Get Mystery Box with random crypto!

አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center

የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የሰርጥ አድራሻ: @amhara_media_center
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.55K

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2023-03-31 22:25:54 "ጋዜጠኛ ጌትነት አሻግሬ
በአማራ ጠሉ ስርዓት የአማራን ህዝብ በደል ማጋለጥና መዘገብ አሳዳጅን የሚያበረክት ነገር ነውና ይሄው እጣ ወድቆበት ከሰሞኑ ወደ እስር ተወርውሯል።"

ጋዜጠኛ እና መምህርት መስከረም አበራ

አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ
መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ሸዋ

ጌትነት አሻግሬ ይባላል፣ወንድማችን ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በመሰረተው "የአማራ ድምፅ" በተሰኘው ሚዲያ ላይ በጋዜጠኝነት ይሰራል።

ጌች በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ማለቂያ የለሽ የመከራ ዶፍ በየጉራንጉሩ እየገባ የሚዘግብ፣ የአማራ ህዝብ ዘር ተኮር ጥቃት የሚያንገበግበው ድንቅ ጋዜጠኛ ነው!

ጌትነት ወለጋ ተወልዶ ያደገ ኦሮምኛ አቀላጥፎ የሚናገር አማራ ነው።

በመሆኑም የአማራውን ዘር ተኮር ጥቃት በወሬ ሳይሆን በህይወቱ ያየ ልጅ ነው።

የአማራውን መከራ ለማጋለጥ ደከመኝ ሰለቸኝ የማይለውም ለዚሁ ይመስለኛል።

ጌች የአማራ ህዝብን በደል ለማጋለጥ ጋራ ሸንተረር የሚባዝን፣ህይወቱን ለአደጋ አጋልጦ እጅግ አደገኛ ቦታዎች ሳይቀር እየገባ የሚዘግብ፣ትልቅ ተስፋ የሚጣልበት ጋዜጠኛ ነው።

የዚህ ወንድማችን ለወገን እንግልት የመንገብገብ "energy" ምነው ለሁሉም አማራ "Apply to all" ማለት ቢቻል ብዬ ተመኝቼ አቃለሁ። በዚህ ላይ ፀባዩ ድንቅ ነው።

ሰው አክባሪ፣ታዛዥ፣ለጋራ አላማ ለመስራት የሚያስፈልጉ ግላዊ ባህሪያትን የተላበሰ ልጅ ነው።

በአማራ ጠሉ ስርዓት የአማራን ህዝብ በደል ማጋለጥና መዘገብ አሳዳጅን የሚያበረክት ነገር ነውና ጌችም ይሄው እጣ ወድቆበት ከሰሞኑ ወደ እስር ተወርውሯል።

ሆኖም የስራውን ያህል አላወቅነውምና "ይፈታ!" የሚሉ ድምፆች አይሰሙም።

የጌችን ስራዎች ለማየት የሚፈልግ ሁሉ የአማራ ድምፅ ሚዲያን "You Tube" እና ቴሌግራም ገብቶ መጎብኘት ነው።

ልጁ "ይፈታ!" ማለት የሚያንስበት ባለውለታ መሆኑን ወዲያው ይረዳል።
2.4K views19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 17:19:55 የአርበኛ ደረጀ በላይ እና ሻለቃ አይሸሽም ዮሐንስ ላይ ምን ተፈጸመ?የአርበኛ ዘመነ ካሴ መልዕክት https://youtube.com/live/4UqqfcleqiA?feature=share
2.8K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 22:25:28 ጋዜጠኛ መስከረም አበራ፣ ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናው፣ ጋዜጠኛ አዲሱ ደርቤ፣ደራሲ ይሁኔ አወቀ፣ አቶ የቆየ ሞላ.....እኔም ለወገኔ! https://youtube.com/live/RHrYU-i9ZJc?feature=share
3.5K views19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 19:11:15
የአማራ ፋኖ በጎንደር የናደው ሻለቃ መሪዎች አርበኛ ደረጀ በላይ እና ሻለቃ አይሸሽም ዮሐንስ ከደምቢያ ወረዳ አመራሮች ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ተለቀዋል፤ የፋኖዎች የምክክር መድረክ ግን ተከልክሏል።

አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ
መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ሸዋ

የአማራ ፋኖ በጎንደር የናደው ሻለቃ መሪዎች አርበኛ ደረጀ በላይ እና ሻለቃ አይሸሽም ዮሐንስ ስብሰባ አታደርጉም የሚል ክልከላ ከደምቢያ ወረዳ አመራሮች የገጠማቸው መሆኑ ታውቋል።

አማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) መጋቢት 21/2015 ረፋድ ላይ እንዳጣራው
1) ከሰቀልት አይምባ፣
2) ከቆላድባ እና
3) ከጯሂት ተጓጉዘው ከመጡ ፋኖዎች ጋር ሊደረግ የነበረው የምክክር መድረክ ከመስተጓጎሉ አልፎ ከበላይ በመጣ ትዕዛዝ በሚል ተከልክሏል።

አሚማ ስብሰባውን ለማካሄድ በዝግጅት ላይ እያሉ ወደ እስር ተወስደዋል የተባሉትን የአማራ ፋኖ በጎንደር የናደው ሻለቃ መሪዎች አርበኛ ደረጀ በላይ እና ሻለቃ አይሸሽም ዮሐንስን ለማግኘት ጥረት አድርጓል።

ወደ ቢሮ ተወስደን ከደምቢያ ወረዳ አመራሮች ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ተለቀናል፤ ስብሰባውም እንዳይካሄድ ተከልክሏል ያለው ሻለቃ አይሸሽም ዮሃንስ ነው።

ወቅቱ የበለጠ አንድነታችን ማጠናከር ያለብን ጊዜ ላይ መሆናችንን ታሳቢ በማድረግ ከአባላት ጋር የሚደረገውን ምክክር ለሌላ ጊዜ ለማራዘም ተገደናል ብሏል።

መሰብሰብ መብት እንጅ ወንጀል አለመሆኑን የጠቀሰው ሻለቃ አይሸሽም "ያለንበት ሁኔታ ካልገባቸው እስኪገባቸው ድረስ ተነጋግረን በሌላ ጊዜ ስብሰባችን እናስኬዳለን" የሚል አቋም መያዛቸውን ተከትሎ ተሰብሳቢዎች ወደየመጡበት እንዲመለሱ ማደረጋቸውንም ተናግሯል።
3.5K views16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 11:36:56 በአናሆሮ ወረዳ የኤርፈንቲ ገበር ቀበሌ አማራዎች አዋሳኝ ወደሆነው አቢደንጎሮ ወረዳ ለግብይት በሄዱበት በመንግስት የጸጥታ አካላት እየታሰሩ በመሆኑ መቸገራቸውን ገለጹ።

አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ
መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ሸዋ

በሆሮ ጉድሩን ወለጋ ዞን አናሆሮ ወረዳ ኤርፈንቲ ገበር ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ አማራዎች ለህክምና፣ ለግብይትም ሆነ ለሌላ ስራ ጉዳይ ከርቀቱ እና ከአሸባሪ ኦነጋዊያን የመንገድ ላይ ጥቃት የተነሳ ወደ ወረዳው ማቅናት አይችሉም።

ያለፈው ቅዳሜ መጋቢት 16/2015 ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ ከ100 በላይ የሚሆኑ አሸባሪ ኦነጋዊያን ወደ ኤርፈንቲ ገበር በማቅናት ተኩስ ከፍተው እንደነበር ተገልጧል።

ከሀሮ ሾጤ ቀበሌ ወደ ገርች ወንዝ በመምጣት ወደ ቢንኩ በመተኮስ ጥቃት ለመፈጸም ስለመሞከራቸው
የኤርፈንቲ ገበር ነዋሪዎች ለአማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) ተናግረዋል።

ከአናሆሮ ወረዳ ኤርፈንቲ ገበር ቀበሌ ለአቢደንጎሮ ወረዳ ጎረቤት
በመሆኑ የግብይት ልውውጥ እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎቶችን የሚያገኙት ወደ አካባቢው በማቅናት መሆኑ ተገልጧል።

ይሁን እንጅ በተለይ ከሰሞኑ ከኤርፈንቲ ገበር ወደ አቢደንጎሮ ለግብይት የሄዱ አማራዎችን የአካባቢው ፖሊስ እና የፌደራል ፖሊስ እየያዘ እያንገላታ ተቸግረናል
የሚሉት ምንጮች እንደአብነት በእለተ ሰኞ መጋቢት 18/2015 ሰባት የኤርፈንቲ ገበር አማራዎች ለወፍጮ በሄዱበት ታፍነው ስለመታሰራቸው ጠቁመዋል።

በአቢደንጎሮ በግፍ እስር ላይ የሚገኙ አርሶ አደሮችም:_

1) እንድሪስ ገ/ህይወት፣
2) ሰይድ መኮንን፣
3) መሀመድ እባቡ፣
4) እንድሪስ መኮንን፣
5) የሱፍ አራጌ፣
6) መሀመድ አስፌ እና
7) ሰይድ አስፌ መሆናቸው ተነግሯል።

አንዳንዶች እንደሚሉት በኤርፈንቲ አማራዎች ላይ የተደራጁ አሸባሪ ኦነጋዊያን ጥቃት ሊፈጽሙ በሄዱበት ወቅት ከቡድኑ የተጎዳ አለ በሚል ቁጣ ቢሮ ላይ ያለው ኦነግ እየተበቀለ ስለመሆኑ ይናገራሉ።

የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አባላትም በሚያገኙን አካባቢ ሁሉ እያሳደዱን በመሆኑ ለችግራችን መፍትሄ ሊፈለግልን ይገባል ሲሉ ጥሪ አድርገዋል።
3.3K views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 11:36:27
በእነ ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ እና ጌትነት አሻግሬ ቤት ፍተሻ ተደርጓል፤ ተጠያቂ ሊያደርግ የሚችል አንድም ነገር አልተገኘም ተብሏል።

አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ
መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ሸዋ

ፌደራል ፖሊስ መጋቢት 20/2015 ረፋድ ላይ በእነ ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ እና ጌትነት አሻግሬ ቤት ፍተሻ አድርጓል።

ነገር ግን ጋዜጠኞችን ተጠያቂ ሊያደርግ የሚችል አንድም ነገር አልተገኘም ተብሏል።

በጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ አራት የፌደራል ፖሊስ አባላት የዐይን እማኞችን ከጎረቤት በማካተት ፍተሻውን አድርገው ተመልሰዋል ተብሏል።

የሮሃ ኒውስ ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ እና የአማራ ድምጽ ሚዲያ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ መጋቢት 17/2015 በፌደራል ፖሊስ ከመኖሪያ ቤታቸው ተይዘው ወደ ሜክሲኮ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዳቸው ይታወሳል።
2.9K views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ