Get Mystery Box with random crypto!

አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center

የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የሰርጥ አድራሻ: @amhara_media_center
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.55K

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-19 19:02:07
በሶደሬ መድሐኒአለም ቤተክርስቲያን ዛሬ የደረሰ ውድመት። የቤተክርስቲያኑ አገልጋዮችም ታግተው መወሰዳቸውን ሰምተናል
2.7K views16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 16:40:07
#ጋዜጠኛ ሰናይት አያሌው ፍ/ቤት ቀርባ የ5 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባት!

የአማራ ሚዲያ ማእከል
ሚያዝያ 11 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በቀን 05/08/2015 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤቷ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ማንነታቸው ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ታፍና የተወሰደችው የአሻራ ሚዲያ ጋዜጠኛ የሆነችው ሰናይት አያሌው ከ6 ቀናት በኋላ ፍ/ቤት የቀረበች ሲሆን ፖሊስ ተጨማሪ 7 ቀናት እንዲሰጠው ቢጠይቅም ፍ/ቤቱ የ5 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ በመስጠት ለሚያዚያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ፍትህ ለጋዜጠኛ ሰናይት አያሌው!

ምንጭ አሻራ ሚዲያ
2.9K views13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 02:30:24
4.3K views23:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 01:25:28 “የአማራ ህዝብ የሚደርስበትን የዘር ማፅዳትና ማጥፋት እንዳመጣጣቸው በመደራጀት እንደ እስራኤላዊያን ባንድነት በመቆም መታገል ይጠበቅበታል፡፡” ባልደራስ

የአማራ ሚዲያ ማዕከል
ሚያዚያ 10 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ

አማራን ለማጽዳት የሚካሄዱ እርምጃዎችን ህዝቡ እንደ አመጣጣቸው መልሶ እንደ እሰራኤላውያን ታላቅነቱን ያሳያል።

ህወሓት መራሹ ሥርዓት የጎሳ ፓለቲካን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ከተከለበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ዜጎቻችን ለዘር መፅዳት እና ለዘር መጥፋት ተዳርገዋል። በተለይ ደግሞ ላለፉት አምስት ዓመታት ያለሟቋረጥ የንፁሃን አማራዎች ደም በወለጋ፣ በቤኔሻንጉል ጉሙዝ፣ በምእራብ ሸዋ፣ በአርሲ፣ በባሌ፣ በሀረር፣ በሻሸመኔ፣ በአጣዬ፣ … ያለ ማንም ከልካይ እየፈሰሰ ይገኛል። ዛሬም የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ እንዲጠፋ ስልታዊ በሆነ መንገድ በኦህዲድ/ኦነግ የብልፅግና መንግሥት ሴራ እየተፈፀመበት መሆኑን ለመረዳት የፖለቲካ ልሂቅ መሆንን አይጠይቅም፤ ነገሮች ግልፅ እየሆኑ መጥተዋልና።

በወልቃይት ከሚገኙት ከአራት የአማራ ልዩ ኃይል ብርጌዶች ሦስቱ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ የተደረጉ ሲሆን፣ ‹‹ልዩ ኃይሉን መልሶ ለማደራጀት ነው›› የሚባለው የሀሰት ፕሮፓጋንዳ እውነትነት እንደሌለው እና ህዝቡ ለፅንፈኛ ኃይሎች እየተጋለጠ እንደሆነ ማሳወቅ እንወዳለን፡፡ የአማራ ልዩ ኃይልን መፍረስ እና መበተን ተከትሎ በጎንደር ፍየል-ውሀ እና በማይጠምሪ አካባቢ ህወሓት ኃይሏን እያስጠጋች መሆኗን ከሚደርሱን መረጃዎች ለማረጋገጥ ችለናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በጭልጋ አካባቢ የቅማንት ፅንፈኛ አካል ኃይሉን እያደራጀ ሲሆን፣ የአገው ሸንጎንም በኦህዲድ/ኦነግ ብልፅግና መንግሥት ድጋፍ እየተደራጀ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

በአጠቃላይ የኦህዲድ ብልፅግና መራሹ ሥርዓት የጎሳ ፓለቲካ ሀ፣ሁን ካስተማረው ከህወሓት እና ተመሳሳይ አቋም ካላቸው ከሌሎች የውስጥ እና የውጭ ኃይሎች ጋር በመተባበር የአማራን ህዝብ ድምጥማጡን ለማጥፋት ቀን ከሌት እየባዘነ ይገኛል፡፡ ሚያዚያ 05/2015 ዓ.ም. ከደሴ ወደ ሸዋ ሮቢት ሲጓዙ የነበሩ ትጥቃቸውን የፈቱ የአማራ ልዩ ኃይሎች ላይ ፅንፈኛው የኦነግ-ሸኔ ታጣቂ ግፍ በተሞላበት መንገድ ያደረሰው ጭፍጨፋ በአስረጅነት ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በወለጋ በአንገር ጉተን ወረዳ ሚያዚያ 05/2015 ዓ.ም. ኦነግ ሸኔ ተብሎ በዳቦ ስሙ በሚጠራው የብልፅግና ኦህዲድ/ኦነግ የጫካ ክንፍ ከአራት መቶ በላይ አማራዎች ጥቃት ደርሶባቸዋል፡፡ ለሠላሳ ሁለት ዓመታት በዚህ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት እና ማፅዳት ሲፈፀም አማራ ባይሆን ማን ይችለው ነበር? ገዥው ብአዴን ባይሆን ማን ህዝቡን እንዲህ ያስጨፈጭፈው ነበር? ግፉ በዝቷል፣ በቃ ማምረር ይገባል፡፡

በመሆኑም፦

➣የኦህዴድ ብልፅግና መራሹ ሥርዓት በአማራ ክልል ለዘመናት ተዋደውና ተከባብረው የሚኖሩትን ብሔረሰቦች የፅንፈኝነት አስተሳሰብ በማላበስ በአማራው ላይ በጠላትነት እንዲነሱ በማድረግ እና ክልሉን በማዳከም በኢትዮጵያ በአንደኛ ደረጃ የሚገኘውን የአማራ ህዝብ ቁጥር ወደ አናሳ /minority/ ቁጥር ማውረድ ተቀዳሚ ዓላማ ነው፡፡ መላው የአማራ ህዝብም ይህንን የገዥውን ፓርቲ ዓላማ ተረድቶ ትግሉን ህዝባዊ እንዲያደርግ ፓርቲያችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡

➣ ህወኃት በሰሜን እዝ ላይ በፈፀመው ግፍ ለፍርድ መቅረብ ሲገባው የኦህዲድ ብልፅግና መንግሥት ግን ከተቀበረበት ጉድጓድ አውጥቶ ለሥልጣን አብቅቶታል፡፡ የህወኃት እና የኦህዲድ ብልጽና ጋብቻ የሚያመለክተው ሥርዓቱ ለመከላከያ ኃይል ደህንነት እና መስዋዕትነት ቅንጣት ያህል ስሜት እንደሌለው ነው፡፡ ስለዚህ የመከላከያ ሠራዊት በወገንህ ላይ ምንም አይነት ቃታ እንዳትስብ እናሳስባለን፡፡

➣የብልፅግና መንግሥት የፅንፈኛ ኦነጋውያንን አስተሳሰብ ስለሚያራምድና አድሎአዊ ስለሆነ የአማራን ህዝብ ለመጠበቅ የሚያስችል ቁመና የለውም፡፡ በመሆኑም የአማራ ህዝብ ለፅንፈኞች ተጋላጭ እንዳይሆን ፋኖ፣ የአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ ትጥቃችሁን መፍታት እንደሌለባችሁ ደግመን እናስገነዝባለን፡፡

➣የአማራ ህዝብ ሆይ - ለሠላሳ ሁለት ዓመታት የሚወክልህ ዕውነተኛ የመንግሥት ተጠሪ ስለሌለህ ከብአዴን/ብልፅግና የሚወጡ ፕሮፓጋንዳዎችን ማዳመጥ የለብህም፡፡ እግር ከወረች አስሮ የሚያስጨፈጭፍህ ብአዴን/አማራ ብልፅግና እንደሆነ አውቀህ የአማራ ክልል ባለሥልጣናት እስካሁን ባንተ ላይ ያደረሱብህን በደልና ግፍ ቆጥረህ በህግ ተጠያቂ እንደምታደርጋቸው ልታሳውቃቸው ይገባል። በሰላማዊ መንገድ የጀመርከውን ትግል ውጤት እስከምታገኝበት ድረስ ባለማቋረጥ እንድታቀጣጥለው ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

➣ሰላማዊ ዜጎችን የሚጨፈጭፍና የተረፉትንም የሚያፈናቅል፣ ንብረትን የሚያወድምና ከተሞችን የሚያነድ ኦነግ-ሸኔን አሽሞንሙኖ የያዘ ክልል፣ ሀገርን የታደጉትን ፋኖን እና ልዩ ኃይልን ሊያወግዝ የሚያስችል የሞራል ብቃት እንደሌለው በመረዳት የአማራ ትግል መዳረሻ ሥርዓቱን እና ባለስልጣናቱን ሙሉ በሙሉ መቀየር እንደሆነ በማለም ለየትኛውም ፈተና ሸብርክ እንዳትል እና ገዥዎች ለማጭበርበሪያ የሚጠቀሙበትን የሽምግልና ሥርዓት እንዳትቀበል እናሳስባለን፡፡

➢የብልፅግና መንግሥት ዕድሜውን ለማራዘም ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል አንዱ የሰሜኑን ክፍል (አማራን እና ትግሬን) ማጋጨት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ይህ እኩይ ዓላማው እንዳይሳካ ለማድረግ የሁለቱ ክልል ነዋሪዎች፣ የታችኛው የመንግሥት አመራሮች፣ ምሁራን እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የሚጠበቅባችሁን ሓላፊነት እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

➢በአማራ ህዝብ ላይ ለዘመናት ሲደርስበት የነበረውን እና እየደረሰበት ያለውን ግፍ ለመቋቋም የአማራ ህዝብ ለሚያደርገው ትግል መላው ኢትዮጵያውያን ከጎኑ እንዲቆሙ እንጠይቃለን፡፡

➢የአማራ ህዝብ የሚደርስበትን የዘር ማፅዳትና ማጥፋት እንዳመጣጣቸው በመደራጀት እንደ እስራኤላዊያን ባንድነት በመቆም መታገል ይጠበቅበታል፡፡

➢የህወኃት ርዕዮት ዓለም ወራሽ የሆነው የብልፅግና መንግሥት - ታሪክ እና ቅርስ ጠል፣ አድሎአዊ፣ ጠባብ ብሔርተኛ፣ የሰብአዊና የዲሞክራሲያዊ መብቶች ረጋጭ፣ ጨፍጫፊ፣ … አምባገነን ሥርዓት መሆኑን ያሳለፍናቸው አምስት ዓመታት ምስክሮች ናቸው፡፡ እነዚህ በአመራሩ ላይ ያሉ ሀገር አፍራሽ ፋሽስታዊ ስብስቦች የትኛውንም ማኅበረሰብ ስለማይወክሉ የኦሮሞ ህዝብ አብሮህ ከኖረው እና ከሚኖረው ከአማራ ወገኖችህ ጋር በመቆም ይህን ዘረኛ ሥርዓት እንድትታገለው ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
27 views22:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 18:42:42
1.7K views15:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 18:23:32 በሱዳን ኦምዱርማን ከተማ የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ አራት ኢትዮጵያዊያን ተገደሉ

የአማራ ሚዲያ ማእከል
ሚያዚያ10 2915 አ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በጦርነቱ በካርቱም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይ ጥቃት ደርሷል

አራተኛ ቀኑን በያዘዉ የሱዳን የከተማ ዉስጥ ጦርነት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል እና የሀገሪቱ ጦር ዉግያ ዉስጥ ይገኛሉ። በርካታ ኢትዮጵያዊያን መኖሪያ በሆነችዉ ሱዳን ኢትዮጵያዊንም ህይወታቸዉ እንዳለፈ ተሰምቷል።

በሱዳን 12 አመታትን የቆየዉና አስተያየቱን የብስራት ራዲዮ ምንጭና የጤና ባለሙያዉ አቶ ወንድወሰን ጌትነት ፤ ከትናንት በስቲያ 11 ሰዓት ከ 30 አካባቢ ኦምዱርማን በተሰኘዉ አካባቢ በጦርነቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ አራት ኢትዮጵያዊያን በጦር ጄት ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን ተናግሯል። እስካሁን ከ 10 በላይ ኢትዮጵያዊያን በጦርነቱ ሞተዋል ያለን አስተያየት ሰጪያችን ፤ በትናትናዉ እለት በካርቱም ( ጅሬፍ ) በደረሰ ሌላ ጥቃት ፤ ባለትዳሮች ህይወታቸውን ሲያጡ የሶስት አመት ህጻን ልጃቸዉ ከጥቃቱ ተርፏል ብሏል።

በተጨማሪም በካርቱም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይም ጥቃት መድረሱን ገልጿል። የትኞቹ ታጣቂዎች እንደፈጸሙት ባያረጋግጥልንም የኤምባሲዉን ቅጥርግቢ ጥሰዉ በመግባት በግቢዉ በሱዳን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ባለቤት በሆነበት የመጠለያ ማዕከል ዉስጥ በነበሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ አጸያፊ ተግባራት ጭምር መፈጸማቸዉን ተናግሯል።

የኤምባሲዉ ጥበቃዎች በጦርነቱ ወቅት ከግዳጅ ቦታቸዉ በመነሳታቸዉ የተባለዉ ጥቃት ደርሷል። ታጣቂዎቹም ገንዘብን ጨምሮ ዘረፋ መፈጸማቸዉን ነዉ የተናገረዉ።

በሱዳን ያለዉ ሁኔታ አስከፊ መሆኑን የገለጸልን የመረጃ ምንጭ በዋና ከተማዋ ካርቱም ከፍተኛ ዝርፊ መስፈኑንም ጨምሮ ለብስራት ራዲዮ ተናግሯል። ብስራት ራዲዮ በካርቱም የኢትዮጵያ ኤምባሲን ለማግኘት ሙከራ እያደረገ ነዉ።
ምንጭ
ዳጉ_ጆ
1.8K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 18:04:30
አማራው ጀማል በአማራዊ ማንነቱ ምክንያት በግፍ ተገደለ

የአማራ ሚዲያ ማዕከል
ሚያዚያ 10 2015 አ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ወጣት ጀማል አህመድ ተወልዶ ያደገው በዚሁ በወለጋ በአንገር ጉትን አርቁምቢ መንደር 2 ቀበሌ ሲሆን ተወልዶ ባደገበት አከባቢም የታወቀ የስራ ሰው፣ ሰው አክባሪ እና ታታሪ ነው።

ጀማል ገና በልጅነቱ በስራ፣ በማህበራዊ ህይወት የመቻቻልና የመግባባት ባህል ውስጥ የህዝብ ለህዝብ ግንኙትን በፍቅር ያስተሳሰረ የህዝብ ልጅ ነበር።

ጀማል ከግብርና ስራው በተጨማሪ ጎበዜ፣ ታማኝ ነጋዴም ነው። ፍልቅልቅ፣ሳቂታና ተጨዋችም ነው። በተፈጠረው ሐገራዊና አካባቢያዊ ቀውስ ለዘመናት ከኖረበት ቀዬው ተፈናቅሎ በአንገር ጉትን መኖር ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል።

ወጣት ጀማል አህመድ ወይም በቅጽል ስሙ ጀማል አባጥሩ እየተባለ የሚጠራ ሲሆን በአከባቢው ደግሞ ጀማል አርቁቢ እየተባለ የሚጠራ ሐገርና ሰው ወዳድ ጀግና ነበር።

ሆኖም ግን ወጣት ጀማል ሚያዚያ 06-2015ዓ.ም በእለተ አርብ ከመኖሪያ ቤቱ እንዳለ ከባለቤቱ እና ከልጆቹ ፊት በጨካኝ አረመኔ እኔ ቂመኛ አክራሪ ጽንፈኛ በሆኑ አብሮ በኖራቸው በየ #አዱኛ በሊና በተባለው ቀንደኛ የኦነግ ሸኔ ክንፍ በጉትን ከተማ እቤቱ ድረስ በመሔድ ተማሪ የመከላከያ ሠራዊት አጃቢ በመያዝ በግፈኞች በተተኮሰበት በግፍ ተገደለ።

ለጀግናው፣ ለወጣቱ ነጋዴና ቱሁቱ ጀማል መገደል ሬንጀር የለበሰ ይከተሉንጂ ገዳዩ ይሔው በዘረኝነት በሰከረው ግለሰብ መሆኑ ደግሞ እጅጉኑ አሳዛኝ አድርጎታል። ምንጭ አጉልዞ ጥያቄ
1.7K views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 17:21:42 «የኢትዮጵያ መንግስት የመገናኛ ዘዴ ባለሙያዎችን ይልቀቅ» አምንስቲ

የአማራ ሚዲያ ማእከል
ሚያዚያ 10 2015 አ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዉሞን በሰላማዊ ሰልፍ የመግለፅ መብትን እንዲያከብርና የታሰሩ የመገናኛ ዘዴ ባለሙያዎችን እንዲፈታ አምንስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ።

ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ትናንት ማምሻ ባወጣዉ መገለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ባለፈዉ ሳምንት አማራ ክልል በተፈጠረዉ “ሁከት “ምክንያት ያሰሯቸዉን 7 የመገናኛ ዘዴ ባልደረቦች ባስቸኳይ እንዲፈቱ፣ ከእስረኞቹ ባንዷ ላይ ተፈፀመ የተባለዉን አካላዊ ጥቃት እንዲያጣሩ ጠይቋል።መግለጫዉ እንዳለዉ ባለስልጣናቱ «ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትንና ሁሉም ወገን በሰላማዊ መንገድ የመቃወም መብቱን ማስከበር አለባቸዉ።»

ባለፈዉ ሳምንት በአማራ ክልል የመብት ጥሰትና ሁከት መቀስቀሱ እንዳሳሰበዉ የመብት ተሟጋቹ ድርጅት አስታዉቋል።በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተኩስ ልዉዉጥ መደረጉ፣ የሰብአዊ ርዳታ አቀባይ ድርጅት ሰራተኞችን ጨምሮ ሰዎች መገደላቸዉ፣ አዲስ አበባ ዉስጥ ሰዎች በጅምላ መታሰራቸዉንም ድርጅቱ «አሳሳቢ» ብሎታል።

የመንግስት ኃይላትም ሆኑ ሌሎች ታጣቂዎች «የሰብአዊ ርዳታ ሰራተኞችን ያለማጥቃት ኃላፊነት አለባቸዉ።» ይላል መግለጫዉ።የኢትዮጵያ መንግስት «አስቸኳይ፣ጥልቅ፣ገለልተኛና ዉጤታማ ምርመራ አድርጎ ተጠያቂዎችን ለፍርድ ማቅረብ አለበት» እንደ መግለጫዉ።

በምስራቅ አፍሪቃ፣በአፍሪቃ ቀንድና በታላላቅ ሐይቆች አካባቢ የአምንስቲ ኢንተርናሽናል ምክትል ተጠሪ ፍላቪያ ምዋንጎቭያ «ዘግናኝ» ያሉት የገነት አስማማዉ፣ ጌትነት አረጋዊ፣አራጋዉ ሲሳይ፣መስከረም አበራ፣አባይ ዘዉዱ፣ ዳዊት በጋሻዉና ቴዎድሮስ አስፋዉ መታሰር ሐሳብን በነፃነት በመግለጥ መብትና በመገናኛ ዘዴ ነፃነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ነዉ።የኢትዮጵያ ባለስልጣናት 7 የመገናኛ ዘዴ ሰራተኞች ባስቸኳይ እንዲለቁና የተመሰረተባቸዉን ክስ እንዲነሱም ምዋንጎቭይ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በተመረጡ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ የጣለዉን ማዕቀብ እንዲያነሳም ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ጠይቋል።አምንስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለዉ የኢትዮጵያ መንግስት እገዳዉን ከጣለ 3ኛ ወሩን ይዟል።እገዳዉ ሰዎች መረጃ እንዳያገኙ መገደብን ጨምሮ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን የመጠቀምና ያለመጠቀም የሰብአዊ መብትን የሚጥስ ነዉ ሲል DW ዘግቧል::
2.0K views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 16:59:04
የአማራ ልዮ ሀይልን ትጥቅ የማስፈታትን እቅድና በአማራነታቸው ብቻ እየተመረጡ እየታሰሩ ስላሉት ጋዜጠኞች በመቃወም በጀርመን ሀገር ከአሜሪካ ኢምባሲ ፊት ለፊት እየተደረገ ያለ የተቃውሞ ሰልፍ።

ድል ለተገፋው ለአማራ ህዝብ!
3.5K views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 13:04:15
መረጃ
ጋዜጠኛ ገነት አስማማው በ10ሺ ብር ዋስትና እንድትለቀቅ ፍ/ቤቱ ወስኗል።
3.7K views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ