Get Mystery Box with random crypto!

Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር C
የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር
የሰርጥ አድራሻ: @christian_mezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.45K
የሰርጥ መግለጫ

🗣እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብከዋለን!
ትክክለኛ የሆኑ የወንጌል አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረጉ፦
ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ምስክርነቶች፣ የሪቫይቫል ታሪኮች፣ ዝማሬዎች፣ መንፈሳዊ ዜናዎች፣ እንዲሁም መንፈሳዊነታቸውን የያዙ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ!
ለወዳጅ ጋደኞቻቹ #ሼር በማድረግ ይጋብዙ!
አስተያየት @ChristianMezmur_bot ላይ ፃፉልን✍
ሁሌም ከኛ ጋር ስለሆናቹ እናመሰግናለን!

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-11-02 19:00:12 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረ
ክፍል ፳፭
@yanetmasra

የዛን ሰአት የተናገሩኝ ንግግር ውስጤን ስርስር አድርጎ ገባ ልክ ነበሩ እንድልና የእናቴ ዋጋ እንዲገባኝ አደረጉኝ በፊት ለኔ የነበራትን አመለካከት እና ቀረቤታ አሁን ካላት ጋር አነፃፀርኩት የተገላቢጦሽ ሆነብኝ በፊት ለኔ መልካም እና እሩሩ ነበረች አሁን ግን በተቃራኒው እናት ሳትሆን የእንጀራ እናት ነው የሆነችብኝ ውስጤ ቢከፋባትም ልረዳት ሞከርኩ እሷ ግን እኔን እንደማትረዳኝ ግልፅ ነው እናቴ ግን ጌታን አምና የዳነች ቀን ደስታዬ የሚሆነው ወሰን አልባ ነው እኔ በመዳኔ ከተደሰትኩት በላይ እጥፍ ድርብ አድርጌ ነው የምደሰተው " እውነት ለመናገር እርሷ ያሰቡትን ያህል ጥቂትም ቢሆን አስቤ አላውቅም ነበር ። እንደውም እናቴ ሆና ይሄን ያህል ለምን ጨከነችብኝ ብትናደድብኝ እንኳን እንደዚህ መጨከኑ ለምን አስፈለገ ብዬ ከማሰቤ የተነሳ ቀን በቀን በተተካ ቁጥር ልቤ ውስጥ ቂም መቋጠሬ አልቀረም አሁን ግን የተጋረጠውን አይነ ልቦናዬን ገልጠውልኛል እሷም ብትሆን ያመነችውን እንዳምንና ያድነኛል የምትለው እንዲያድነኝ ካላት ፍላጎት የተነሳ ነው እውነት ስለመልካም ሀሳቦ እና ስለምክሮ አመሠግናለሁ " አልኳቸው "አይ አንተ! ይሄ ምስጋና የሚያስፈልገው ነገር አደለም ደሞ ማሰብ ያለብህ ከቤተሰብ በላይ አብዛኛው  ማህበረሰብ በእምነትህ ምክንያት እንደሚጠላህ በማወቅ አንተ ግን እነሱን መውደድ ነው ። እናትህ እኮ ግፋ ቢል ብትጮህብህ ከዛ ከዘለለም እንደ ልጅ ብትገርፍህ ነው ። ውጪ ላይ ያሉ አብዛኞቹ ህብረተሰቦች ደሞ ቢገሉህም ደስተኛ ናቸው ። ስንት መከራ በአማኙ ማህበረሰብ ላይ እንደሚያደርሱባቸው ላንተ አልነግርህም ምክንያቱም የአደባባይ ሚስጥር ስለሆነ ነው ታድያ የሚጠሏችሁን  ውደዱ ስለተባለ የሚጠሉህን ለመውደድ ዝግጅ ነህ እየደበደቡህ ትወዳቸዋለህ ? ቢሰድቡህና ሊገሉህ ቢሞክሩስ ትወዳቸዋለህ ? ይሄን ራስህን ጠይቀው መልስህ አዎን ከሆነ እውነትም አንተ



ወንጌል ገብቶሀል ክርስቶስን መስለህ ትኖራለህ ከዛ ግን ራስህ ላይ መስራት አለብህ ወንጌል ሊለውጥህ ይገባል ገና ከዚ የባሰ መከራ ከፊትህ ይጠብቅሀል ለዛ ደሞ ጠንካራ ሆነህ ማለፍ አለብህ በዚ መልኩ ለሞተልህ ፣ ዋጋ ለከፈለልህ ታማኝ ሆነህ ትገኛለህ " አሉኝ መልሶም ትካዜ ገባኝ የጠየቁኝን ጥያቄ እራሴን ጠየቅኩት እውነት እወዳቸዋለሁ ወይስ ጠላቶቼ ብዬ እጠላቸዋለሁ ? ሀጥያተኛ ሆኜ ሳለሁ ተወድጄ ተመርጬ ከዳንኩ በሗላ ሀጥያተኛ ብዬ ያልዳኑትን እጠላለሁ ወይስ የመስቀሉ ስራ የእውነት ገብቶኝ የሚጠሉኝን አብዝቼ እወዳለሁ ? መልሴ እኔንጃ አላውቅም ቢሆንም መሆን ያለበት ስለገባኝ እንደዛ አይነት ሰው ለመሆን እራሴ ላይ መስራት እንዳለብኝ ተረዳሁ " ዝግጅ መሆኔን ባላውቅም ዝግጁ ለመሆን እጥራለሁ " አልኳቸው "እንድትጨነቅ ብዬ ሳይሆን እንደዚህ ያልኩህ ነገሮችን በብዙ መልኩ እንድታይና እነሱንም በመልካም እንድትመለከት ካለኝ ፍላጎት የተነሳ ነው " ብለው ተነሱ እኔም መልሼ " አሁንም ሊወጡ ነው እነሱን ፍለጋ ? "አልኳቸው " አይ አይደለም በባዶ ሆድህ በወሬ ይዤህ እንደራበህ እርግጠኛ ነኝ የሚበላ ነገር ላዘጋጅልህ ነው " አሉኝ ከዛ ወደ ጓዳ ገቡ እኔም ተመልሼ ጋደም እንዳልኩ የለበስኩትን ልብስ ተጠቅልዬ አይኔን ለእንቅልፍ ጋበዝኩት ከምኔው እኔደሆነ ባላወቅኩበት ድብን ያለ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ የነቃሁት በሱፈቃድ እና አባት እቤት መጥተው ደህንነቴን ለማወቅ ከተኛሁበት ሲቀሰቅሱኝ ነው ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
2.1K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 11:40:29 #ተለቀቀ
ቃልኛ መንፈሳዊ መፅሔት
    ዘጠነኛ እትም
   በቃልቲዩብ የተዘጋጀ
7ሜ.ባ PDF ያውርዱት

●18 ጥያቄዎች
ለተወዳጇ ዘማሪት አይዳ አብርሀም
የስራ ባህልና ክርስትና
(በነቢይ መሳይ አለማየሁ)
ክርስትናችሁን ከወረት ጠብቁ
(በፓስተር ስንታየሁ በቀለ)
ትናንቱን የረሳ ትውልድ ፤ የባህልና ትውፊት ክስረት
(በቢንያም አዲሱ)
ጥሩ አድማጭ መሆን!
(በአቤኔዘር አለማየሁ)

እና ሌሎች . . .
... ለወዳጆቻችሁ ለአማኞች ፣ ለማያምኑ ሼር
  ለበፊት እትሞችን | ይሄን ይጫኑ |

         @KALTUBE
         @KALTUBE
         @KALTUBE
2.6K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 11:37:48 ዝማሬ “ ይነጋል "
ዘማሪት Hildana Shibabaw
የተለቀቀው October , 2022
Size 6MB
ርዝመት 6Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
2.3K viewsedited  08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 19:01:06 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ከፍል  ፳፬
@yanetmasra

"በል እንዳሻህ ጥራን ዋናው አንቱታህን መተውህ ነው አሁን አንተ ጋደም በል እኔ ወጣብዬ ትንሽም ቢሆን እነበሱፈቃድን አየት አየት አድርጊያቸው ልምጣ ስመለስ ደሞ አፍህ ላች የምታደርገው ነገር እሰራልሀለው " ብለውኝ ወጡ እኔም ብሆን እረፍት ለማድረግ ወደ ውስጥ ገባሁ የተቀጠቀጠው ቦታ ላይ እና የቆሳሰለው አካሌ ላይ ጥዝጣዜ እና ህመም ይሰማኛል ጋደም ያልኩበት ቦታ ላይ ሆኜ የት ሄደው ይሆን ብዬ አወጣ አወርድ ጀመር መቼስ እናቴ ጋር ይሄዳሉ ብዬ ተስፋ አላደረኩም እንደዛ ቢሆን ግን እጅግ በጣም መጥፎ ነገር ይፈጠራል ወይ እኔኑ መልሳ ደግ አረጉህ እሰይ እንኳን ተደበደብክ ትለኛለች አልያም ደሞ እኔን ! ብላ ነገሩን ወደነበሱፈቃድ ቤተሰቦች ትጠመዝዘዋለች እንኳንም ዘንቦብሽ ድሮንም ጤዛነሽ ይባል የለ እንዲሁም ከበሱፈቃድ እናት ጋር ተናቁራለች እንኳን ተደበደበ ተመታ ተብላ ሌላ ነገር እንዳታመጣ በውስጤ ተጨነቅኩ ፤የበሱፈቃድ እናትም ከወጡ ግማሽ ሰአት አለፋቸው ከዛ ግን በሩ ሲከፈት ተሰማኝ ባገኟቸው ብዬ በልቤ  በመመኘት አንገቴን ቀና አድርጌ ላያቸው ሞከርኩ ነገር ግን ብቻቸውን ነበሩ " ምነው አላገኟቸውም እንዴ ? " አልኳቸው " አዎ አላገኘሗቸውም የት ብዬ እንደምፈልገቸው ግራ ገባኝ ጭራሽ አየሗቸው የሚለኝም ጠፋ ለነገሩ ባልጠይቃቸው ነው የሚሻል የነበረው እንኳን አየሗቸው ሊሉኝ እኔን ሰው ብሎ ለጥያቄዬ መልስ የሚሰጠኝ አልነበረም እንግዲህ እግዚአብሔር በሰላም ያምጣቸው እንጂ በዚህ ምሽት የት ብዬ እፈልጋቸዋለሁ " አሉኝ  እኔም በልቤ ሳስብ የነበረውን ጠየቅኳቸው " መቼስ ጠፋ ብላችሁ ለእናቴ አልጠየቋትም አደል ፤ ማለቴ ጠፋብለው ነግረው ወይም አይተሽዋል ብለዋታል ?" አልኳቸው " አይ ልጄ ልጠይቃት ብዬ ካንዴም ሁለቴ ሄድኩና ተመለስኩ



መጀመሪያ ይፈልጉህና ከዛ ካልመጣህ እንጠይቃቸዋለን ብዬ ተውኩት አንተም ብትሆን ሳትነግረን እዛ ታመሻለህ ብዬ አላሰብኩም እሷም ብትሆን መጥፋትህን ሰምታ እንዲሁ እንደ ዋዛ ዝም አትልም መናገር እንኳን ቢኖርብኝም ነገሮችን አትረዳም ብዬ ዝም አልኳት " አሉኝ ለነገሩ ልክ ናቸው ሌላ ግር ግር ቤት ውስጥ መፍጠር ነው "ልክ ኖት እንኳን አልነገሯት ብትሰማም ለውጥ የለውም ለችግሩ መፍትሄ ሳይሆን ሌላ ችግር ነበር የምታመጣው " አልኳቸው እሳቸውም ጠጋ ብለው " እናትህ ለምን እንዲ እንደምትሆን ታውቃለህ ? በጣም ስለምትወድህ ነው ባሏ ሞቶባት ስትጎዳና ስታዝን አለኝ የምትለው አጋዧ አንተ ነበርክ ታድያ እሷ ወደማትፈልገው ነገር ስትገባና ስታጣህ ምን ይሰማት ይመስልሀል ባሏ ሞቶ ልጆ ከሷ ተለይቶ ልቧ በጣም ይጎዳል ስለኢየሱስ ስላልገባት እሳት ውስጥ የገባህ ፣ የምትሞት ፣ ሀጥያተኛ የሆንህ ከሀዲ አድርጋ ነው የምትመለከትህ ይሄ ደሞ እንዲሆን እንኳን እናት ለልጇ ማንም ለወዳጁ አይመኝም ላንተ መልካም ነገር ከመመኘት አንፃር ጉዳትህን አትፈልግም አሁን ያለህበት ነገር ደሞ ጉዳት ይመስላታል ስለዚህ ታዝናለች ሀዘኗን ልትረዳት ስላልቻልክ በብስጭትና በቁጣ ታወራሀለች የልቧን ጩኸት ነው አንተ ላይ የምታስተጋባብህ ትዳሯም ቤቷም ተበተነ በዚህ ሰአት እህቶችህን እንድትቆጣጠርና እሷንም እንድትደግፋት ትፈልጋለች ይሄ ግን ሊሆን አልቻለም በእሷ ቦታ ሆነህ ብትመለከታት ሀዘኗ ልክ ነው ባንተ ቦታ ሆና ልትረዳህ ስላልቻለች ለእናትህ መዳን አብዝተህ ፀልይላት ግን መቼም ቢሆን እንደ ክፉ አይተህ እንዳትጠላት እንደውም ከጎኗ ሁነህ ባስፈለጋት ሰአት ከጎኗ ተገኝ እየጨቆነችህም ቢሆን መልካም ሁንላት ከፍቅሯ የተነሳ ነው ቁጣዋን የምታሳይህ " አሉኝ ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
3.5K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 19:01:00 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፳፫
@yanetmasra

" ቀኔ መጥፎ ነበር ከትምህርቴ ቤት ልጆች ጋር ተጣልቼ እንደዚህ አድርገው ለቀቁኝ ነገር ግን መንገድ ላይ መሄድ አቅቶኝ ወድቄ ሳለሁ የሱ ቤተሰብ የሆነች አንዲት ሴት አግኝታኝ ቤቷ ወስዳ ተንከባከበቺኝ ራሴን ስቼ ከወደቅኩበት ሰአት ጀምሮ እስካሁን ድረስ እነሱ ጋር ቆይቼ ስነቃ ወደናንተ መጣሁ እንደምትጨነቁ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ ነገር ግን ምንም ማድረግ አልቻልኩም ያለኝ አማራጭ ቶሎ መምጣት ነው በጣም ይቅርታ " አልኳቸው " ዋናው መምጣትህ ነው ግን አልተረፍክም እኮ ፊትህ ራሱ ብልሽትሽት ብሏል እኔ አፈር ልብላለህ ካለወትሮህ ስትቆይ ጊዜ ደብድበውት ይሆን ብዬ መጠርጠሬ አልቀረም ነበር ልቤ ራሱ አላረፈም ግን ምን ልሁን ብለው ነው እንደዚህ ያደረጉህ በትምህርት ቤት ጉዳይ ነው ወይስ በዚ በሀይማ..." አላስጨረስኳቸውም " እህ እያመመኝ ነው ንፋሱ ሲነካኝ ወደ ቤት እንግባና እናወራለን " አልኩ አዬ የኔ ነገር ሀሳቤ ተበታትኖ እደጅ መሆናችንንም ረሳሁት ና ግባ ልጄ " አሉኝ ሊሸኘኝ የመጣው ልጅ ተመልሶ ስላልሄደ ወደ ቤት እንዲገባ ብንጠይቀውም ስለመሸ መሄድን መረጠ እኛም አላስጨነቅነውም አመስግነን ተሰናበትነው ። የተመታሁበትን ምክንያት እሱ ፊት ማውራት ስላልፈለኩ ነበር ወሬውን ያቋረጥኳቸው እዛ ስጠየቅ ከተማሪ ጋር ተጣላሁ ብዬ እዚ ደሞ በሀይማኖት ምክንያት ነው ብል ውሸታም መስዬ መታየት ነው እሱን ደሞ አልፈለኩም ከዛ በሗላ ግን የተፈጠረውን አንዳች ሳላስቀር ነገርኳቸው የምር አለቀሱ በጣም ደነገጥኩ በሱፈቃድ እና አባቱ ሲመቱ ጥልቅ ስሜት ቢሰማቸውም ከአይናቸው ግን እንባ አልፈሰሰም ነበር በኤ ምክንያት ግን ሲያለቅሱ በጣም ተደናገጥኩ " ለምን ያለቅሳሉ ደና እኮ ነኝ ፤ ብዙ የተጎዳሁ መስሏችሁ ነው እንዴ ? " አልኳቸው ትክዝ ብለው " አዬ ዩሀንስ ምኑን ደና ሆንህና ደና ነኝ ትላለህ ደና አለመሆንህን ይኸው እያየሁት ደሞ ማልቀሴ አሳስቦህ ከሆነ ስለኔ አታስብ ከሆዴ ያጠራቀምኩት ብሶት ግንፍል ብሎብኝ ነው



ባለፈው ባለቤቴ እና በሱፈቃድ ተደበደቡ እሱ አለፈ ዋናው ደና መሆናቸው ነው ብዬ ራሴን ፅናናሁ መጎዳቴን ፣ ማዘኔን አይታችሁ እንድትደክሙና እንድታዝኑ ማድረግ አልፈለግኩም ዛሬ ግን አንተ እንዲ ሆነህ ሳይህ አላስቻለኝም መከራችን በዛ ፤ ጥላቻቸው ያለ ልክ እደገፋ መጣ በኔና በባለቤቴ ላይ የፈለጉትን ቢያረጉ አይገርመኝም በልጆች ላይ ግን ይሄን ያህል ጭካኔ ሲደረግ በጣም ያሳዝናል ግን ብከፋም ፣ ባዝንም ምንም ብሆን እግዚአብሔር ከጎኔ መሆኑን መቼም አልረሳም ከዚ መከራና ጭንቀት አንድ ቀን ይገላግለናል አምናለሁ ቃሉና የተናገረው ነገር አንድ ቀን እውን ይሆናል " አሉኝ አይናቸውን ቡዝዝ አድርገው በሀሳብ ማዕበል ተዋጡ ጭልጥ ...አሉ ዝም ብዬ ሳያቸው ቆየሁና በማህላችን ያለውን ዝምታ ለመገርሰስ ስል "በሱፈቃድ የት ሄዶ ነው እስካሁን ያልመጣው አባቱም ቆዩ እንዲ አያመሹም ነበር " አልኳቸው "ውይ !ውይ ! ሞት ይርሳኝ አንተኑ ፍለጋ እንደወጡ አልተመለሱም አዬ አሁን የት ብዬ ልፈልጋቸው ወይ እስኪመጡ መጠበቅ ነው እንጂ ...ቆይ ግን እኔምልህ ብዙ ጊዜ እነግርሀለሁ ብዬ አስብና እረሳዋለሁ ለምንድነው አንቱ እያልክ የምትጠራን በዛ ላይ የበሱፈቃድ እናትና አባት እያልህ ነው የምትጠራን እኛ አደለንም አላልን የውጭ ሰው ብትሆን እሺ እንደ ቤተሰብ እየኖርን ግን እንዲ ማለቱ ደግ አይደለም አንቱታህን ተውና ብትፈልግ እማዬ አልያም እቴቴ በለኝ እሱንም ቢሆን አባዬ ወይም ያሻህን ስም አውጥተህ በለው አይከፋውም " አሉኝ " እሺ እርሶን እቴቴ እሎታለሁ እሳቸውን ደሞ ጋሼ ብላቸው ይሻለኛል አንቱታውን ግን ባንዴ መተው ይከብደኛል ቀስ ብዬ እተወዋለሁ " አልኳቸው ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
2.5K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 19:00:16 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፳፪
@yanetmasra

" ልጄ ተነሳህ እንዴት ነህ ?" አለችኝ።ጭንቅላቴን እየነቀነቅኩ ደና መሆኔን ገለፅኩላት ቀጥዬም " የት ነው ያለሁት እናንተ እነማን ናችሁ?" ብዬ ጠየኳት እሷም ከገበያ ስመለስ ወድቀህ አገኘሁህ ክፉኛ ተጎድተህ ስለነበር ወደ ቤት አስገብተን ቁስልህን ጠራረግንልህ። ማነው ግን እንደዚ ጨክኖ የደበደበህ ሰው በሰው ላይ እንደዚ መጨከን ይከብዳል።አለችኝ እኔም ትምህርት ቤት ከልጆች ጋር በትንሽ ነገር ተጋጭተን ዛሬ የአመቱ መጨረሻ መዝጊያ ስለሆነ እንደዚ አርገው ደብድበውኝ ሄዱ። አልኳት ...."እኔን! ምን አይነት ጨካኝ ልጆች ናቸው ይሄን ያህል ምን ብታደርጋቸው ነው!?" አለችኝ። እውነቱን መናገር አልመረጥኩም እሷ ምን መሆኗን በምን አውቃለሁ....ጴንጤ መሆኔን ብታውቅ ኖሮ እንኳን ልትንከባከበኝ ልትረዳኝ ቀርቶ እሰይ ይበሉህ ብላኝ ልትሄድ ትችል ነበር ማን ያውቃል። ያው ከጥያቄው ግን መሸሽ ስለማልችል "... ፈተና እንዳስኮርጃቸው ጠይቀውኝ ሳላስኮርጃቸው ቀርቼ በዛ ቂም ይዘውብኝ ነው ዛሬ እልሀቸውን የተወጡብኝ እኔ ደግሞ ብቻዬን ነኝ እነርሱ ከአምስት ያልፋሉ።ሳልችላቸው ቀርቼ እንደዚ ተጫወቱብኝ" አልኳት። አጠገቧ ያለችው ልጅ ቀደም ብላ " እውነት ነው ሰርተፍኬቱን ሳየው ነበር አንደኛ ነው የወጣው ጎበዝ ልጅ ነህ ደግሞ የምን ማስኮረጅ ነው ደግ አደረግክ። ዝም ብለው አመቱን ሙሉ ሲዘሉ ይከርሙና ልክ የፈተና ቀን ይጉረጠረጣሉ። የሞቱ። አንተ ቆይ ለምን ለአስተማሪ አትናገርም እንደዚ ያደረጉህን ልጆች ጠቁም ካልሆነ ቤተሰብህ ጋር ሄደህ መናገር ነው አንተን ባይሰሙህ እነርሱን ይሰማሉ" አለችኝ። ቤተሰብ ስትል ቤተሰቦቼ ትዝ አሉኝ አሁን በዚ ሰአት ምን እያሰቡ ይሆናል ብዬ ተጨነቅኩ። ወደ በሩ አይኔን ሳማትር ጨላልሟል በፍጥነት ከተኛሁበት ተስፈንጥሬ ተነሳሁ



ግን አነሳሴ ልክ ስላልነበር ጎኔ አካባቢ የተመታሁት ቦታ ላይ ወጋኝ ህመሙ አየለብኝና መልሼ ተቀመጥኩ "እንዴ ምን ሆነህ ነው ?ምን ነካህ የማይሆን ነገር አወራሁ እንዴ ፤ ከና ከመናገሬ ቤቱን ጥለህ ለመውጣት ቸኮልክሳ " አለቺኝ የሁሉም አይን እኔ ላይ ሆነ በሌላ በኩል ደሞ የህመሜ ምክንያት ትንሽም ቢሆን ያስደነገጣቸው ይመስላል " ኧረ አንቺ ምንም አላደረግሽኝ ድንገት ቤተሰብ ስትዪ ቤተሰቦቼ ትዝ ብለውኝ ነው ጠዋት የወጣሁ እስከማታ ሳልገባ ስቀር ስንት ክፉ ክፉ ነገር ያስባሉ ብዬ ፈርቻለሁ ደሞ ሰማዩም ጠቋቁሯል ቶሎ ካልሄድኩ ልባቸው አያርፍም ይሄኔ እዛ እየተፈጠረ ያለውን ነገር የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው ስለዚህ ልሂድ ስላደረጋችሁልኝ ነገር በጣም አመሠግናለሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ባይሆን ሌላ ቀን መጥቼ እጠይቃችሗለሁ " ብዬ ለመሄድ ተነሳሁ መጀመሪያ ያወራችኝ ሴትዬ " ቆይ እንጂ ከሄድክም ብቻህን አትሄድም በዚ በማታ አሞህ ብቻህን እንድትሄድ አላደርግህም " ማነህ አብርሀም እስከሰፈሩ ሸኘው "ብላ ከጓዳ አንድ ሰው ጠራች ልጁ ወደ ሀያዎቹ መጀመሪያ ይገመታል ቁመቱና ሰውነቱ ሲታይ የሰማይ ስባሪ ያህላል እንኳን ሰው አደለም ከሱ ጋር ሆኜ ንፋስ አይነካኝም ። እንዳለችው ከልጁ ጋር መንገድ ቀጠልን ። ዝምታው በጣም ያስፈራል ! እቤት እስከምንደርስ ድረሰ አንድ ቃል አልተነፈሰም ለነገሩ እኔም ብሆን ህመሜን እያዳመጥኩና ቤተሰቦቼ ምን ያስባሉ የሚለውን እያንሰላሰልኩ ነበር ገና ወደደጃፉ ከመጠጋቴ የበሱፈቃድ እናት "ዩሀንስ ! ዩሀንሴ !  "  እያሉ ወደኔ መጥተው ከእቅፋቸው አስገቡኝ " የት ሄደህ ነው ? ፊትህ የቆሳሰለው ከማን ጋር ተጣልተህ ነው ? አንተንም ደበደቡህ እንዴ ...? " ብዙ ነገር አሉ ፤ እንደ እውነተኛ  እናት እንስፍስፍ አሉልኝ ። በሳቸው ዘንድ እንዲ መወደዴ አስደሰተኝ ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
3.8K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 19:00:46 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፳፩
@yanetmasra

ሲቆይ የተረሳ ቢመስልም መሆኑ የማይቀር ሆኖ የአመቱ መጨረሻ ላይ ለመዝጊያ ፕሮግራሙ ድምቀት ብለው ይሁን ወይም ደሞ ጥላቻቸው ገንፍሎ መቋቋም ስላቃታቸው መሆኑን ባለውቅም ከበር ሊደበድቡኝ አድፍጠው ጠበቁኝ ገና ሳያቸው መትረፌን ተጠራጠርኩ አንዴ ብቻ ወደ ሰማይ ቀና ብዬ " ጌታ ሆይ ነፍሴን ተቀበላት" አልኩ መመለስ የማልችልበት  ሁኔታ ውስጥ ሆኜ እግሬን ለመንገድ አዘጋጅቼ ያላየዋቸው  በመምሰል  ለማለፍ ጣርኩ ግን አልተሳካልኝም አንደኛው ከመሀከላቸው ተስፈንጥሮ መቶ ትከሻዬን ነካ አደረገኝ እየቀፈፈኝ ዞርኩ ማንነትን በሚያስረሳ ቦክስ እንዴ ሲለኝ ከመሬቱ ተጣበኩ  አፍንጫዬም አለመሰበሩ እግዜር ሲረዳኝ ነው። ታድያ በዛ ቦታ  ሆኜ ከአፍንጫዬ የሚፈሰው ደም ሳስተውል በሱፍቃድ በሀሳቤ ውልብ አለ ባለፈው ለካ ወዶ አይደለም "ደና ነኝ ከአፍንጫዬ የወጣ ንስር ነው "ያለኝ ባንዴ ደሙያበሻቅጣል እነሱም የክፋታቸው ክፋት በዛ አልበቃ ብሏቸው በእግራቸው እንዴ ጀርባዬን ፣ ከዛ ሆዴን ፣ እግሬን ደስ ያለው ደግሞ እጄን ደገም ደገም አርገው   በመዘንዘር ተረባረቡብኝ ካላማጋነን የሞት ደጃፍ አድርሰው መለሱኝ ብል ውሸት አይሆንብኝም በዛ ላይ እየተደበደብኩ መልስ እንድመልስላቸው ጥያቄ አይሉት ሀሳብ በንግግራቸው ያንፀባርቁብኛል " ይሄ በሱፍቃድ የት ሄዶ ነው ? አመለጠን ማለት ነው ? እንጂ ካንተ በላይ ዋናው እሱ ነበር መቅመስ የሚገባው የት አባቱ ሄዶ ነው " ይሉኛል
ግራ ገባኝ የነሱን ጥያቄ ልመልስ ወይስ ህመሜን ላዳምጥ ደግሞ ስሙን ማወቃቸው ገረመኝ በዚህ አይነት የኔንም ያቁታል ብዬ ደመደምኩ ከዛን ለጠየቁኝ ነገር መልስ ሳልሰጣቸው ቀረሁ  ሆኖም ግን አልተውኝም " አንተን አይደል የምለው " ብሎ አንዴ በሀይል ጀርባዬን ሲመታኝ አይኔ እንደፈጠጠ "እኔጃ አላውቅም" ብዬ መለስኩለት እሱም "ያመለጠ መስሎታል ሂድና ቀንህን ጠብቅ አይቀርልህም ብለህንገረው አንተም ደግሞ አላርፍ ካልክ በዚ አያበቃም እንደግምሀለን" አለኝ



ጥፋቴ ምን እንደሆነ ባላውቅም እሺ አልኳቸው። በዛን ሰአት እውነት ግን በሱፈቃድ የት ሄዶ ነው ብዬ አሰብኩ ምክንያቱም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አብሮኝ ነበረ። ብቻ አንድ የክፍሉ ልጅ ጠርቶት መጣሁ ብሎኝ እንደሄደ አስታወስኩ ትረፊ ያላት ነፍስ መውጫዋና ማምለጫዋ አይታወቅም ይሄ ልጅ ምክንያት ሰጥቶ ባይጠራው ኖሮ ይሄኔ ከጎኔ ወድቆ አየው ነበር ብዬ አሰብኩ። ደሞ በሌላ በኩል መልሶ ዛሬም ቢመታ ምን ያህል ያሳዝናል ብዬ ራሴው አዘንኩለት ግን ያም ሆነ ይህ የባለፈውን ህመሙን እና ስቃዩን ቀመስኩለት። ውልቅልቅ አድርገውኛል። ደሞ የጠበቁኝ ቦታ ጭር ያለ በመሆኑ ማንም አይቶ ሊያነሳኝ የሚሞክር አንድም ሰው ጠፋ መጨረሻዬ እዚሁ ወድቆ መቅረት መሆኑን ሳስብ ለራሴ ራሴው ደጋፊ ሆኜ እግዚአብሔር እንደሚያግዘኝ እያሰብኩ ተነሳው። ልክ እንደ ሰከረ ሰው ወደዚ ወደዛ እንደ ንፋስ እየተወዛወዝኩ ቀኙ እጄ የተመታው ሆዴን ደግፎ ግራው ደግሞ ከትምህርት ቤት የተሰጠኝን የውጤት መስጫ ካርድ በደም እንጥብጣቢ ማህተም የተደረገበት እንደመሰለ ይዤው ጉዞ ቀጠልኩ ለስሙ ሲታይ አንደኛ ነበር የወጣሁት የነበሱፈቃድ ቤት ከኛ ቤት በተሻለ ለጥናት ስለሚመች ውጤቴ ከበፊቱ ይበልጥ ተሻሽሏል እናቴ ይሄን ብታይ ደስታዬ ነበር። ግን ሳያድለኝ ቀረ።

  መንገዴ ረጅም ሆነብኝ ብሄደው ብሄደው አላልቅ አለ። ከሌላው ቀን በተለየ መንገዱ ላይ መንገድ የተጨመረ እስኪመስለኝ ድረስ አሰለቸኝ። በዛም ላይ በዛ ፍጥነቴ ህመሜ ተጨምሮ የማያልቅ ሆነ በመጨረሻም ግን ተዝለፍልፌ ወደቅኩ።... ከደቂቃዎች በኋላ ስነቃ ራሴን ያገኘሁት ሰዎች ቤት ነበር። በግራና በቀኝ ከበው ያዩኛል ደሜ ከፊቴና ከእጆቼ ተጠርጓል ሊረዱኝ እንዳመጡኝ ብጠረጥርም እንዴት የሚለው ግን ጥያቄ ፈጠረብኝ ወዲያው አንዲት ሴትዮ.... ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
4.5K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 21:03:15 አንብባችሁ ለማታውቁ አንብቡ በጣም ብዙ የምትማሩበት እና በህይወታችሁ ብዙ የአመለካከት ለውጥ እንደምታመጡ እርግጠኞች ነን ። ተባረኩ

4.9K views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 21:01:37 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፳
@yanetmasra

ከአእምሮ አውጣ ብለው ተቆጡኝ እኔም መልሼ ብሄድ የት እንደምሄድ እንኳን አላውቅም ነገር ግን በእናቴ ስራ እጅግ አፍርያለሁ እያዋረደቻችሁ እየተመለከትኩ ምንም እንዳልተፈጠረ ማስመሰል ለኔ ከባድ ነው የሚሆንብኝ " ብዬ መለስኩላቸው  መስሎህ ነው እንጂ አንተ ባትመጣም ለኔ ጥሩ አመለካከት የላትም ስለዚ ኖርህም አልኖርህም ልትወደኝ አትችልም ባንተ ምክንያት አደለም የሌለ ነገር እየፈጠርክ አትታወክ ድጋሚ እንዲ ካልከኝ ግን ከናንተ ጋር መኖር አልፈልግም አልተመቻችሁኝም እንዳልከኝ ነው የምቆጥረው ያኔ መብትህ ነው መውጣት ትችላለህ " አሉኝ ምንም እንዳልል አፌን አዘጉኝ እንኳን ላይመቹኝ ይቅርና የበዛ መልካምነታቸው ሠው መሆናቸውን እያጠራጠረኝ ነው ። የዛኑ ቀን ወደ ቤተሰቦቼ ቤት ሄድኩ እናቴ አልነበረችም ያሉት እህቶቼ ነበሩ ከእነሱ ጋር እያወራሁና እየተጫወትኩ እናቴን መጠበቅ ጀመርኩ እሷም ትንሽ ብቻ አስጠብቃኝ መጣች ገና እኔን ከማየቷ ፊቷ ድምን ሲል ታየኝ " ደሞ ምን ቀረኝ ብለህ ነው የመጣኸው ? እቤቴስ ማን ግባ አለህ ? እናንተስ ብትሆኑ አታስገቡት ብያችሁ አልነበር ለምን አስገባችሁት ነው ወይስ ትዕዛዜን ማክበር ተዋችሁ " ብላ አፈጠጠችባቸው ከመፍራታቸው የተነሳ እምባቸው ቅርር አለ እነሱን ተያቸው አላስገባህም ማለት ስላልቻሉ ነው እኔም ደሞ ላወራሽ ስለፈለኩ ነው የመጣሁት ከእቤት ውጪ የት ላገኝሽ እችላለሁ ልጠብቅሽ የምችለው እዚ ስለሆነ ነው ይቅርታ ግን ማውራት አለብን " አልኳት "ጭራሽ ልታዘኝ እየሞከርክ ነው አጅሬው ፤ ደሞ ስለምን ልታወራኝ መጣህ " አለቺኝ ቤቱን ቃኘት አረኩት እህቶቼ አሉ እነሡ ፊት ርዕሱን ማንሳት ባልፈልግም ግቡ የምላቸው ትርፍ ክፍል ስለሌለ እዛው እንዳሉ " ለምንድነው የበሱፈቃድን እናት በሠው ፊት የምታዋርጃቸው አንቺ ከቤት ስታባረሪኝ እና መሄጃ ሳጣ ሊያስጠጉኝ ቤታቸውን ከፈቱልኝ እንጂ ምን አደረጉኝ እና ነው ከቤት ያስወጡኝ ይመስል



እንደ ሀጥያተኛ ሠው ፊት የምታስኮንኛቸው ለምንስ ከእድር እንዲባረሩ ሰውን አሳመፅሽባቸው አሁን ይሄን ስራ እግዚአብሔር ይወደዋል ?.." ሌላውን ቃል እንድቀጥል ፋታ ሳትሰጠኝ " እንዴ ጭራሽ ብለህ ብለህ ልትቆጣኝ መጣህ ና ደብድበኝ እሱ ነው የቀረህ ምንስ ብል ምን አገባህና ልትናገረኝ መጣህ ወይስ ያቺ ክብረ ቢስ ሴትዬ ሂድና ስደባት ብላህ ነው የመጣኸው " አለቺኝ " እማ እንዴት እንዲ ትያለሽ እኔ በምን አቅሜና ህሊናዬ ነው አንቺን የምሰድብሽ እሳቸውም ቢሆኑ ሂድና ተናገራት አላሉኝም እራሴ ስለፈለኩ ነው ላወራሽ የመጣሁት ካለ ስራቸውና ካለ በደላቸው  እንዳገለላችሗቸው ሰምቻለሁ ለዛ ደሞ ዋናዋ አንቺ ስለሆንሽ እንድትተይ ልጠይቅሽ ነው ፤ እጅግ በጣም ፈጣሪ የሚጠላውን ነገር እያደረግሽ ነው አልገባሽም እንጂ ከእሳቸው ጋር ሳይሆን ከፈጣሪ ጋር ነው እየተጣላሽ ያለሽው ስለዚ እባክሽ ልለምንሽ ተያቸው መናገርም ፣ መደብደብም ፣ ልታደርጊ የምትፈልጊውን ነገር ሁሉ እኔን አድርጊኝ እሳቸውን ግን ተያቸው " አልኳት የበሱፈቃድ እናት ያረጁ ሆነው ሳይሆን ለአክብሮት ነው አንቱ የምላቸው በእድሜ ግን ከእናቴ በጥቂቱ ብቻ ቢበልጡ ነው ። " ሟሟና እንደ በረዶ ደሞ እማ ይላል እንዴ ገና ከሰፈሩ እንድትወጣ ነው የማደርጋት ገና ምን አየህና ነው የምታሞጠሙጠው ጨርቋን አስጥዬ ካላሳበድኳት ሠው አትበለኝ እንደውም በጊዜ መኖሪያሽን ፈልጊ በላት አንተም ብትሆን ከእንግዲ ደጄ እንዳትደርስ ሾካካ በል ውጣልኝ " ጥንብርኩሴን ከውጥታ እያመናጨቀች ከቤቱ አስወጣቺኝ እናቴ በጣም ብሶባት ነበር ከቀን ወደቀን ነገረኛ እየሆነች ነው....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
4.8K views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 20:56:20
የሚጣፍጥ ስቃይ
Anonymous Poll
43%
እከታተላለሁ በጣም ነው የምወደው
10%
አልፎ አልፎ አነባለሁ
47%
አንብቤው አላቅም
309 voters4.1K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ