ፊታቸውን ሳያጨልሙብኝ " ለምን ትፈራለህ ግባ እንጂ እዚሁ ከኛ ጋር እንደቤተሰብ መኖር ትችላለህ 



ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም ማንም በሌለህ ሰአት እንዴት ከንፈር መጠን የራስህ ጉዳይ እንልሀለን በፍፁም አናደርገውም አሁን በል ሀይለኛ ንፋስ እየተነሳ ነው ስለዚ ግባ " አሉኝ መልካምነታቸው ለኔ ተስፋ ሆነኝ የያዝኩትን ይዤ ወደ ቤት ውስጥ ገባሁ ማንም አልነበረም በሱፈቃድ የት ሄዶ እንደሆነ ባላውቅም እቤት ሳላገኘው ቀረሁ " ቁጭ በል ምንም ሀሳብ እንዳይገባህ እኛ የበላነውን እየበላህ እኛ የጠጣነውን እየጠጣህ ከኛ ጋር ትኖራለህ ከልጃችን ለይተን አናሳድግህም አንተ ከእንግዲ ከእግዚአብሔር የተሰጠኸኝ የአደራ ልጄ ማለት ነህ አንተም እንደ እናትህ እየኝ " አሉኝ በዚህ ግዜ ካይኔ እምባ ቀረረ " በጣም ነው የማመሠግነው በዚህ ሰአት እናንተ ባትቀበሉኝ የት እንደምሄድ አላውቅም ነበር እውነት ከልቤ ፈርቼ ነበር አሁን ግን ማረፊያ ስላገኘሁ ሌላው አያስጨንቀኝም ግን የበሱፈቃድ አባት ሲመጡ እና ሲያዩኝ ቅር አይላቸውም ማለት እሳቸው ሳይወስኑ እንድኖር ስለፈቀዱልኝ " ብዬ ጠየቅኳቸው ፤ አንደኛው ስጋቴ ይሄ ነበር " ኧረ እሱ እንደዚህ አያውቅም በተቃራኒው እንደውም ልቡንም ቤቱንም ከፍቶ ነው የሚቀበልህ እንደውም ቢችልና አቅሙ ቢፈቅድ ለወንጌል ተብሎ የተሰደደን ሠው ቢያኖር ደስታው ነው እኔ ካልኩህ ውጪ ምንም መጥፎ ቃል አይናገርህም እሱን እንደ አባት እኔን እንደ እናት በሱፈቃድን ወንድምህ እያየህ ትኖራለህ እናትህ ብትራራና ብትመልስህ ያኔ መሄድ ትችላለህ ካለዛ ግን ምንም ሳታስብና ሳትጨነቅ ቤታችንን እንደ ቤትህ ተመልክተህ መኖር ትችላለህ " አሉኝ እውነት እንዳሉኝም የበሱፈቃድ አባት ፊታቸውን ሳያጠቁሩ ተቀበሉኝ ቤታቸው ውስጥ ያለው መከባበር አስቀናኝ ሁሉም ደሞ በአንድ መንፈስ ሆነው እግዚአብሔርን በአንድነት ያመልካሉ መንፈሳዊ ቅናት ተሰማኝ ምናለ እኔና ቤተሰቤም እንዲ ብንሆን ብዬ ተመኘሁ ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
5.2K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 21:01:37 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፮
@yanetmasra

እመኑኝ አለችን ......
   የዛን ቀን ከዘፍጥረት ጀመርኩላቸው በመጀመሪያ ቃል እንደነበር ሁሉም ነገር የተፈጠረው እግዚአብሔር ይሁን ብሎ እንደሆነ ከሠኞ-እሁደ ከፋፍሎ በምድር ላይ ያለው ነገር እንደተፈጠረ ምድርን ካበጃጀ በሗላ በመጨረሻ ቀን እንደተፈጠርን ስለአዳም እና ስለሄዋን ፣ ሄዋንን ስላሳታት እባብ ፣ ከገነት ስለመባረራቸው ብቻ የዛን ለት ሠፊ ጊዜ ወስጄ አወራሗቸው በማህል ቀና ብዬ ሳያቸው የተመሠጡ ይመስላሉ " እና ወደዳችሁት ወይስ አልወደዳችሁትም ? " አልኳቸው መሠረት ቀጥላ " ይሄ የተፃፈው ነገር እውነት ነው ? ይሄ ምድር የተፈጠረው በ7 ቀን ውስጥ ነው ? እኛም ከአፈር ነው የተፈጠርነው እንዴ ? " አለቺኝ " አዎ ይሄ የእግዚአብሔር ቃል ነው ፤ የእግዚአብሔር ቃል ደሞ እውነት ነው ። እኛ ማድረግ የማንችለውን ማድረግ የሚችል ፍፁም አምላክ ነው በ7 ቀን ውስጥ ይሄን ሁሉ  ማድረግ ችሏል እኛንም በአምሳሉ ከአፈር አበጃጅቶ እስትንፋስን ሰጥቶናል " አልኩና ወደ ፍቅር ዞሬ " አንቺ የምትይኝ ነገር የለም ? " አልኳት " እኔ ስታነብልኝ ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ ነበር ምናልባት ሁሉንም ስላላነበብክልን ይሆን እንጃ እንጂ ለምን መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ እንደ መጥፎነት ይታያል ለምንስ ብዙ ሰው አያነብም ብዬ ሳስብ ነበር ምክንያቱም ካነበብክልኝ ውስጥ ሠይጣን የሚያደርግ ወይም እምነት የሚያስቀይር ነገር የለም እንደውም ታሪኩ በጣም ይስባል ፤ ግን ሠው አይወደውም ለምንድነው ? አለቺኝ " ለምን መሠለሽ ፍቅር እውነት ሁል ጊዜ አሸናፊ ስለሆነች ውሸት ሊደብቃት ይሞክራል ሆኖም ግን አንድ ቀን መውጣቷ አይቀርም ሰይጣን ኢየሱስን ሊጋርደው ይሞክራል ብዙ ህዝብ ደሞ በሠይጣን መንግስት ውስጥ ነው ያለው ወደ እግዚአብሔር መንግስት ለመግባት ደሞ ኢየሱስን አምኖ ንስሀ መግባት ያስፈልጋል " አልኳት




ግን ስለቃሉ ብዙ እውቀት ስለሌላቸው ያብራራልኛል ብዬ የምጠቀመው ቃል ጭራሽ ብዥታን እየፈጠረባቸው መሆኑን ተረዳሁ እንዳልኩትም " ኢየሱስና እግዚአብሔር ምንድነው ልዩነታቸው ? " ብለው ጠየቁኝ ስለዚ ከአዲስ ኪዳን መጀመር እንዳለብኝ እና በማውቀው ጥቂት እውቀት ኢየሱስን ላስረዳቸው አሠብኩ ታድያ ከዛን ቀን ጀምሮ እናታችን በማትኖርበት ሰአት እቤት ስኖር ከብሉይ እና ከሀዲስ ኪዳን እያደረግን መፅሀፍ ቅድስን ማጥናት ጀመርን ከቀን ቀን እነሡ ላይ ለውጥ እያየሁ መጣሁ ራሳቸውም መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ እና ቁጥርን ምዕራፍን መለየት እየተለማመዱ ነበር እኔም እንዲያነቡ ካለኝ ፍላጎት የተነሳ እኔ በማልኖርበት ጊዜ ካነበባችሁ የምትፈልጉትን እንድትገዙበት ሳንቲም እሰጣችኋለሁ " ብያቸዋለሁ የማገኘው ጥቂት ቢሆንም ለእናቴና ለእነሱ አብቃቅቼ እሠጣቸዋለሁ እነሱም መጀመሪያ አካባቢ ሳንቲሙን የማግኘት ፍላጎታቸው እየገፋፋቸው ያነቡና ያነበቡትን ክፍል ከተረዱት ጋር ጨምረው ይነግሩኛል ከጊዜ በኀላ ግን እንደ ቋሚ ስራ ወሰዱት ከሳንቲሙ ይልቅ ያልገባቸውን እንዳስረዳቸውና አብርያቸው እንዳጠና ይገፋፉኝ ጀመር እንደውም አንድ ቀን እንደ ልማዴ ሳንቲም ልሰጣቸው ከኪሴ ሳወጣ እንደማይፈልጉና መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ ለራስ እንጂ ጠቀሜታው ለማንም እንዳልሆነና ለራሳቸው ሲሉ ስለሚያነቡ ብር እንደማያስፈልጋቸው ነገሩኝ ፤ ከንግግራቸው ብስለትን አስተዋልኩ አሁን ቢያንስ መስመር ይዘዋል ሌላው በጊዜ ሂደት የሚቀጥል ይሆናል ብዬ ለውስጤ ነገርኩት ነፍሴ ሀሴት ስታደርግ ይሰማኝ ጀመር ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው ሗላ ሲያድግ ከዛ ፈቀቅ አይልም የሚባለው ነገር እውነት ነው ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
5.8K views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 19:01:36 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፭
@yanetmasra

በ14 አመቷ ይህን ማሰቧ እንድገረምባት አደረገኝ መለስ ብዬ የኔን እህት ፍቅርተን አሰብኳት እሷ በዚ እድሜዋ ይህን ታስብ ይሆን ብዬ አሰብኩ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ሁለቱንም እህቶቼ ምንም እንደማያውቅ ህፃን ልጅ ነው የማያቸው
   የዛኑለት እቤት ገባሁና ሁለቱንም ጠራሗቸው ትንሽ አጫወትኳቸውና እናቴ ስትወጣ ጠብቄ " መፅሀፍ ቅድስ አብረን ብናነብ ቅር ይላችሗል  " አልኳቸው የሁለቱም ፊት ተለዋወጠ " ምነው ?" አልኳቸው ለመናገርም ላለመናገርም ቃጣቸው ከተናገርን በሗላ ቢቆጣንስ ብለው የፈሩ መሠለኝ " ግድ የለም የመሠላችሁን መናገር ትችላላችሁ  " ብዬ ፈገግ አልኩላቸው ፍቅርተ ደፈር ብላ " እንዳንተ ጴንጤ ልታደርገን ነው መፅሀፍ ቅድስ እናንብብ የምትለን ደሞ እማዬ ብታይ ትገርፈናለች አንፈልግም " አለች  "ቆይ ያለቻችሁ ነገር አለ እንዴ " አልኳት
ፍቅርተ ለመደበቅ ፈልጋ " ኧረ ምንም አላለችም አለች " መሠረት ግን " ከዩሀንስ ጋር መጫወት ቀንሱ የሱን ጴንጤነት ያስተምራችሁ እና የሰይጣን መጫወቻ ትሆናላችሁ እኔም እናታችሁ አልሆንም በሰው ዘንድም የተጠላችሁ እና በፈጣሪም ዘንድ የተረገማችሁ ነው የምትሆኑት " ብላናለች አለች ፍቅርተም በአይኗ ተቆጣቻት ያኔ አትናገሩ ብላ እንደነገረቻቸው ተረዳሁ " እውነት ነው ፍቅርተ ?" አለኳት ፈራ ተባ እያለች " አዎ እማዬ በእምነት ዙሪያ ያለ ወሬ ካንተ ጋር እንዳናወራ እና እንዳንሰማክ አስጠንቅቃናለች " አለች " ቆይ ግን ለምን ? " አልኳት " የሰይጣን እምነት መከተል ስለማንፈልግ ነዋ " አለቺኝ " አሀ ሠይጣን እንዳትሆኑና እንዳትጠሉ ፈርተሽ ነው "አልኳት ጭንቅላቷን እየነቀነቀች የአዎንታ ምላሽ ሰጠቺኝ " ታድያ እንደሱ ከሆነ ለምን ከኔጋር ታወራላችሁ እናንተ እንደምታስቡት ከሆነ እኔም ሰይጣን ነኝ ማለት ነው ስለዚ ከሠይጣን ጋር አታውሩ " ብዬ አልኳቸው " እንዴ አንተማ ወንድማችን ነህ እንዴት አናወራህም እኛ ያልነው እምነቱን ነው " አለቺኝ መልሳ




" እኮ እምነቱ የሰይጣን ነው ካልሽ እኔ የሰይጣን ተከታይ ነኝ ማለት ነው ስለዚ አትቅረቡኝ " ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳሁ " እንዴ እንደሱ እኮ አደለም " ብለው እጄን ያዙኝ " ታድያ እንዴት ነው ? " አልኳቸው የሚሉኝ ጠፍቷቸው አንዴ ሰማይ አንዴ መሬት ያያሉ መልሰው አሳዘኑኝ " እሺ የፈለጋችሁትን ማሰብ ትችላላችሁ ግን ምንም ሳታውቁ በደፈናው አንድ ነገር ላይ አትፍረዱ መጀመሪያ ስለዛ ነገር ለማወቅ ፍላጎት ይኑራችሁ ስታውቁ የፈለጋችሁትን መናገር ትችላላችሁ ስለዚ በስርአት እናውራና ከዛ የፈለጋችሁትን ትላላችሁ እኔ ጴንጤ ሁኑ አላልኳችሁም መፅሀፍ ቅድስ አንብቡ እንጂ ቆይ እኔም እናንተም እግዚአብሔርን እናምን የለ ? አልኳቸው " አዎ " አሉኝ " ስለዚ እኔ የሰይጣን እምነት የምከተል ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔርን አልወደውም አላምነውም ነበር  ደሞ ሰው አንድ ነገር መጥፎ ነው ስላለ ይሀ ነገር መጥፎ ነው ማለት አደለም ጥሩም ነው ስላለ ጥሩ ላይሆን ይችላል ይሀን የምታውቁት በአእምሮአችሁ በማመዛዘን ነው ስለዚ መፅሀፍ ቅድስ ላንብብላችሁና ካልወደዳችሁት እተወዋለሁ ከወደዳችሁት ደሞ ሁሌ እናነባለን " አልኳቸው ሁለቱም ተስማሙ ግን ከፊታለው በድጋሚ ቅሬታ አየሁ "ምነው ? " አልኳቸው ወደ ፍቅር ዞሬ " እማ ብታውቅ ግን ትገለኛለች ባለፈው አንተን በርበሬ እንዳጠነችህ እኛን ብታጥነንስ ወይ ብትደበድበንስ " አለቺኝ እኔም " ስለሱ አታስቡ እማዬ ስትኖር ዝም ብለን እንጫወታለን ስትወጣ ደሞ እናነባለን ታድያ እንዳታውቅ ከፈለጋችሁ እናንተም ፀጥ ማለት ነው ያለባችሁ ለእናታችን ምንም አትነግሯትም ሁላችንም ዝም ካልን አታውቅም በዚ ትስማማላችሁ ? " አልኳቸው አሁንም ፍቅርተ ቀደም ብላ " እኔ እስማማለሁ መሲ ግን ብትናገርስ እሷ አፏ አይቋጥርም " አለቺኝ " ትናገርያለሽ እንዴ አልኳት " አልናገርም " አለቺኝ " ቃል ትገቢያለሽ ለሁለታችንም ? " አልኳት " እግዚአብሔርን ለማንም አልናገርም እመኑኝ " አለችን ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
5.7K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 14:50:00 ዝማሬ “ ልንቃ"
ዘማሪት ፀጋ ተስፋዬ
የተለቀቀው August , 2022
Size 3.6MB
ርዝመት 3Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
5.8K viewsedited  11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 21:00:08 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፬
@yanetmasra

ከእህቶቼ ጋር ያለኝ ቅርበት አባቴ ከሞተ በሗላ በትንሹም ቢሆን እየጨመረ መጥቷል እንዲያወሩኝ እንዲቀርቡኝ እድል እየሰጠሗቸው ነበር በዛ ወቅትም 17 አመቴ ሲሆን እነሱ ደሞ ፍቅርተ 14 መሠረት ደሞ 12 አመቷ ነበር እናቴ ስጋት ስለገባት እንጂ ከእነሱጋር ምንም ከዕምነት ጋር የተያያዘ ነገር ነግርያቸው አላውቅም ነበር ሀሳቡም አልነበረኝም ግን እናቴ ካለቺኝ በሗላ እንደውም ለምን አልነግራቸውም ብዬ አሰብኩ እናቴ ብነግራት እንደማትሰማኝ ግልፅ ነው እግዚአብሔር  ካልረዳት በቀር እነሱ ግን ገና አይምሯቸው በማህበረሰቡ ልማድና እይታ ስላልተወረሰ የምነግራቸውን ነገር ሊረድኝና ሁለት ነፍስ ወደ ጌታ ላመጣ እችላለሁ የሚል ሀሳብ ውስጤ ውስጥ ተፀነሰ ግን እንዴት የሚለው ነው ጥያቄው እናቴ ሳታውቅ እነሱን አግባብቼ እንዴት ነው የእግዚያብሄርን ቃል ልመግባቸው የምችለው እንዴትስ ብዬ ወሬውን ልጀምር ? እነዚህን ነገሮች በደንብ ማሰብ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል ።

   እንደ ጨዋታ አድርጌ ለበሱፈቃድ አዋየሁት እሱም  " እናትህ የእውነት አምርረው ከቤት የሚያስወጡህ ከሆነ የት እሄዳለሁ ? ፣ የት እገባለሁ ? ብለህ እንዳታስብ  እኔ ለወላጆቼ ነግሬ ከእኛ ጋር ትኖራለህ ቤት የእግዚአብሔር ነው አትጨነቅ የእህቶችህን ነገር ደሞ መላ እንፈልግለታለን በመጀመሪያ ግን አብዝተህ መፀለይ እንዳለብህ አትዘንጋ አንተን ያየ ፣ ያዳነ የጎበኘ ጌታ እነዚ ብላቴና እህቶችህንም እንዲጎበኝ ፀልይ ፤ በነገራችን ላይ እኔም ታናሽ እህት እንዳለኝ ታውቃለህ ? " አለኝ በፍፁም አላውቅም ነበር ነግሮኝም አያውቅም እቤታቸውም ስሄድ ከእሱና ከወላጆቹ በቀር ሌላ አብሯቸው የሚኖር እንኳን ዘመድ አልነበረም " ታድያ እህት ካለችህ የት ሄደች ለምን አብራችሁ አትኖሩም " አልኩት በጣም በመገረም ስሜት ውስጥ ሆኜ እሱም " አብራን ነበር የምትኖረው ይህችን 4 አመት ግን የእናቴ እናት ጋር ሄዳለች



ብቻዋን ስለሆነች አያታችን የምትኖረው ምህረት አብራት እንድትኖርና እንድታግዛት ወላጆቻችን የወሰኑትና እሷም የተስማማችበት ነገር ነው ለክረምት ግን ሁሌ እኛ ጋር ትመጣለች ደሞ በ1 አመት ብቻ ነው የምበልጣት በጣም የምግባባት እና የምወዳት እህቴ ነች ከሁሉም ነገሯ ብልሀቷ ያስገርመኛል " አለኝ "ለምን እናንተስ አያትህ ጋር አትሄድም ወይም ደሞ እናትህ ቢረዷቸው አይሻልም ለእህትህ በልጅነቷ ሀላፊነት ከሚሰጣት ደሞ ባለፈው ክረምት ሳትመጣ ቀርታ ነው ወይስ ሳላያት ቀርቼ ነው አልኩት ነገሮችን ከነ ምክንያትና ውጤታቸው ስር ድረስ ዘልቆ ለመረዳት ያለኝ ጉጉት እና ፍላጎት ጥልቅ ነው " ምን መሠለህ ዩሀንሴ የእናቴ እናት በጣም አክራሪ ኦርቶዶክስ ናቸው ባለቤታቸውም ቄስ ነበሩ እና እናቴ ጴንጤ ሆነች ብለው ልጄ አደለሽም አትድረሽብኝ አልደርስብሽም ተባብለዋል አባቷ በህይወት የሉም እና ከአያቴ  ጋር ያላት  ግንኙነት ጥሩ ስላልሆነ ሲያማቸው ልታስታምማቸው አብራቸው ሆና ልትረዳቸው ስለማትችል ይሄን ለማድረግ ያለው ምርጫ እህቴን መላክ ነው በነገራችን ላይ ይህን ሀሳብ ያመጣችው እራሷ ምህረት ናት አያቴ ሴት ልጅ እንደምትወድ እናታችን ስለምትነግረን ለምን የእሳቸውን እምነት የምከተል መስዬ አልረዳቸውም ? " አለች አባቴ ግን መንፈሳዊ ህይወቷ ላይ ጉዳት ያመጣል ብሎ ስላሰበ መጀመሪያ ላይ አልፈቀደም ነበር እሷም መልሳ " በዚ በኩል ስጋት አይግባችሁ ለጥቂት አመታት በስውር አመልካለሁ በዛላይ አያቴ ያን ይህል ስለማትቆጣጠረኝ ህብረት ለማድረግም ለመፀለይም ይመቸኛል " አለች እናትና አባቴም ተማክረው በመጨረሻ እንድትሄድ ወሰኑ አሁን ድረስ አያቴ በጌታ መሆኗን አታውቅም ግን  ለዛውም ብርቱ ነች በቃ ምን ልበልህ በልጅነቷ በሳልናት እህቴ ስለሆነች አደለም እንዲ የምልህ እና ባለፈው ክረምት አያቴን ትንሽ ስላመማት መምጣት አልቻለችም በአሁኑ ግን ትመጣለች ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ከመጣች አስተዋውቅሀለው " አለኝ ....ይቀጥላል

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
6.6K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 19:01:51 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፫
@yanetmasra

መቼም የማልረሳው ታድያ እናቴ መነጫነጮ አልቀረም "አባትህ ስለሞተ ምንም አታመጣም ብለህ ነው አደል የምልህን የማትሰማኝ ለነገር አሁንማ ለመድኩት እንኳን አንተ የሰፈሩ ሰው ሁሉ ባሏ ሞተባት ኑሮ አጎሳቆላት ብሎ አደል ንቆ ከሰው በታች ያደረገኝ አይ ጊዜ ስንቱን ያሳያል ዛሬ እንዲ መሆኔን አትይ ሌላው ቢቀር አንተ እንኳን ስማኝ አክብረኝ " ብላ ልታለቅስም አሻት በጣም ታሳዝነኛለች ጉዳቷን አልወድም በሌላ በምንም አይነት ሁኔታ ላሳዝናት አልፈልግም እንደውም ከሌላ ጊዜ በተለየ ለትምህርቴ ትኩረት መስጠት ጀመርኩ ምክንያቱም የኔ ደና ቦታ ላይ መገኘት የናቴንም ህይወት ደና ያደርገዋል ብዬ ማሰብ ጀመርኩ በስራም ቢሆን ከትምህርት ጎን ለጎን ጫማ በመጥረግ እናቴን ለማገዝ እፍጨረጨራለሁ እሷ ግን ይሄ አልታያትም ሁሉ ነገር ቀርቶባት መፅሀፍ ቅዱስ ባላነብና ጴንጤ ባልሆን ምኞቷ ነው ይሄ ደሞ ሌላ ፍርሀትና ጭንቀት ፈጠረባት በዛ ላይ የሠፈር ሰው በማያገባው እየገባ ልጅሽን እዚ አየሁት እዛ አየሁት ተቆጣጠሪው ፣ ቅጭው ፣ መጥፋቱ ነው ይሏታል ከሁሉ በላይ የሰው አፍ አላስቀምጥ አላት የናትነት አንጀቷም አላስችል እያላት እንዳልታሰር ፣ እንዳልመታ  ስትል ስጋት ያድርባታል እኔ ግን ምን ላርግ አንዴ የበራልኝን ብርሀን እንዴት ላጨልመው የቀመስኩትን የሰማሁትን እውነት እንዳላየ ሆኜ እውነት ማለፍ ብፈልግም እንኳን ማድረግ አልችልም በተለይ በዛን ወቅት አዲስ ክርስቲያን እንደመሆኔ መጠን የሚቀጣጠልብኝ እግዚአብሔርን የማወቅ እሳት እንዲሁ በከንቱ የሚጠፋ አልሆነም በዛ ላይ ከስር ከስር በሱፈቃድ ጋዝ ሲጨምርበት ቦግ ይላል ታድያ በዚ ሁኔታ ሳለን በወታደራዊው መንግስትና በአማኙ ማህበረሰብ ያለው



እንደ አይጥና ድመት መተያየት በዛው ልክ ፋመ በቅርብ የምናውቃቸው አማኞች መፅሀፍ ቅድስ ሲያነቡ በነበሩበት ወቅት በቀበሌ አመራሮችና በወጣቶች ተከበቡ በወቅቱ ከያዟቸው በሗላ መፅሀፍ ቅዱሳቸውን ሰብስበው አቃጠሉትና እንዲታጠኑት አደረጉ በዚ መልኩ ሊጎዶቸው ይሆን ወይ መከራው ሲበዛ እምነታቸውን እርግፍ አድርገው ይተዋሉ ብለው አስበው ይሆን ባላውቅም አንድ የገባኝ እውነት ግን ለወንጌል ተብሎ የሚከፈል ዋጋ ከስቃዬች ሁሉ በጣም የሚጣፍጥ ስቃይ ነው መከራው ሲበዛ የሚሸሽ ሳይሆን በተቃራኒው አንገቴን ለቢላ እያለ የሚያምነው አማኝ በዛ እኔም ብሆን ባለማወቄ በሱፈቃድን የተቆጣሁት እየፀፀተኝና ለምን ይሄን እንዳደረገ በደንብ አድርጎ እየገባኝ መጣ እየቆየ ግን እናቴ አስማሚያዬን ስታይ ጠነከረችብኝ " ወይ ኢየሱስህን ወይ እኛን ትመርጣለህ "አለቺኝ " የት መሄጃ አለኝ አንቺ እናቴ ካስወጣሺኝ ሌላ ማን ይቀበለኛል "ብዬ አይኖቿን ትኩር ብዬ አየሁት ሆዷን ባባባው ብዬ እሷም አይኖን ካይኔ እያሸሸች  " አንተስ ልጄ አደለህ የምልህን መስማት የለብህም ነበር ? ፤ ደሞ አንተስ ተበላሸህ አፈንግጠህ ወጣህ ግን እነዚህ ሁለት ምንም የማያውቁ እህቶችህን እንድታበላሽብኝ አልፈልግም ሰሞኑን ቁጭ አድርገህ የምታወራቸው ነገር አላማረኝም ያንተን መስመር እንዳይከተሉ ስጋት አለኝ ስለዚ ይሄ ውሳኔዬ ነው የሚያዋጣህን ምረጥ " አለቺኝ ከእህቶቼ ጋር ያለኝ ....ይቀጥላል

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
6.3K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ