Get Mystery Box with random crypto!

አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center

የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የሰርጥ አድራሻ: @amhara_media_center
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.55K

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-07 18:14:47
1.3K views15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 18:14:39 ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ “ሁከት እና ብጥብጥ” የሚል የሀሰት ክስ ቀረበበት።

‹የጦር መሳሪያዎችን በመያዝ ተልዕኮ ተቀብለው የመንግስትስ ከፍተኛ አመራሮችን እና ታዋቂ ሰዎች ላይ እርም ለመውሰድ ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት ህገመንግስቱን እና ህገመንግስታዊ ስርአቱን በሀይል ለመናድ...› አቃቢ ህግ

‹የቀረበብን ክስ ሳይሆን ስድብ ነው። ምሁራንን በእንዲህ አይነት ተራ ወንጀል መጠርጠር አለማወቅ ነው› የህሊና እስረኞች

የአማራ ሚዲያ ማዕከል
መጋቢት 29 2015 አ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የአማራ ሚዲያ ማዕከል ዋና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ ከሌሎች 8 ሰዎች ጋር የሀሰት ክስ ቀረበበት።

በትናንትናው ዕለት መጋቢት 28 2015 ዓ/ም በፖሊሶች ለጥያቄ እንፈልግሀለን በሚል የተወሰደ ሲሆን ከሰአት በኋላ አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ከሌሎች 8 የህሊና እስረኞች ጋር “ሁከት እና ብጥብጥ” መፍጠር በሚል የሀሰት ውንጀላ ቀርቦባቸው ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ፋይል የተከፈተባቸው የህሊና እስረኞች

1 ሰይፈ ተስፋዬ ተፈሪ
2 ማስረሻ እንየው ታረቀኝ
3 ታደሰ ወዳይነው ተሰማ
4 ታደለ መንግስቱ ጉዳይ
5 ጌታቸው ወርቄ አያሌው
6 አንደበት ተሻገር ታደሰ
7 አለልኝ ምህረቱ አድገህ
8 አባይ ዘውዱ ደመቀ
9 ዶክተር አሰፋ ደሞዜ ሲሆኑ

አቃቢ ህግ ያቀረበው የሀሰት ውንጀላ “የራሳቸውን የፖለቲካ አላማ እና ፍላጎት ለማሳካት አስበው የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀምና በተለያዩ መንገድ በመገናኘት ህገወጥ አደረጃጀት በመፍጠር ወጣቶችን ለወንጀል ተግባር በመመልመል እና

በማደራጀት ወጣቶችን ለአመፅ በማነሳሳት በሀገሪቱ መረጋጋት እንዳይኖር ግጭት እንዲነሳ በማሰብ በአዲስ አበባ ከተማ እና በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀስ በህገወጥ መንገድ ወጣቶችን በህቡዕ እየመለመሉ በማደራጀት የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን በማስታጠቅ በተለያዩ ቦታ ከሚንቀሳቀሱ ለአመፅ ተግባር ከተደራጁ ኢ መደበኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር

የመለመሏቸውን ወጣቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ እንዲወስዱ በማድረግ በህገወጥ መንገድ ቡድኑን ከሚመሩ አመራሮች ጋር በመገናኘት በአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች እና በአዲስ አበበአ ከተማ ህዝብ በመንግስት ላይ አመኔታ እንዳይኖረው ለማድረግ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን በመያዝ ተልዕኮ ተቀብለው የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችን እና ታዋቂ ሰዎች ላይ እርም፡ ለመውሰድ ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት

ህገመንግስቱን እና ህገመንግስታዊ ስርአቱን በሀይል ለመናድ ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ በተደረገ ክትትል ከቀን 26/07/15 ዓ/ም ጀምሮ በቁጥጥር ስር ውለው በምርመራ ክፍላችን በ እስር ላይ ይገኛሉ” ይላል በሀሰት የተቀነባበረው ክስ።

በሀሰት የቀረበባቸው ውንጀላ የሰሙት የህሊና እስረኞችም ለፍርድ ቤቱ የሚከተለውን ብለዋል
። መንግስት ከሕዝብ አመኔታ የሚያጣም ሆነ የሚያገኘው በሚሰራው ስራ እንጅ ፌስቡክ ላይ በሚለጠፍ ሀሳብ አይደለም፣

ህገመንግስት የሚናደውም የሚፀናውም በራሱ የመንግስት አስተዳደር እንደሆነ፣ እኛ በሀሳብ ሞግተን ማሳመን የምንችል እና የተሰራ ሀሳብ ለሚያቀርብልንም ሀሳቡን ለመቀበል ጭንቅላታችን ዝግጁ ስለሆነ የብጥብጥ ስራ ላይ አንሰማራም፣

ለአማራ ህዝብ ከታሰበለት የአማራ ምሁራንን ለቃቅሞ ማሰር ሳይሆን የሚገደለውን አማራ እንዳይገደል ማድረግ እንዳይፈናቀል ማድረግ ነው፣በጥቅሉ እኛ ላይ የቀረበው ክስ ስድብ ነው ከምንለው በቀር እንዲህ ያለ ለከስካሳ ስራ ላይ አንሰማራም። ከሀሳባችንም የለም ።

ምሁራንን በእንዲህ አይነት ተራ ወንጀል መጠርጠር አለማወቅ ነው። የሙያ ስራዎች ሚዲያ ላይ የሚወጡት የሙያ ግዴታችንን ለመወጣት እንጅ ማንንም ለማስጠላት አይደለም።መንግስት የሚጠላውም የሚወደደውም በሚሰራው ስራ ብቻ ነው የሚል ምላሽ ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል።

ፍርድ ቤቱ አቃቢ ህግ ያቀረበውን የሀሰት ውንጀላ በመስማት 14 ቀን የምርመራ ግዜ ፈቅዷል።

ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ የአማራ ሚዲያ ማዕከል ጋዜጠኛ ሲሆን በአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰው መጠነ ሰፊ ጥቃት በመዘገብ ለህዝብ በማድረስ ግፍን የሚያጋልጥ : ለህዝብ ድምፅ የሚሆን ብርቱ ጋዜጠኛችን ነው።

ከዚህ በፊትም ለተደጋጋሚ ግዜ የታሰረ ሲሆን ፀረ አማራ ስርአት የሚመራው መንግስት ጋዜጠኛ ዓባይን በማፈን የህዝብ ድምፅ እንዳይሆን ማድረግን ያለመ አፈና አካሄዶበታል።

የብልፅግና መንግስት የነቁ እና አማራ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ የተረዱ ምሁራንን በማፈን ላይ መጠመዱ አማራን ማሳዳድ መንግስታዊ መመሪያ መሆኑ የሚያሳይ ብሎም ስርአቱ የገባበትም ፍርሀት እና አጣብቂኝ መገለጫ መሆኑ በምሁራን ተገልጿል።
1.3K views15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 18:12:36
በወልዲያ እና መርሳ ከተሞች መንገድ እና ተቋማት ተዘግተዋል፡፡

የአማራ ሚዲያ ማዕከል
መጋቢት 29 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ እና መርሳ ከተሞች መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከጧቱ 2 ስዓት ጀምሮ ተቋማት ተዘግተዋል፣ተሽከርካሪ በከተማዋ እንዳይንቀሳቀስ ተደርጓል ሲሉ ነዋሪዎች ለአዲስ ዘይቤ ተናገሩ።

በከተማዋ የባንክ አገልግሎትን ጨምሮ ሁሉም የህዝብ መገልገያ ተቋማቶች እና የተሽከርካሪ መንገድ የተዘጋ ሲሆን በአማራ ክልል ልዩ ሃይል እና ፋኖ ላይ ከመንግስት በወረደ ትዕዛዝ ትጥቅ ፍቱ ከመባሉ ጋር በተያያዘ ህዝቡ ባለመስማማቱ እንዲዘጋ እንደተደረገ ነው ነዋሪዎች የገለፁት።

በትላንትናው እለት በከተማዋ ዙሪያ በምትገኜው ጎብየ ተብላ በምትጠራ አካባቢ በሁለቱ ሃይሎች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ ተኩስ ገጥመው እንደነበር በመግለፅ ከዛሬ ጧት 2 ስዓት ጀምሮ የስራ ማቆም እና የመንገድ መዝጋት አድማ እያደረጉ እንደሆነ ተገልፇል ።አዲስ ዘይቤ እንደዘገበው
1.3K views15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 09:34:21
ጋዜጠኛ ገነት አስማማው በፀጥታ ሃይሎች ድብደባና እንግልት ደረሰባት

ትናንት መጋቢት 28/2015 ዓ/ም የየኔታ ሚዲያ ጋዜጠኛ ገነት አስማማው በመንግስት የፀጥታ ሃይሎች ተይዛ በምትወሰድበት ወቅት ድብደባና እንግልት እንዲሁም የፀጥታ ሃይሎቹ የወከሉትን ሃገራዊ የፀጥታ ተቋሙን የማይመጥን ፀያፍ ስድብ ሲሰድቧት እንደነበር ከተገኘው የድምፅ ቅጂ ለመረዳት ተችሏል።

ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ከቢሮዋ በምትወሰድበት ወቅት በፀጥታ ሃይሎች እየተወሰደች መሆኗን ለሌ ሰው እያሳወቀች ባለችበትና ጋዜጠኛ መሆኗን እየገለፀች በነበረበት ወቅት ነው ድብደባ የተፈፀመባት።

በወቅቱም በአካባቢው ሰው ከቦ እንደነበረና የፀጥታ ሃይሎቹም እንደበተኗቸው ሮሃ ቲቪ ለማወቅ ችላለች።
የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በጋዜጠኞችና በመብት ተሟጋቾች ላይ የሚፈጽሙትን አፍኖ መሰወር፣ ሕገ ወጥ እሥር፣ ድብደባ፣ ዛቻና ማስፈራሪያ ሊያቆሙ ይገባል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ተከላካይ ማዕከል አቶ ያሬድ ሃይለማሪያም ናቸው።

አቶ ያሬድ " ትላንት ከሥራ ቦታዋ ታፍና እና ድብደባ እየተፈጸመባት በታጣቂዎች የተወሰደችው የየኔታ ሚዲያ ጋዜጠኛ ገነት አስማማው የአያያዟን ሁኔታ የሚያስደምጠው የስልክ ንግግርና የድምጽ ቅጂ የአገዛዝ ሥርዓቱ ወደ መጥፎ አቅጣጫ እያመራ መሆኑን ከሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች አንዱ ነው። በቅርቡ በተመሳሳይ ሁኔታ ታፍኖ የተወሰደውና ድብደባ የተፈጸመበት ጋዜጠኛ ንጉሴ እና መምህር ታዬ ላይ የተፈጸመውም ድርጊት እንዲሁ ተጨማሪ ማሳያዎች ናቸው።" ብለዋል

ገነት አስማማውን ጨምሮ በተከታታይ ተይዘው በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችና የመብት ተሟጋቾች ይፈቱ ብለዋል አቶ ያሬድ።
ሮሀ ሚዲያ
2.5K views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 18:44:51
የእስር ዜና!

የየኔታ ቲዩብ ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ከቢሮዋ በፖሊሶች ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ተወስዳለች።
1.8K views15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 17:58:47 መከላከያ ሰራዊት በጭንቁ ቀን በደረሰለት በአማራ ልዩኃይል ላይ ጥቃት ከፈተ/ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ ታሰረ- መጋቢት 28 2015 ዓ/ም
https://www.youtube.com/live/lmxIF0P_bH4?feature=share
2.0K views14:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 17:56:47
ከባህር ዳር ወደ ጎንደር የሚወሰደው መንገድ በመከላከያ ሰራዊት እንደተዘጋ ታወቀ።

ከተዘጋው መንገድ በቅርብ ርቀት ላይ የክልሉ ልዩ ኃይል ካምፕ ይገኛል።

ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ ጎንደር የሚወስደው መንገድ ወረታ ከተማ አካባቢ በመከላከያ ሠራዊት መዘጋቱን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ከስፍራው ገለፁ።

መንገዱ በመንግስት የመከላከያ ሠራዊት ኃይል አባላት የተዘጋ ሲሆን አዲስ ዘይቤ ምክንያቱን ለማጣራት ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። መንገዱ የተዘጋው ደቡብ ጎንደር ወረታ ከተማ ላይ ሲሆን ከተዘጋው መንገድ በቅርብ ርቀት ትልቅ የአማራ ክልል የልዩ ሀይል ካምፕ ይገኛል።

ሰሞኑን የልዩ ሀይል ትጥቅ መፍታት ወሬ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በስፋት መዘዋወሩን ተከትሎ በክልሉ መዲና ባህር ዳር ጨምሮ አንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ውጥረት ተፈጥሯል።

ምንጭ አዲስ ዘይቤ
1.9K views14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 17:55:25
1.8K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 17:55:21 የአማራ ልዩ ኃይል መፍረስን በተመለከተ ከባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ!

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ በ27/07/2015 ዓ.ም. ስብሰባ በማድረግ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡ በመርህ ደረጃ የክልል ልዩ ኃይል መፍረስ እንዳለበት እና ሀገራዊ በሆነ ተክለ ሰውነት በተላበሰ የመከላከያ ሠራዊት መጠናከር እንዳለበት ፓርቲያችን የሚያምንበት ጉዳይ ቢሆንም ከወቅታዊ ሁኔታዎች አንፃር እና አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ጉዳዩ ተቀባይነት የለውም፡፡

የአማራ ልዩ ኃይል በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ዙር ጦርነቶች የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይልን ታድጎ የኦህዴድ/ብልፅግናን በትረ-ስልጣን ካጸናለት በኋላ —የአማራ ልዩ ኃይል ከወልቃይትና ከራያ ይውጣ፤ የእኛ ዓላማ ህግ ማስከበር እንጅ ‘ርስት ማስመለስ አይደለም፤” በማለት በልዩ ኃይሉ፣ በፋኖው እና በሚኒሻው ደም ሲሳለቅ መስማት የተለመደ የዜና እወጃ ነበር፡፡ በማይካድራ፣ በጭና እና በተለያዩ የአማራ እና የአፋር ህዝብ ላይ ወያኔ ያደረገው እልቂት እና ውድመት የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ የፌዴራል መንግሥት የአማራ ልዩ ኃይል እንዲፈርስ ያስተላለፈውን ውሳኔ በሁሉም ክልሎች ልዩ ኃይሎች ላይ በእኩል ደረጃና መጠን ተፈፃሚ በማይሆንበት ሁኔታ የአማራን ህዝብ ለጥቃት የሚዳርግ እኩይ ውሳኔ ስለሆነ ውሳኔውን ባልደራስ አጥብቆ ያወግዘዋል፡፡

የሀገሪቱ መከላከያ በአንድ ብሄር የበላይነት በተዋቀረበት ሁኔታ፣ የኦሮሚያ ክልልዊ መንግሥት የልዩ ኃይል ምልምላ እያካሄደ ባለበት ወቅት እና ትጥቁንም በማይፈታበት ሁኔታ የአማራን ልዩ ኃይል እንዲፈታ ማድረግ በኦሮሚያ ክልል ጭፍጨፋ ለመፈፀም የሚኖራቸውን ዓላማ የሚያሳብቅ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዳልፈታ እየታወቀ እና አመራሮች ከሰላም ስምምነቱም በኋላ በአማራ ህዝብ ላይ እየገለፁ ያሉትን የጥላቻ ቅስቀሳ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ብሎም የአማራ ርስቶችን ወልቃይት እና ራያን በኃይል ለማስመለስ እንዲረዳቸው የታሰበ የፖለቲካ ሴራ ስለሆነ ባልደራስ አጥብቆ ይቃወማል፡፡

በዚህ መሠረት፤
➢የታረዱት ዜጎቻችን ደም ሳይደርቅ ኦነጋዊ -ብልጽግና ለዳግም እልቂት የአማራን እና የአፋርን ህዝብ እያመቻቸው ስለሆነ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው ትጥቁን እንዳይፈታ ማሳሰብ እንወዳለን፡፡

➢ወልቃይት የሰው ልጅ የስቃይ፣ የጎሰኝነትና የዘር ማጽዳት ላለፉት አርባ ዓመታት አስተናግዳ ዛሬም ለሌላ እልቂት ተዘጋጅ እየተባለች እንቢልታ እየተነፋላት ስለሆነ እና ውሳኔው የአካባቢውን ማህበረሰብ ለጥቃት ቀጥተኛ ተጋላጭ የሚያደርግ አደገኛ ውሳኔ ስለሆነ የአማራ ህዝብ ከልዩ ኃይሉ ጎን እንዲቆም ማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

➢ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፣ ምሁራን፣ የንግዱ ማህበረሰብ ይህንን እኩይ ተግባር በመቃወም ከልዩ ኃይሉ ጎን እንድትቆሙ እና ገዢው ፓርቲ የወሰነውን ውሳኔ አጥብቃችሁ እንድትቃወሙ እንጠይቃለን፡፡

➢የአማራ ክልል መንግሥት ይህን የአማራ ህዝብን ለአደጋ አጋላጭ የሚያደርግ ትጥቅ የማስፈታት ውሳኔ እንዲቃወምና ተግባራዊ እንዳያደረግ በማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ባልደራስ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

ባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ፓረቲ
ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
መጋቢት 28/2015 ዓ.ም
1.8K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 17:54:30
ሰበር የ እስር ዜና

የአማራ ሚዲያ ማዕከል ዋና አዘጋጅ የሆነው አባይ ዘውዱ ዛሬ ጠዋት በፖሊሶች ታፍኖ ወደ ሜክሲኮ ፌደራል ፖሊስ ተወስዷል።
1.7K views14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ