Get Mystery Box with random crypto!

Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር C
የቴሌግራም ቻናል አርማ christian_mezmur — Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር
የሰርጥ አድራሻ: @christian_mezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 62.68K
የሰርጥ መግለጫ

🗣እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብከዋለን!
ትክክለኛ የሆኑ የወንጌል አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረጉ፦
ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ምስክርነቶች፣ የሪቫይቫል ታሪኮች፣ ዝማሬዎች፣ መንፈሳዊ ዜናዎች፣ እንዲሁም መንፈሳዊነታቸውን የያዙ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ!
ለወዳጅ ጋደኞቻቹ #ሼር በማድረግ ይጋብዙ!
አስተያየት @ChristianMezmur_bot ላይ ፃፉልን✍
ሁሌም ከኛ ጋር ስለሆናቹ እናመሰግናለን!

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-12-10 20:48:43 ዝማሬ “ በስሜ ታውቀኛለህ "
ዘማሪ Kefa Mideksa
የተለቀቀው Nov, 2022
Size 7MB
ርዝመት 7Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
1.7K viewsedited  17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 20:48:32
ዝማሬ “ በስሜ ታውቀኛለህ  "
ዘማሪ Kefa Mideksa
የተለቀቀው Nov, 2022
Size 40MB
ርዝመት 7Min
Quality 720HD(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
1.7K viewsedited  17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 20:46:34 #ሜርሲ_እና_ብዕሯ (Digital) መፅሔት

#አንደኛ_ዕትም

#መልካም_ንባብ


@Mercy_ena_berua
@Mercy_ena_berua
1.4K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 19:29:01 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፶
@yanetmasra

እቤት ከገባሁ በሗላ ምናለ መሽቶ በነጋ ብዬ ተቁነጠነጥኩ ትንሽ ፍርሀት ፍርሀት ቢለኝም አንድ ችግር ስለቀለለልኝ ደስታም ተስምቶኛል ግን ደሞ የእውነት ትምህርት ላቋርጥ ነው ብዬ አሰብኩ ማመን ቢከብድም ፣ ቅር ቅር ቢለኝም አምኜ መቀበሌ ለኔ ግድ ነው። ስራውን እስካገኝ ድረስ ሀሳቤ ስራው ላይ እንጂ የትምህርት መንገዴ ቁርጥ ብሎ የሚቋረጥበት ቀን ነው ብዬ አላሰብኩም ነበር የዛን ቀን ግን አሰብኩት አይምሮዬን ማሳመን እንዳለብኝ ተሰማኝ ምክንያቱም ስራ መጀመሬ እንኳን ቢታወቅ እንዴት እኔ ሳላምንበት እነሱን አሳምናቸዋለሁ እነሱ በስራዬ እንዲያምኑ ትምህርት ማቋረጤን እንዲረዱ እና እንዲቀበሉ ማድረግ አለብኝ

  ከእቤት በጊዜ እየተጣደፍኩ ወጣሁ እንዳላረፈድኩ ተስፋ በማድረግ  ወደካፌው ስገባ ገና እየከፋፈቱ  ነበር ባለቤቱን እና ሁለት አስተናጋጆችን አገኘው ቀስ ብዬ በመጠጋት " አስታወሱኝ ጋሼ የትላንትናው ልጅ ነኝ " አልኳቸው ምን እንደምላቸው ጠፍቶኝ እንጂ መቼስ ይረሱኛል ማለት ዘበት ነው " አዎ እንደምነህ ጥሩ ሰአት ነው የመጣኸው መአዛ የምትሰራውን ታሳይሀለች " ብለው ከሁለቱ ሴቶች መካከል አጠር ያለችውን ጠርተው የምሰራውን እንድታሳየኝ ነገሯት ከዛም ወደኔ መጥታ " ሰላም መአዛ እባላለሁ " ብላ ንግግሯን ጀመረች እኔም " ሰላም ነኝ ዩሀንስ እባላለሁ " አልኳት " እሺ ዩሀንስ ጋሼ እንደነገሩህ ፅዳት ነው የምትሰራው ጠዋት ትመጣና ቤቱን ጠርገህ ትወለውላለህ ጠረጴዛውንም እንደዛው ከዛ ደንበኛ መቶ በሄደ ቁጥር ለሌላ ተስተናጋጅ ጠረጴዛውን አፅድተህ ወንበሩን ታሰናዳለህ ስራህ ይሄነው አሁን አብረን እንሂድና የማፅጃ እቃዎቹን ላሳይህ ፤ የመውጫ ሰአትህ ጋሼ እንዳሉኝ 11 ሰአት ነው " አለቺኝ የምትለኝን ሁሉ አዳምጬ እሺ በማለት ተከተልኳት



የእቃዎቹን ቦታ እያሳየችኝ ፅዳቱን ጀመርኩ የመጀመሪያ ቀኔ ስለሆነ አብራኝ በማፅዳት ተባበረቺኝ ደንበኛ ይመጣል ይሄዳል እኔም እንደተባልኩት የጠረጴዛውን ጨርቅ ይዤ ለመወልወል እሄዳለሁ የምሰራው ስራ ከበደኝ ማለት አልችልም እቤት ውስጥ ስራ መስራቴ የጠቀመኝ ይመስለኛል ቀኑን በመልካም አሳለፉኩ እንደተባልኩት 11 ሰአት ላይ ወጣሁ ፤ እየበረርኩ እቤት ሄጄ የሊስትሮ እቃዬን ይዤ መልሼ ደሞ በቀረችው ሰአት ጫማ ለመወልወል ወጣሁ አርፍጄባቸው ስለነበር አስቀድመው እህቶቼ እዛው ደርሰዋል ቀድማ ያየችኝ ፍቅር ስለነበረች " ዩሀንስ የት ሄደህ ነው እስካሁን ካለወትሮህ ስትቆይ እኮ አስጨነቅከን በሱፈቃድንም ስጠይቀው እንደውም ቀኑን ሙሉ  እንዳላየህ ነው የነገረኝ ፤ የሰሞኑ ሁኔታህ ግን ልክ ነው የሆነ ያስጨነቀህ ነገር ያለ እና ብቻህን እየተብሰለሰልክ ያለህ ይመስለኛል "አለቺኝ በሱፈቃድን እና ፍቅርተን መዋሸት እንደማይቻል ነው የገባኝ ነገሮችን ጥልቅ ብለው የማሰብ እና የማስተዋል ብቃት አላቸው  " አይ ምንም የለም ከትምህርት ቤት ወጥቼ ጓደኛዬ ጋር ሄጄ ነው የቆየሁት " አልኳት ጥያቄዋ ግን አያበቃም " የትኛው ጓደኛህ ከበሱፈቃድ ውጪ ሌላ ጓደኛ እንዳለህ እስከዛሬ አላውቅም ነበር " አለቺኝ " አንድ ክፍል ነን እና በቅርቡ ነው የተግባባነው ብቸኛ ስለሆነ ጓደኛ አድርጌው ነው ዛሬ ቤቴ ካልወሰድኩክ ሲለኝ እምቢ ማለት አልቻልኩም ለዛ ነው " ብዬ በፍጥነት ካካባቢዋ ልሰወር ስል " አይመስለኝም ባለፈው ቆሎ መሸጥ ስንጀምር ለጥቂት ቀን ብቻ ነው የሆነ መፍትሄ አመጣለሁ ብለኸኛል እንዲሁ ከመሬት ተነስተህ አይመስለኝም እባክህ ንገረኝ ውሸት ይብቃህ እውነት እንዳልሆነ ንግግርህ ከፊትህ ይነበባል  " አለቺኝ ከዛ በላይ ማስመሰሉ ሊሳካልኝ እንደማይችል ስለተረዳሁ " ደረቅ እኮ ነሽ እሺ በቃ እነግርሻለሁ ግን ሚስጥር ነው ለማንም እንደማትናገሪ ቃል ጊቢልኝ " አልኳት ፈጠን ብላ  " ቃል እገባለሁ " አለች " ስራ ስፈልግ ነበር ሰሞኑን ፤እና ትላንት አጊንቼ ዛሬ ጀምርያለሁ ለዛ ነው ያረፈድኩት አሁን የተሻለ ስለሚሆን የማገኘው እናንተ ትምህርታችሁን መማር ትችላላችሁ እኔ ቀን ካፌ ወደ አመሻሽ ደሞ ጫማ እየጠረግኩ በማመጣው ገቢ መኖር ትችላላችሁ አውቃለሁ ሙሉ ለሙሉ ችግራችንን ባይቀርፍም ከእጅ ወደ አፍ ለሆነ ኑሮ ግን  ይበቃል " አልኳት እንዳሰብኩት አልተደሰተችም " ምን ! ትምህርትህስ ! በፍፁም አታደርገውም " ብላ አምባረቀችብኝ ብላት ብሰራት አልሰማ ብላ ክችች አለች አስቀድማ ቃል ስለገባችልኝ ብቻ ለማንም እንዳትናገር ቃሏ አሰራት " ወይኔ ወንድሜ ለኛ ብለህ ህይወትህን መስዋት ልታደርግ ነው እንድንማር ብለህ ላትማር ነው በቃ " እያለች ተንሰቅስቃ አለቀሰች ላባብላት ሞከርኩ እየባሰ ቢመጣ ግን ሀዘኗ ሀዘኔን ሰርስሮ እምባዬን ሊያመጣው ሞከረ ብቻ እንደምንም ብዬ ገታሁት....ይቀጥላል
#share

ምዕራፍ ፩ በዚሁ አበቃ ምዕራፍ ሁለትን በቅርቡ ይዘንላችሁ የምንቀርብ ይሆናል ።


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
1.2K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 19:26:01 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፱
@yanetmasra

እንደምንም እያልን ኑሮአችንን ለመግፋት እና ለማሻሻል ሞከርን ግን ያሰብነውን ያህል ሊሆን አልቻለም ስለዚህ ጋራዥ ውስጥ ለመስራት ወይም ምግብ ቤት ውስጥ ለማስተናገድ ብቻ ሻል ያለ ገቢ የሚገኝበትን ስራ ለመስራት ማፈላለግ ጀመርኩ ። ብዙ የሚረዳኝ ሰው ስለማላውቅ ስራውን የምፈልገው አንዳንድ ቀን ትምህርት በመቅረት ነው በሄድኩባቸው ቦታዎች ስራ እንደምፈልግ እና እንዲሰጡኝ እጠይቃቸዋለሁ አንዳንዶች ተጨማሪ ሠው እንደማይፈልጉ እና ያሏቸው ሰራተኞች በቂ መሆናቸውን ይገልፁልኛል ። ሌሎች ደሞ እየቀለድኩ የሚመስላቸው ለቀልድ ጊዜ የለንም ብለው ያሰናብቱኛል በዚህ መሀልም አርፈህ ትምህርትህን ብትማር ይሻልሀል የሚሉኝም አልጠፉም ለነዚህ ሠዎች መማር ሳልፈልግ ሳይሆን መማር ሳልችል ቀርቼ መሆኑን ማን በነገረልኝ ብዬ ሳላስብ የቀረሁበት ቀን የለም ። ታድያ ይሄን በማደርግበት ሰአት ማንም ሊያውቅና ሊጠረጥር አልቻለም ፤ በዚህ መልኩ ጥቂት ቀናት ካሳለፍኩ በሗላ እየቆየ ሲሄድ በሱፈቃድ ነገረ ስራዬ ሁሉ አልዋጥልህ አለው አብረን አንድ ትምህርት ቤት ስለምንማር ስራውን ለመፈለግ ያሰብኩ ቀን እንደምቸኩል ነግሬው እንዲሁም ስንለቀቅም አትጠብቀኝ ብዬው እሄዳለሁ ከጊዜ በሗላ ያመጣሁት ፀባይ ጥርጥሬ ውስጥ ከተተው በዛ ላይ በተደጋጋሚ የትምህርት ቤት ጊቢ ውስጥም ፈልጎ ሳያገኘኝ ቀርቷል ምንም ያህል ትምህርት ቤት አለመግባቴን እንዳያውቅ ብጥርም አንድ ነገር እንዳለ ሳይገባው አልቀረም ። ከዛን በሗላ ግን የምለውን ከማመን ይልቅ እኔን ላለማስከፋት ሲል ብቻ " እሺ " ይለኛል እንጂ ፊቱ ላይ ያለማመን ስሜት አነብበታለሁ የማደርገው ባጣ እንጂ መዋሸት በጣም ከባድ እና የራስ ማንነትን ዝቅ የሚያደርግ በእግዚአብሔር ዘንድም የሚጠላ ቢሆንም "የቸገረው እርጉዝ ያገባል " እንደሚባለው ሌላ የመፍትሄ ቁልፍ የሆነ መንገድ በማጣቴ አይናቸውን እያየሁ ዋሸሗቸው



እንደውም አንዳንድ ቀን እቤት ስንሆን እቴቴ " አሁን የምጡ ማብቅያ ተቃርቧል ሁለታችሁም በርትታችሁ አጥንታችሁ ያመጣችሁት ውጤት የምታዩበት የዘራችሁትን የምታጭዱበት ምዕራፍ ላይ ናችሁ ደሞ አምናለሁ መልካም እና ጥሩ ውጤትን አምጥታችሁ ለራሳችሁ ተስፋ ለኛ ደስታ እንደምትሰጡን ስለዚህ በቀረው ጊዜያችሁ በርቱ አምላካችን እግዚአብሔር ከናንተ ጋር ይሁን የምታነቡትን ይግለጥላችሁ " ትለናለች ከእናታዊ ፍቅሯ የተነሳ ይህንን እንደምትለን ባውቅም የኔ አካሄድ ግን ከዛ ተቃራኒ ስለነበር ምርቃቷ እና ምክሯ ፍርሀትን ይለቅብኛል ዝም ላለማለት ብቻ " አሜን " እያልኩ በሱፈቃድን አጅበዋለሁ

  አንድ ቀን እንደተለመደው ስራ ፍለጋ ከላይ እታች ስዳክር ውዬ እድል ቀናኝ ካፌ ውስጥ ገብቼ ለባለቤቱ ስራ እንደምፈልግ ስነግራቸው በአባታዊ አስተያየት እየተመለከቱኝ " እውነት ስራ ብሰጥህ ትሰራለህ ማለቴ ትችላለህ "  አሉኝ " በሚገባ በደንብ እሰራዋለሁ ስራ ለማግኘት ምን ያህል እንደደከምኩ ስለማያውቁ ነው ብቻ አምነው ይቅጠሩኝ " አልኩና ቢያዝኑልኝ እና ቢቀጥሩኝ ብዬ የቤተሰቤን የድህነት ሁኔታ ዝክዝክ አድርጌ ነገርኳለው ታድያ ሳላስበው እንባዬም በመውረዱ ንግግሬን አደመቀው ። " እሺ እዚህ ካፌ ውስጥ ፅዳት እንድታፀዳ እና የሚሰሩትን በማየት በማይኖሩበት ጊዜ አስተናጋጆቹን እንድታግዝ እቀጥርሀለሁ ፤ ማወቅ ያለብህ ነገር ማጭበርበር  ፣ እና ስርቆት ምን ያህል እንደምጠላ ነው በአግባቡ ስራህን ከሰራህ ቋሚ አስተናጋጅ ሆነህ ትሰራለህ " አሉኝ በደስታ ጮቤ ረገጥኩ ቶሎ  ሀሳባቸውን ሳይቀይሩ ብዬ በማሰብ " ታድያ አሁን ልጀምር ? " አልኳቸው " አይ ነገ ትጀምራለህ በጠዋት ናና ልጆቹ መስራት ያለብህን ያሳዩሀል " አሉኝ ትልቅ ምስጋናን አቅርቤላቸው ወደ ቤቴ ሄድኩ....ይቀጥላል
#share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
1.3K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 19:01:03 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፰
@yanetmasra

አንዳንድ ጊዜ የምትናገረው ነገር ወሽመጥ ነው የሚቆርጠው እኔማ ወሽመጤ ተቆርጦ ተቆርጦ ወሽመጥ አልባ ልሆን ምንም አልቀረኝም " ግን እኮ ከባድ ነው ብዙ ወንዶች ይተናኮሏቸዋል ካልሆነ ሌላ ስራ ፈልጌ እኔ እገባለሁ " አልኳት እሺ ትላለች ብዬ በማሰብ እሷ ግን " እስከዛ እራብ እንሙትልህ አንተ እንደሆንህ አይገድህ እዛው ትሰለቅጣለህ ይብላኝ እንጂ ለኛ " ብላ ወደ ጓዳ ገባች መናደዴ ሲበዛ ቤቱን ጥዬ ወጣሁ ሂዱም አትሂዱም አላልኳው ብቻ ከነገሮች ለመራቅ ይመስል የተጠቀምኩበት አማራጭ ብቻዬን ሆኜ እራሴን የማዳምጥበትን መንገድ መፈለግ ነው ። ከአንድ ዛፍ ስር ብዙ ሠዎች ለመረማመድ ወደማያዘወትሩበት ቦታ ሄጄ ቁጭ አልኩ አንዳንድ ጊዜ ድህነት ሽንፈት የሚመስልበት ሁኔታ አለ የምናሳልፈው ችግር ፈተና መሆኑን ስንዘነጋ ነው እንደሱ የምናስበው እኔም ታድያ ይሄኔ ብር ቢኖረኝ እንደዚህ አልሆንም ብዬ ቁጭት ተሠማኝ ትምህርት የማቋረጥን ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ  በልቤ የፀነስኩት ያን ለት ነበር ለማንም ግን ልናገር አልወደድኩም ምክንያቱም ለትምህርት ያለኝን ቦታ እና ውጤቴን ስለሚያውቁ የእብድ ሀሳብ ነው ብለው ነው የሚያስቡት ። ትምሀርት ለመውደዴ ምክንያት የምትሆነው እናቴ ናት " ሠው ከተማረ ትልቅ ቦታ ይደርሳል  " ብላ የማሰቧ ነገር እሷ መማር ባትችልም ልጆቿን ግን እንድታስተምር አድርጓታል ማቋረጤ ያስከፋታል ብዬ ሳላስብ ቀርቼ ሳይሆን ሰርቼ መገኘቴ በዛን ሰአት ለቤተሰቦቼ በተለይም ለእህቶቼ ምንያህል ጠቃሚ እንደሆነ በማሰብ ነው ። ቢያንስ አይምሮአቸውን ሰብስበው መማር ይችላሉ ። በወቅቱ የነበረው ማህበረሰብ የተማረ የሚባል አይደለም በቀለም ትምህርት ሲመዘን ፤ እንዲሁም የትምህርት ጥቅም ያልገባው ይበዛል እንደውም 12ኛ የደረሰ እንደኛ አይነት ተማሪ ሁሉ የሚሰጠው አመለካከት ልዩ ነው ልክ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ጭላንጭል ብርሀን ሲታይ አድርገው ነው የሚቆጥሩት



ሁለተኛ ላስብ የቻልኩት አንድ ነገር ቢኖር ለጊዜው መስራታቸው ካልቀረ ሌላ የተሻለ እና ደና ስራ እስካገኝ  ድረስ እኔ ጫማ የምጠርግበት አካባቢ መሸጥ እንደሚችሉ እና በአይኔ ልከታተላቸው እና ባስካለ ነገር ልጠብቃቸው እንደምችል ተገነዘብኩ ይሄን ማሰቤ ትንሽ እረፍት ሰጠኝ ለካ ነገሮችን በችኮላ እና በቶሎ ከመወሰን በተረጋጋ ስሜት እራስን ማዳመጥ ለመፍትሄ እንደሚያደርስ ተረዳሁ ዋናው ነገር ደሞ " ሠው ያስብ እግዚአብሔር ይፈፅም "  እንደሚባለው ሀሳቤ እንዲፈፀም የእግዚአብሔር ጥላ እና ከበባ በኔ እና በቤተሰቤ ላይ እንዲሆን ፀለይኩ ።

  በንጋታው እህቶቼን ሳገኛቸው እንደ ትላንቱ ልቆጣቸው መስሏቸው ከፊታቸው ላይ የመሸማቀቅ ስሜት ተመለከትኩባቸው ነገር ግን ቀለል አድርጌ " ከዚህ በሗላ ለተወሰነ ጊዜያት አብረን በመሆን እኔም ጫማ እጠርጋለሁ እናንተም ቆሎ ትሸጣላችሁ ስለዚህ ስንሄድም አብረን ስንመጣም አብረን ነው የሚሆነው እኔ ካለሁበት አካባቢ ትሸጣላችሁ " አልኳቸው ፍቅርተ ከአፌ ቅብል አድርጋ " ማለት ትላንት ከልክለኸን አልነበር አሁን ፍቃደኛ መሆንህን እየገለፅክልን ነው እንዴ " አለቺኝ በጥርጣሬ መንፈስ እየገረመመቺኝ " አዎ አልቀለድኩም በዚሁ ውጥረት ውስጥ እያለን ለመቀለድ የሚያስችል አቅም የለኝም አማራጭ የሌለው ምርጫ ባይሆንብኝ ኖር ይሄን አልወስንም ነበር ክፉ ቀን እስኪያልፍ መተጋገዛችን ግድ ነው ግን አታስቡ ለጥቂት ቀን ብቻ ነው እግዚአብሔር እረድቶኝ የሆነ መፍትሄ አመጣለሁ " አልኳቸው ያልኩት ነገር ቢዋጥላቸውም ባይዋጥላቸውም ዝም ብለው እኔ ባልኩት ነገር ለመስማማት ሞከሩ ከዛ ከዛኑ ቀን ጀምሮ አብረን እኔ ከምሰራበት አካባቢ ሄድን የዛን ቀን የመጀመሪያ ቀናችን ስለሆነ ነው መሠለኝ ትኩረቴን ሰብስቤ ስራዬን መስራት አልቻልኩም አይኖቼ ወደዚህ ወደዛ እያሉ ቆሏቸውን ይዘው ወደላይ ወደታች ከሚንከራተቱት እህቶቼ ላይ ተተከለ....ይቀጥላል
#share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
3.2K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 15:02:59 ዝማሬ “ ከስንቱ ጠብቆ "
ዘማሪት ቤተልሔም ብዙነህ
የተለቀቀው Nov, 2022
Size 7MB
ርዝመት 8Min
Quality 128 kbps(High Quality)
Genres Gospel Song

ገራሚ ዝማሬ ነው ሰምታቹ ተባረኩበት
ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
1.3K viewsedited  12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 13:24:22 የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፵፯
@yanetmasra

ቀናት በጨመሩ ቁጥር ኑሮአችንም በዛው ልክ እየከበደ እንደ ዳገት አልገፋ አለ አንዳንድ ጊዜማ የሚላስ የሚቀመስም ይጠፋል እኔ የምሰራው ስራ ምንም በቂ ሊሆን አልቻለም የእናቴ አሠሪ የሆኑት ሠዎች በግ ይዘው ከመጡ ወዲህ ደብዛቸው ጠፍቷል አስቀድማ እንደነገረችን ከሆነ ሚስቲቱም የባሏን እጅ ነው የምትጠብቀው እንጂ ሌላ መተዳደሪያ የላቸውም አቅሟ ውስን እንደሆነ እና ማረግ ከምትችለው በላይ ማድረግ እንደማትችልም ነግራኛለች ደሞ ማድረግም ግዴታዋ አልነበረም ።
        አንድ ቀን ከትምህርት ቤት ስመጣ መሰረት እና ፍቅርተ ሠፋ ባለ ጎድጓዳ የወጥ መቀነሻ በሚመስል ሳህን ቆሎ ይዘው ተመለከትኳቸው ጠጋ ብዬ ወደነሱ ለመብላት እጄን ስዘረጋ " ተው ! " ብላ መሠረት ከለከለቺኝ " ለምን ? " ብዬ ጠየቅኳቸው ፤ ይህን ሁሉ ልትበይ ነው በሚል አመለካከት እየተመለከትኳት " ይሄ እኛ አንድንበላው የተዘጋጀ ሳይሆን እንዲሸጥ ተብሎ ነው የተሰጠን " አለቺኝ በድንጋጤ ተመለከትኳት ከመቼ ጀምሮ ነው ሻጭ  የሆኑት የሚል ጥያቄ ውስጤ ፈጥሮብኝ " ማነው ሽጡ ያላችሁ ? ለምንስ ትሸጣላችሁ ማለቴ ከመቼ ጀምሮ ? " ብዬ በቁም ነገር ጠየቅኳቸው " እማዬ ናት ከትምህርት ቤት ስንመለስ ፤ ' ከእንግዲህ በሗላ ከትምህርት ስትመጡ የውጭ ስራ መስራት አለባችሁ አሁን ህፃን ልጆች አይደላችሁም እኔ እናንተን ማስተዳደር ስለማልችል ፆማችሁን ላለማደር ስትሉ የግድ መስራት አለባችሁ ፤ ይህን ደም የምትጀምሩት ቆሎ በመሸጥ ነው ። ' ብላ አዘጋጅታ የጠበቀችንን ቆሎ እንድንሸጠው ሠጠችን ፤ ደሞ የት መሸጥ እንዳለብን ፣ ምን ማድረግ እንዳለብን ነግራናለች ስለዚህ ይህ ቆሎ የሚሸጥ ነው ። " ብላ አረፍተነገሯን ቋጨች



የሠማሁትን ነገር ማመን ከበደኝ አደባባይ ወጥተው ገና በታዳጊ እድሜያቸው ቆሎ ሲሸጡ ማየት ለኔ ከባድ ነው ሠካራሙ ፣ ዱርዬው ፣ በእድሜ ተልቆ በአስተሳሰብ የቀለለው ሁሉ መጫወቻ እንደሚሆኑ በአይነህሊናዬ ታየኝ ። ይህን ያልኩት እንዲሁ ከመሬት ተነስቼ አይደለም እኔ ጫማ የምጠርግበት አካባቢ ብዙ ጎዳና ተዳዳሪ የሆኑ ወላጅ የሌላቸው ህፃናት ፣ ቤተሰቦቻቸው ልጆቻቸውን ማስተዳደር ስለከበዳቸው እደጅ ወጥተው የሚሰሩ ልጆቻቸውን ስለማች በተለይ ሴቶቹን ምን ያህል ፈተናቸውን እንደሚያበዙት ስለማውቅ በሰው የምጠላው ነገር እህቶቼ ላይ ይደርሳል ብዬ ማሰቡ ሰቀጠጠኝ ማንኛውም ወንድም እህቱ የማይሆን ቦታ ስትገባ እያየ ዝም ማለት እንደማይችለው ሁሉ " እኔም  ፍቃዴን የጠየቁ ይመስል " " አትሄዱም " ብዬ ከለከልኳቸው ከነሱ አልፌ ከየት እንዳመጣሁት ባላውቅም እናቴን " እነሱ ወጥተው መስራት አይችሉም የቤቱንም ስራ እየሰሩ ስለሆነ የውጪውን መስራት ለነሱ አይታሰብም ፤ ደሞ በምን ጊዜ ሊያጠኑ ነው ትምህርት ቤት ውለው ፣ ቆሎ ሽጠው  የቤት ውስጥ ስራ ሰርተው " ብዬ ተናገርኩ በእርግጥ ይሄ ብቻ ሳይሆን ያሳሰበኝ በሴትነታቸው የሚደርስባቸውም ጥቃት ጭምር ነው ። ለእናቴ ግን ከምክንያቶቼ መካከል ይሄን ሳላካትት ነበር የነገርኳት " ያንተን ፍቃድ የጠየቀ የለም መኖር ከፈለጉ መስራት አለባቸው እንደድሮው ጉልበቷን አፍሳ የምታኖር እናት የለችም እዚው ተሽመድምዳ ቀርታለች ስለዚህ ሁሉም የድርሻውን መስራት እና እራሱን መምራት አለበት የምታመጣው ሽርፍራፊ ሳንቲም ቤቱን ቀጥ አድርጎ የሚያስተዳድር መስሎህ ከሆነ ተሳስተሀል እንኳን እሱ ቀርቶ ቀድሜ የሸመትኩት ሙጥጥ ተደርጎ ተበልቶ አልቋል ሌላ የገቢ ምንጭም ሆነ የሚረዳ ዘመድ የለንም ስለዚህ በማያገባህ አትግባ ልጆቹ ስራ ይስሩበት " አለቺኝ ....ይቀጥላል
#share

ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur
938 viewsedited  10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 13:22:23
Coming soon

@Mercy_ena_berua
883 views10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 20:52:03
ማዳን የእግዚአብሔር ነው። የምንወዳት እህታችን ዘማሪት መክሊት ግርማ Meklit Girma በደም ካንሰር ህመም በመታመም ላይ ስትሆን ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብታ ህክምና ብትጀምርም ወዲያውኑ ህክምና ማግኘት ባለመቻሏ እና ህመሙ እየከፋ በመምጣቱ በአስቸኳይ ከሀገር ውጭ መታከም እንዳለባት ተብሏል:: ይህ ደግሞ ከቤተሰቦቿ አቅም በላይ ስለሆነ የእህታችንን ሕይወት ለመታደግ የእናንተ ድጋፍ አስፈልጎናል ::

የምንችል
በፀሎት
በገንዘብ
Share በማድረግ

Gofundme እስኪከፈት
1, በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000229767503 መክሊት ግርማ ጊንጆ (ዘማሪት)

2, በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000020061457 ግርማ ጊንጆ ሰጠና ( ወላጅአባት)

3, ብርሃን ባንክ 1000675368220 ግርማ ጊንጆ ሰጠና

@KALTUBE
4.9K views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ