Get Mystery Box with random crypto!

Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር C
የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር
የሰርጥ አድራሻ: @christian_mezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.45K
የሰርጥ መግለጫ

🗣እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብከዋለን!
ትክክለኛ የሆኑ የወንጌል አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረጉ፦
ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ምስክርነቶች፣ የሪቫይቫል ታሪኮች፣ ዝማሬዎች፣ መንፈሳዊ ዜናዎች፣ እንዲሁም መንፈሳዊነታቸውን የያዙ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ!
ለወዳጅ ጋደኞቻቹ #ሼር በማድረግ ይጋብዙ!
አስተያየት @ChristianMezmur_bot ላይ ፃፉልን✍
ሁሌም ከኛ ጋር ስለሆናቹ እናመሰግናለን!

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-11-19 19:44:24 ዝማሬ “ ኢየሱስ "
ዘማሪት Ayda Abraham
የተለቀቀው Nov, 2022
Size 4.7MB
ርዝመት 5Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
7.4K viewsedited  16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 19:44:24

7.4K views16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 19:33:36
ቀጣይ ክፍል ምሽት ሶስት
Anonymous Poll
87%
ይለቀቅ
13%
አይ
174 voters6.9K views16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 19:31:25 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፴፯
@yanetmasra

እሷን የመለሱ እየመሰላቸው ጭራሽ መከራዋን አበዙት ት/ቤት ተምራ ብትመጣም ቤት ውስጥ ያለው ሀላፊነት እሷ ላይ ወደቀ ቤት ውስጥ ካሉ ልጆች በተለየ እሷ ላይ የስራ ጫና እንዲሁም ታናናሾቿን የመንከባከብ ሀላፊነት ተጣለባት ትዝ ይለኛል ለማጥናት ጊዜ ስለሌላት ከት/ቤት መልስ ስራዋን ሰርታ ከእንቅልፋ ተሻምታ ታጠና ነበር ባንድ በኩል እናቷ ጤናቸው ወሰድ መለስረ ያደርጋቸዋል አባቷ ደግሞ ቄስ በመሆናቸው " አሰደብሺኝ የሰው መሳቂያ መሳለቅያ አደረግሺኝ በተከበርኩበት ሀገር የመዋረዴ ምክንያት ሆንሽ በሄድኩበት ሁሉ  'የቄስ ከበደ ልጁ ጴንጤ ሆና አረፈችው ' እያሉ በአፋቸው ያላምጡኛል ባንቺ ምክንያት አንገቴን ደፋሁ አንቺ ከምትወለጂ የእናትሽ ማህፀን ደረቅ ቢሆን ይሻል ነበር "ይሏታል አንዳንድ ጊዜ ምርር ሲላት ቅዳሜ ቅዳሜ ስንገናኝ ከህብረት በኋላ ለሁላችንም ትነግረናለች "በቃ የአባቴ ጭቅጭቅ ሲበዛ ፣ የቤቱ ስራ ሲበዛብኝ ብን ብለሽ ጥፊጥፊ ይለኛል መኖር ምርር ሲለኝ ደግሞ በትምህርትም ተስፋ እቆርጥና የማጠናበትን ጊዜ በእንቅልፍ አሳልፋለሁ ከኔ ጋር ፉክክር ውስጥ በመግባታቸው ምክንያት ታናናሾቼን አያሰሯቸውም ልክ እንደ ቤት ውስጥ ሰራተኛ ሆኛለሁ ሌላው ቢቀር ወንድሞቼ እና እህቴ ካላቸው ነፃነት የተነሳ እንደ ታላቅ እህት ሳይሆን እንደ ሞግዚት ሊያዙኝ ይፈልጋሉ ብቻ የእግዚያብሄር ቃል ስለሚያበረታኝ እና የእናቴም ጤና ስላልተስተካከለ በዚ ሁኔታ ውስጥ ጥያቸው ብወጣ ምን ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ እንጂ በፊት ቤታቸው እንድኖር የፈቀዱልኝ ሰዎችም ቢሆኑ ቤታቸው ለኔ ሁሌ ክፍት እንደሆነ ይነግሩኛል መሄድ እንደምችል ባውቅም ልቤ ግን ጨክኖ መሄድ አልቻለም ብቻ የኔ ነገር ግራ እየገባኝ ነው እራሴን ለማጠንከር ብሞክርም መልፈስፈሴ አልቀረም



የሆነ የሚመክረኝ እና የሚያወራኝ ሰው እፈልግ እና እኔን ተረድቶ ምክር የሚሰጠኝ ሰው በዙሪያዬ አጣሁ ስለዚህ ያለኝ አማራጭ በውስጤ መብከንከን ስለሆነ በትንሹም በትልቁም ይከፋኝ ጀምሯል ፤ እዚህ የምነግራችሁም ለራሴ መቻል ሲያቅተኝ ብታዳምጡኝ እና ብትመክሩኝ ብዬ ነው " ትለናለች እንደ ወተት የጠራው አይኗ እንባዋን ፍልቅ ፍልቅ ያደርጋል ያን ጊዜ ሆዴ ውስጥ የሆነ ገብቶ ያለ ነገር ይመስላል አንጀቴ ይላወሳል በዚህ ጊዜ ከኔ በተሻለ ሴቶች እህቶቻችን እንዲሁም የፀሎት ህብረታችን መሪ ምክር ይሰጧታል እንደውም አንድ ሰሞን ብዙ ጊዜ አብዝተን ስለሷ እንፀልይ ነበር ሁኔታዋ ከቀን ወደ ቀን እየባሰ ሄደና ለረጅም ጊዜ ህብረት ሳትመጣ ቀረች መጀመሪያ አከባቢ በቃል እውቀት የበረታች ስላልነበረች የመዳከም ነገር ይበዛ ነበር ኋላ ግን ከቀን ወደ ቀን መበርታቷ እየጨመረ መቶ ለኔ እስከሚያስደንቀኝ ድረስ ብስለቷ አስገረመኝ ከኔም በተሻለ ብርቱ ሆነች የቀረችበትንም ምክንያት ስንጠይቃት የእናቷ እህት ከገጠር መጥተው ሁኔታውን ሁሉ ሲሰሙ ሀይለኝነታቸው ተባብሶ ጭራሽ ከቤት እንዳትወጣ አደረጓት አመጣጣቸው የታመመች እህታቸውን ለመጠየቅ ቢሆንም ሶስተኛ ሰው ሆነው ከቤተሰቦቿ በላይ ጫናን እና ቁጥጥርን አበዙባት እናቷ ህመማቸው እያየለ ፋታ ስለነሳቸው ከሷ በላይ ጤናቸው ላይ ጭንቀት አብዝተዋል ታድያ ለወራት የቆዩት አክስቷ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲመለሱ እሷም ወደ ፀሎት ህብረት ተመለሰች ሁሉም ምስራቅ የት ሄደች ብሎ በልቡ የሚያብሰለስለውን ነገር እና በጋራ የሚወያዩበትን ጉዳይ የመምጧቷ ነገር ሲሰማ በማከታተል ምክንያቷን ጠየቋት የገጠማትን ስትነግረን እኔንም ጨምሮ ስለሷ መጥፋት የተጨነቀ ሁሉ "ዋናው ሠላም መሆንሽ እና መመለስሽ ነው አልናት....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
8.0K views16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 19:00:23 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፴፮
@yanetmasra

" ምን መሰለህ እዩዬ በጣም እርቦህ ምግብ ሲቀርብልህ እና እንዲሁ ምግብ በሞላበት ለመብላት ስትዘጋጅ ያለህ ስሜት ይለያያል በጣም እርቦህ ከምግብ እርቀህ ትንሽ ነገር እየቀማመስክ ስትኖር ለምግብ ያለህ ፍላጎት እና ጉጉት ይጨምራል እንዲሁም የምግብ ቡፌ እየቀረበልህ  አማርጠህ  የምትበላ ከሆነ ግን ይሄን ያህል ጉጉት አይኖርህም የተሰጠህን በቅጡ ላትበላ ወይም ደሞ ቁንጣን ሊያጨናንቅህ ይችላል ። ክርስትናም እንደዚሁ ነው ማምለክ በማትችልበት ሰአት እና ሁኔታ ላይ ሆነህ መንግስትም ቤተሰብም ቢነሳብህ በድብብቆሽ እና በመከራ ሲሆን እምነትህ ይበልጥ ኢየሱስን ለማወቅ ያለህ ጥማት እየጨመረ ርሀቡ ያንገበግብሀል መንፈሳዊ ነገሮችን ተሻምተህ ትካፈላለህ ምክንያቱም የረሀብህ ማስታገሻ ስለሆነ ፤ አሁን ላይ ግን ብዙ ነገሮች እንደልብህ ነው ቤተክርስቲያን መሄድ ብትፈልግ ፣ በቤትህም ሆነ በሰው ቤት ፕሮግራም ብታዘጋጅ የሚያስቆምህ የለ ፣ ከበፊቱ በተሻለ መንገድ ላይ ወንጌልን መናገር ትችላለህ ብቻ ብዙ ነገሮች በነፃነት እየተገኘ ስለሆነ ቢፈልጉ ማድረግ ስለሚችሉ ረሀቡ ወደ ቅንጦት ተዘዋውሯል ለሌላ ነገር ቅድሚያ እየሰጠን መንፈሳዊ ነገሮችን ወደሗላ መገፍተር ጀምረናል በዛ ላይ ደሞ አንዳንዴ ዋጋ ከፍለህ የምታገኘው ነገር እና እንዲሁ በነፃ የምታገኘውን ነገር ስትጠቀም አጠቃቀምህ አንድ አይነት አይሆንም ። ለከፈልክበት ነገር ይበልጥ ትጠነቀቃለህ ለነፃው ነገር ግን ብዙ ትኩረት አትሰጠውም እና በግልፅ የሚታየው እየሆነ ያለው ይሄ ነው ፤ እንዳልከው ጭራሽ አሁን ላይ በደንብ መትጋት ሲገባን ጥቂቶች ግን የማይሆን ነገር ሲያደርጉ ይታያል ግን ማወቅ ያለብህ ነገር ቃሉም ቢሆን ስለሀሰተኛ ነብያት ስለሚናገር ከእነሱ ተጠብቀህ በፍፅም ልብህ ጌታ እግዚአብሔር አምላክህን ተከተለው



ሰዎችን ካየህ ትስታለህ እግዚአብሔር ካየህ ደሞ ታተርፋለህ በዛው ልክም ደሞ አብዛኛው አማኝ ማህበረሰብ ፈሪሀ እግዚአብሔር ያለው እና ቃሉን ለመኖር የሚጥር ሰው ነው ቢሆንም ግን የተበላሽ ፍራፍሬ ከጤነኛው ጋር አብሮ ሲቀላቀል እንደሚያበላሸው ሁሉ እኛም ብንሆን እራሳችንን ከሚያበላሹ አሳቾች መጠበቅ አለብን ። በንዴት ፣ በጥላቻ ፣ በክፋት ወይም በብልጣብልጥነት የሚሆን ነገር የለም መፍትሄው እውነት ነው ። እውነትን በመናገር ለእውነት  መኖር በንፁህ ልብ

   መፅሀፉን ለመቀጠል ጉጉት ቢኖረኝም ሶፋ ላይ እንደተንጋለልኩ በሀሳብ እሩቅ ነጎድኩ ጓደኞቼን ፣ እራሴን ፣ ዘመናችንን ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ፣ በህይወት የሌለው አባቴ ያሰፈረውን ቃል ብዙ ነገሮችን አብሰለሰልኩ ለምን ? ለምን ? ለምን ? እንደዚህ ሆነ የሰው ልጅ ልብ የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት ምነው ደነደነ ፈጣሪውን እረሳ በምን መልኩ ወንጌልን ብንሰብክ ልባቸው ይራራል ? ኢየሱስን ያልተቀበለ እኛን ያምናል ? የኛስ አካሄድ ወዴት ወዴት ነው አንድ ክርስቶስን እኛመንን አንድ ሺ የሳተ ትምህርቶችን አዛብተን እናስተምራለን ፤ አዳንን እያልን በግብዝነት ስንቶቻችን ነን ገደል ጠራርገን ፤ ተጠራርገን የምንገባው ? ከመመካከር ፣ ከመወያየት ፣ ከመተራረም ይልቅ ጉዳችንን እየሸፋፈንን የሆዳችንን በሆዳችን ይዘን ሌሎች ላይ ጣታችንን የምንቀስረው ? የኛ መበላሸት ሳያንሰን በድርጊታችን እና በሁኔታችን የማያምኑ እንዳያምኑ ሊያምኑ ጫፍ የደረሱ አፈግፍገው እንዲሸሹ ምክንያት የምንሆነውስ ስንቶቻችን ነን ? እጅግ በጣም ብዙ ብቻዬን አስቤ መልስ ያጣሁለትን ጥያቄ ከማሰብ ገታ ብዬ ያቆምኩትን ፅሁፍ ለመቀጠል ገለጥ  ፣ ገለጥ አደረግኩት ....ይቀጥላል
#share
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
11.1K views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-14 19:20:04 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፴፭
@yanetmasra

ይሄን ታሪክ አውቀዋለሁ ስሟም አዲስ አልሆነብኝም የምስራች የእናቴ ስም ነው ታሪኳም እዚህ መፅሀፍ ላይ እንደሰፈረው ነው ለሰአታት ተመስጬ ሳነበው የነበረውን የአባቴን ታሪክ ከድኜ ወደ እናቴ ሄድኩ እናቴ መኝታ ክፍሏ ጋደም ብላ ነበር ያገኘሗት " እማ አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር እዚህ ፅሁፍ ላይ ካንቺ ጋር ተመሳሳይ ታሪክ እና ስም ያላት ልጅ ሳነብ አጊንቻለሁ አንቺ ነሽ ወይስ አስገራሚ ምስስሎሽ ነው " ብዬ ጠየቅኳት ጋደም ካለችበት ለመነሳት እየሞከረች " አንብበህ ብትጨርሰው እኮ ሁሉንም ትረዳው ነበር " አለቺኝ እኔም እንዳላስቻለኝ ነግሬ ከአንደበቷ ማረጋገጥ እንደምፈልግ ነገርኳት እሷም ቀጠል ብላ " አዎ እኔው ነኝ ይሄ አስገራሚ ምስስሎሽ ሳይሆን እውነታ ነው መጀመሪያ አካባቢ ላይ ከትውውቆሽ ከዛም ሲዘል ከጓደኝነት ውጪ ምንም አልነበረንም ሗላ ላይ ግን የፍቅር ግንኙነት ጀመርን ተጋብተንም አንተን የመሰለ ሸበላ ወለድን " አለቺኝ ፈገግ ብላ ይሄን ስሰማ ይበልጥ ታሪካቸውን ለማወቅ አጓጓኝ " እስቲ አብራሪልኝ ? " ብዬ ስጠይቃት " እኔ ከምነግርህ በላይ አባትህ እሱ የያዝከው መፅሀፍ ውስጥ ቁልጭ አድርጎ እያንዳንድን ክስተት ዘርዝሮታል ይልቁንስ አንብበህ ጨርስ እና እናወራበታለን "  አለቺኝ በሀሳቧ ተስማምቼ መፅሀፉን መጀመሪያ ባነበው ይሻላል ብዬ ወሰንኩ ከዛ በፊት ግ " እማ መፅሀፉን ሳነበው በጣም ተገርሜም ፣ አዝኜም ፣ ካሁኑ ጊዜ ጋርም አመዛዝኜው ነበር ጠዋት ተናድጄ ባልኩት ነገር እራሱ አፍርየለሁ የእውነት እናንተ በዛን ወቅት መከራውን ፣ ስደቱን ተቋቁማችሁ ወንጌልን በመስበክ አደራችሁን በመወጣት ለኛ አስተላልፋችሁ ሳለ እኛ በዚ ጊዜ በጥቂቱ ነገር ስንበሳጭ ወይ ስንፈተን ቶሎ መናደድ እና ገፋ ሲልም " ባክ ለማድረግ "እንቸኩላለን ከበፊቱ የተሻለ ነፃነት ስናገኝ የበለጠ ከመትጋት እና ከመበርታት ይልቅ የስም ክርስቲያን መሆን እና ብዙ መተረማመስ ይታይብናል



አንዳንድ ወጣቶች ደሞ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሲኖሩ ሁሉን ነገር ቤተሰቦቻቸው እያደረጉላቸው በግላቸው ሳይበረቱ ይቀሩ እና ከቤተሰቦቻቸው የተለዩ ቀን ወደማይሆን ነገር ይገባሉ እኛ እራሳችን እራሱ ከበፊቶቹ ጋር ልንነፃፀር አንችልም እውነት መከራ ቢመጣ አሜን ብሎ በፀጋ መቀበል እንችላለን ወይ ብዬ እጠራጠራለሁ አሁን እኮ እማዬ የበፊቶቹ አገልጋዬች በድህነት እና በታማኝነት ወንጌልን እየሰበኩ ለዛሬው ትውልድ እንዳላስተላለፉ አሁን ላይ ደሞ የእግዚአብሔርን ስም መነገጃ ያደረጉ ፤ ወንጌል ሳይሆን ሀብታቸው የሚያሳስባቸው ፤ ባስ ሲልም ህዝቦችን የሚያስቱ ፤ ኑሮሯቸው አርቴፊሻል የሆነ አገልጋዬች ብቅ ብቅ ከማለታቸውም በላይ እየተስፋፉ መጥተዋል አሁን ከቀድሞው ጊዜ በበለጠ መትጋት ሲኖርብን ጭራሽ እየተንሸራተትን መጥተናል ልላውን ተይው እና እራሴን እራሱ እንደ ሌላ ሰው ታዘብኩት ከዚ በላይ ወንጌልን መስበክ ሲኖርብኝ በወንጌል የሚመጣብኝን መከራ በማሰብ ተዝረክርክ ያለሁ ታውቅያለሽ ወንጌል ቅብብሎሽ ነው እኔ አወቅኩ ፣ ዳንኩ ብዬ የምዘጋው ነገር ሳይሆን ደሞ ለሌሎችም ያወቅኩትን አውቀው እንዲድኑ የምናገርበት ነው ካለዛ ልክ ' እንደ ጋን ውስጥ መብራት ' ይሆናል የኔ ማወቅ ታድያ ዋናው ልልሽ የምፈልገው ነገር ቢኖር እንዴት ነው መንግስት በሀይማኖት ጣልቃ በማይገባበት ጊዜ ላይ ሆነን እንደቀድሞው ወይም  ከዛ በበለጠ መልኩ እምነታችን በድርጊት የምንገልፀው ? መቼ ነው ክርስቶስን መስለን ለክርስቶስ የምንኖረው ? የምድር የቅራቅንቦ ቡፌን ለማንሳት የምንስገበገበው እንስፍስፍነት ገታ አድርገን ለዘለአለሙ የምንንሰፈሰፈው እንደውም ሳስበው እግዚአብሔር አባታችን ነው ብለን ስንናገር ከዛ በላይም ደሞ እየተዳፈርነው ያለን ይመስለኛል ቁጡ መሆኑን ማወቅ የተሳነን ይመስላል ብቻ ጉድ ብዙ ነው አንድ እግዚአብሔር ያስተካክለው እንጂ ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
10.2K views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-04 19:01:04 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፳፯
@yanetmasra

ቤተሰቡ ተሰብስቦ ምህረትን በመጠበቅ በር በሩን ይመለከታል መምጫዋ ደረሰና በሩን ወከክ አድርጋ ገባች ገና የቤተሰቧን ፊት ከማየቷ በፈገግታ ተሞላች እማዬ ፣ አባዬ ፣ ወንድሜ እያለች በየተራ አገላብጣ ሳመቻቸው ሁሉም በደስታ አፀፋውን መለሱላት ምህረት ቀይ ዳማ ፣ ቁመቷ ለሴት ልጅ ረጅም የምትባል ፣ ፈገግ ስትል ጉንጮ ላይ ስርጉድ ያላት መልከ መልካም ልጅ ናት ። ማንነቴን ባለማወቋ ፊቷ ላይ የግርታ ስሜት ቢታይባትም ለሰላምታ እጆን በመዘርጋት " ሠላም ነው " አለቺኝ እኔም እጆቼን ዘርግቼ ሰላምታዋን ተቀበልኳት ከዛን ከቤተሰቦቿ ጋር ስትጫወት ፣ ስታወራ በማህል እረሱኝ ለነገሩ እኔን የሚያማክል ወሬ ስላልተወራ ነው የጨዋታው አንድ አካል ያልሆንኩት እውነትም ግን በሱፈቃድ እንደነገረኝ ምህረት በሳልና ብልህ ልጅ ናት የምታወራውን ነገር በሰማሁ ቁጥር ከእድሜዋ በላይ መብሰሏን ተረድቻለሁ በተለይ ደሞ የማያምኑትን አያቷ የማታምን መስላ እንዴት እንደምትንከባከባቸው ስትነግረን እና እንዴት በስውር እንደምታመልክ ስታጫውተን ተረገምኩባት ለነገሩ የእሷ ላቅ ያለ ስለሆነ ነው እንጂ በሱፈቃድም ቢሆን አስተዋይ እና መንፈሳዊ ህይወቱ የጠነከረ ልጅ ነው ። ማንነታቸው ከአስተዳደጋቸው ጭምር የመጣ ይመስለኛል ።

    ወደኔ በመመልከት " የበሱቃድ ጓደኛ ወይም ጎረቤት ነህ ከዚህ በፊት አይቼህ አላውቅም  "አለቺኝ በእርግጥ ብትፈልግም ከዚ በፊት ልታየኝ አትችልም ምክንያቱም እነሱ ወደሰፈራችን ከገቡ ገና ሁለት አመታቸው ነው እሷም ባለፈው አመት ስላልመጣች ልታየኝ የምትችለው ዛሬ ገና ነበር ። " ያው ሁለቱንም ነኝ ማለቴ ጎረቤቱም ጓደኛውም ነኝ " አልኳት ለጥያቄዎቿ አጭር ምላሽ ነበር የምሰጣት



" መልካም እንግዲህ በቆይታዬ ብዙ ጊዜ እዚህ የምትመጣ ከሆነ ከእኔም ጋር በደንብ እንተዋወቃለን " አለቺኝ ይሄን ጊዜ በሱፈቃድ ጣልቃ ገብቶ " እንግዳ አደለም አሁን የቤተሰባችን አባል ሆኗል ስለዚ ሁሌ እዚ ይኖራል " አላት ነገሩ ስላልገባት "ማለት " ብላ ጠየቀችው "ማለት እማ የሚኖረው ከኛ ጋር ነው በወንጌል ምክንያት ከቤተሰቡ ጋር ተጣልቶ ከቤት ስለወጣ እዚህ አብሮን ይኖራል ከጎረቤትም ከጎደኛም በላይ ወንድሜ ሆኗል ላንቺም ከእንግዲህ ታናሽ ወንድምሽ ነው " አላት " እውነት በጣም ደስ ይላል አንድ ወንድም ብቻ ነው ያለኝ እል ነበር ከእንግዲህ በሗላ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ማለት እችላለሁ ፤ በነገራችን ላይ ለወንጌል ብለው ዋጋ የሚከፍሉ ሰዎች በጣም ነው የሚያስደስቱኝ በተመቻቸ መንፈሳዊ ህይወት ውስጥ ከሚኖሩት በላይ አባጣ ጎርባጣ በሆነው መንገድ ውስጥ ኢየሱስን የማያመልኩ የሚያስቀና የህብረት ህይወት አላቸው አንተም ከእነሱ መካከል በመሆንህ ልትደሰት ይገባል ለወንጌል የሚከፈል መስዋዕትነት መከራ ብቻ ሳይሆን እድልም ነው ስለተመረጥክ ደስ ይበልህ " አለቺኝ " አመሠግናለሁ ያልሽው ነገር ልክ ነው ባልመረጥ እና እግዚአብሔር ባያየኝ ኖሮ ይሄኔ ከሚሞቱት መካከል እየባዘንኩ እኖር ነበር ይሄ እንዳይሆን ደሞ እንድድን ተመርጫለሁ ሌላው ቢቀር ይሄ ብቻ ለኔ በቂ ነው " አልኳት " አዎ ከዚ በሗላ በነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይረዳሀል እሱ አባት ነው ተስፋ ይሆናል ከቤተሰቦችህ ጋር ያለህ ግንኙነት ሁሉ እንደሚስተካከል እምነቴ ነው " አለች
  " በሉ ልጆች ጨዋታችሁን አቁሙና ወደ ማዕድ ኑ ክረምቱ ገና መጀመሩ ነው ሰፉ የመጫወቻ ጊዜ አላችሁ አንቺም ከመንገድ መምጣትሽ ነው እኛም ስንጠብቅሽ እህል አልቀመስንም ተሰብሰቡ እና እንብላ " አሉ አቶ ታሪኩ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
1.9K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-03 19:01:43 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፳፮
@yanetmasra

አይኔን እየጠራረግኩ ከመኝታዬ ተነሳሁ "ዩሀንስ የት ሄደህ ነው የጠፋኸው ያልፈለግንህ ቦታ እኮ አልነበረም ሀገሩን ሙሉ አሰስነው ብንል ይቀለናል ፤ ፊትህ ደሞ ምንድነው ? ማነው እንደዚህ አድርጎ የደበደበህ ? አሉኝ አቶ ታሪኩ እኔን በመፈለግ የደከሙትን ድካም ከፊታቸው ማንበብ ችያለሁ ፤ አሳዘኑኝ ! እኔም መልሼ ለበሱቃድ እናት የነገርኳቸውን መልሼ ለነሱ ነገርኳቸው " እንዴ ከበሱፈቃድ ጋር አልነበራችሁ እንዴ ? ከምኔው ተለያይታችሁ ነው የደበደቡህ ? " በማለት የበሱፈቃድ አባት ጠየቁኝ   " እሱን የሆነ ልጅ ጠርቶት ለጥቂት ከመለያየታችን ነው እኔን ያገኙኝ ምን አልባት ኖሮ ቢሆን ግን የኔ እጣ ለሱም ነበር የሚተርፈው እንደውም እንደነገሩኝ ከሆነ ለሱ ያሰቡት ከኔም ይብስ ነበር አለመኖሩ በጣም የተሻለ ነው ካለዛ ምን ያረጉት እንደነበር የሚያውቀው  እግዚአብሔር ብቻ ነው እንደውም ከመንገድ ሁሉ ካየሀቸው ጠንቀቅ ብለህ መራቁ የተሻለ ነው " አልኩት እሱም መልሶ " እንዴ እንደሱማ አይባልም እንደውም አብሬህ ብሆን የተሻለ ነበር እንዲህ እስክትሆን  አይደበድቡህም ለክፉም ለደጉም 'ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሀኒቱ ' እንደሚባለው አብረን ብንሆን መልካም ነበር ብዬ አስባለሁ ፤ ባንደበድባቸውም የሚደበድቡህን እጋራህ ነበር " አለኝ ባይደበድብልኝም የተመታሁትን እንደሚጋራኝ ሲነግረኝ ከልቤ አሳቀኝ አርቆ አለማሰቡ ነው እንጂ ለቤተሰቡ እዳ ነበር የሚጨምረው በዚ ኑሮ ላይ ሁለት በሽተኛ ማስታመሙ እዳ ከመጨመር ውጪ ሌላ ትርፍ አይኖረውም " በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ " ማለት ይሄ ነው ። " ጉድ እኮ ነው ዘንድሮ ለመደብደብም መጋራትን ታስባለህ ሆ ! ሆ ! አሁን ዋናው ነገር ከዚ የባሰ የአፋ ነገር አለመፈጠሩ ነው የእናንተ መጎዳት መልሶ እኛንም ይጎዳናል በምትችሉት ተጠንቀቁ የቀረውን እራሱ እግዚአብሔር ያስተካክለዋል " ብለው የምክርን ተግሳፅ አቶ ታሪኩ ለገሱን ያን ቀን በዛ አለፈ የኔም ህመምና ቁስል መሽቶ በነጋ ቁጥር እየዳነ መጣ ።



  ክረምት እንደመሆኑ መጠን የበሱፈቃድ እህት እንደምትመጣ ከራሱ ከበሱፈቃድ አንደበት ሰማሁ ። አያቱ አሁን ደና ስለሆኑ እንደ ባለፈው አመት የሚያስቀራት ነገር አልነበረም  ልተዋወቃት በመሆኑ ብደሰትና ብቸኩልም በሌላ በኩል ደሞ ምን አይነት ሰው ትሆን ወይም የኔ ከነሱ ጋር መኖር ምቾት አይሰጣት ይሆነሸ ብዬ ማሰቤ አልቀረም ፤ እንደ  እውነቱ ከሆነ ብዙ ሰው አዲስ ሰው ለመተዋወቅና ለመቅረብ ይከብደዋል እኔም ብሆን እንደሱ አይነት ስሜት ነበር የተሰማኝ ።

    አስታውሳለሁ ቅዳሜ ነበር ቀኑ ምህረት ትመጣለች የተባለው በዛን ቀን ነበር የበሱፈቃድ እናት ደስታቸው ፊታቸው ላይ ጎልቶ ይታያል እንደ ህፃን ልጅ መቦረቅ የቃጣቸው ይመስላል ለነገሩ ልክ ናቸው እንደ ዘመን መለወጫ በአመት አንድ ጊዜ እየመጣች መናፈቃቸው አይቀርም ሊያውም ያለፈውን አመት ቀርታ ። ታድያ የእናት ነገር ሆኖ መሰለኝ ከሁሉም በላይ ሊያዯት የጓጉ ይመስላሉ በሱፈቃድም ቢሆን እንደ እናቱ ባይንሰፈሰፍም ሊያያት ግን ናፍቋል ፤ አባቷም ቢሆኑ አገልግሎት ስለነበረባቸው እንጂ የወጡት ልጃቸውን ለማየት የቸኮሉ ይመስላሉ ታድያ ከመሄዳቸው በፊት " እንደጨረስኩ ቶሎ ነው የምመጣው ከመድረሷ በፊት ቀድሜ እደርሳለሁ " ብለውናል እኔ ግን ስለማላውቃት ነው መሰለኝ የደስታም የሀዘንም ስሜት አልታየብኝም ነበር ብቻ " ማን ትሆን ? የቤተሰቡን ትኩረት እንዲህ ስባ ልባቸውን በናፍቆት  ያራደችው ስል እራሴኑ ጠየቅኩት በትዝብት እየተመለከትኩ ። እኔም ለልጃቸው መምጣት ብለው ቤቱን የአመት ባህል እያስመሠሉ ጉድ ጉድ የሚሉትን እናቷ እቃ በማቀባበል አግዛቸው ነበር ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
3.6K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 20:43:36 በፖለቲከኞች ሳይሆን ለነገሮች መቋጫ እንደሚያበጅላቸው ሁሉን በሚችለው በእግዚአብሔር እንታመናለን!

#InGodWeTrust!
1.6K viewsedited  17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 19:11:50
በመጨረሻም መልካም ዜና

የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ላይ ደረሱ


በደቡብ አፍሪካ ለቀናት ድርድር ላይ ተቀምጠው የሰነበቱት የፌደራል መንግሥቱ እና ህወሓት በዘላቂነት ግጭት ለማቆም ከስምምነት ደረሱ።

ይህ የተገለጸው ሁለቱ ኃይሎች በደቡብ አፍሪካ ሲያደርጉ የነበረው የሰላም ንግግር ውጤት በተገለጸበት ወቅት ነው።

የፌደራሉ መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ንግግር ይዘት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ እየገለጹ ይገኛሉ።

BBC Amharic
@christian_mezmur
2.3K views16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ