2023-04-07 18:28:19
ከአማራ ፋኖ አንድነት ምክር-ቤት የተሰጠ መግለጫ
የተከበረኸው የአማራ ህዝብ
ከመቸውም ጊዜ በላይ በምንጊዜም ጠላቶችህ የጥፋት ወጥመድ ተጠምዶብሀል። እንደሚታወቀው የአማራ ፋኖ ከጥንት ጀምሮ ሀገር እየታደገ የመጣ የሀገር አድባር የኢትዮጵያ መከታ ሆኖ ዘመናትን አሻግሯታል።
ወራሪው የትግራይ ሀይል የእናቱን ጡት በነከሰበት ጊዜም ክተት ለነፃነት፣ መክት ለእናት ሀገር ብሎ ተዋግቷል፣ ሙቷል ቆስሏል። የባለስልጣኑን ወንበርም አድኗል። ዘርፈው ሻንጣ ጠቅልለው ሊወጡ የነበሩት ካድሬወችም ተመልሰው ከወንበራቸው ተቀምጠዋል። ለዚህ ውለታው ተረኞቹ በየቀኑ ሲያወግዙን እና ሲያጥላሉን ቆይተዋል። በዚህ ያልበቃቸው ጠላቶቻችን ፈረሳቸውን ብአዴንን ተጠቅመው የአማራን ፋኖ እና የአማራ ልዩ ሀይል ትጥቅ አስፈትተው አማራን ለማጥፋት ጋላቢወቹ ህውሀት እና ኦነግ በብልፅግና ሽፋን ሊያጠፉን በፈረሳቸው በብአዴን በኩል በራችን ድረስ መጥተዋል። በመሆኑም ሁሉም አማራ ከአማራ ፋኖ እና ከአማራ ልዩ ሀይል ጎን በመሰለፍ አማራን ከማንኛውም ጥቃት ትከላከል ዘንድ የአማራ ፋኖ አንድነት ምክርቤት ጥሪውን ያስተላልፋል!
የአማራ ልዩ ሀይልን እና ፋኖን ትጥቅ ለማስፈታት እና ለመበተን አቅዶ ወደ ስራ የገባው ተስፋፊ እና ጨፍጫፊው የኦረሙማ ሀይል እየተጠቀመባቸው ያሉት ብአዴን እና የብአዴን እርዝራዦች፣ የስርዐቱን የእጅ ጥራጊ መብላት የለመደባቸው ከሀዲ የፖለቲካ እና የፀጥታ አመራሮች፣ የዋንጫ ልቅላቂ መጠጣት የለመዱ አንዳንድ አድሀሪ የአማራ ተወካይ ተብየወች፣ አማራነታቸውን ክደው የአብይን አጥፊ ወንጌል ተቀላቅለዋል። በአማራ ህዝብም የዘር ፍጅት አብረው አውጀዋል። በአንፃሩ ሰው በላው የአብይ መንግስት የአማራን ህዝብ እያጠፋ መሆኑ ገብቷቸው በድብቅ እና በግልፅ ከኛ ዘንድ የሆኑ የፖለቲካ እና የፀጥታ አመራሮች ምስጋና ይገባቸዋል። እስከ መጨረሻው የድል ጮራ ድረስ በፅናት እንዲታገሉም እንጠይቃለ።
ከአማራ ፋኖ አንድነት ምክርቤት ጎን ለተሰልፋችሁ የአማራ ልዩ ሀይሎች በሙሉ የናንተ ዕውነት፣ ፅናት፣ አይበገሬነት፣ ከግብረ-በላወቹ በላይ የአንበሳ ግርማሞገስ አለው፣ ስለ አማራነት ታምናችሁ ከስግብግቦቹ እና አምባገነኖቹ ጋር አንተባበርም አማራ ሆነን ነው የተወለድነው አማራ ሁነን ታግለን እንሞታለን በማለታችሁ ኮርተንባችኋል! የጋራ ትግላችንም ለድል ይበቃል፣ የንፁሀንን እንባ እንጠርጋለን፣ የአማራን እርስቶችም እናስከብራለን።
...
የተከበራችሁ የአማራ ልዩ ሀይል እናንተ ልክ እንደ አማራ ፋኖ ተክዳችኋል። የሞታችሁለት፣ የቆሰላችሁበት፣ የደማችሁበት ትግል፣ በመጨረሻ አፈሙዝ አዙሮባችኋል። ምክንያቱ ደግሞ አማራ በመሆናችሁ አማራን ለማጥፋት አቅዶ እየሰራ ያለው የብልፅግ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ጠለምት እና ሁመራን፣ የራያ አለማጣ እና ወፍላን እርስቶቻችንን አሳልፎ ለመስጠት እንቅፋት ይሆኑኛል ያለውን የአማራ ፋኖን እና የአማራ ልዩ ሀይልን ትጥቅ በማስፈታት በአማራ ህዝብ ላይ ክህደት እየፈፀመ ይገኛል። ይሄን እኩይ ሴራ ተረድታችሁ ለአማራ ህዝብ ለመታገል እና ህዝባችንን ለማታገል ቆርጣችሁ ከፋኖ ጎን የተሰለፋችሁ የአማራ ልዩ ሀይል አባላት እና አዛዦች ለአማራ ህዝብ እስከመጨረሻ የደም ጠብተችሁ በታማኝነት እንድትፋለሙ በአማራ ህዝብ ስም እንጠይቃለን።
የብአዴን አሽከላ ለመሆን የወሰናችሁ የአማራ ልዩ ሀይል የክፍለ ጦር አዛዦች እና ከዛ በላይ ያላችሁ አመራሮች ለማዕረግ ጭማሪ፣ ለስልጣን፣ ለተሻለ ጡረታ፣ ለቤትመስሪያ ቦታ እና መኪና ብላችሁ አማራነታቹህን እና ክብራችሁን ለንዋይ ፍቅር አሳልፋችሁ በመስጠት፣ በኩርነታችሁን የሸጣችሁ ይሁዳወች እናንተን ለዘለዓለም የአማራ ህዝብ ይቅር አይላችሁም። ልጆቻችሁን እና ቤተሰቦቻችሁንም ጭምር አንገት አስደፍታችኋል።
አማራን የካዳችሁ ግብረበላ ጥቁር አማራወች፣ ከመንግስት ጎን የተሰለፋችሁ አክቲቪስቶች፣ ፖለቲከኞች እና ባለስልጣናትን ዛሬ እንኳን ከህዝባችን ትካሻ በመውረድ ይሄንን አስከፊ ስርዐት ለመታገል እና ለማስወገድ ከህዝባችን ጎን እንድትሰለፉ ጥሪ እናቀርባለን።
የአማራ አድማ ብተና፣ የአማራ ፓሊስ እና የአማራ ሚሊሻ ስለ አማራነት ከሚዋደቀው አማራ ፋኖ እና ከአማራ ልዩ ሀይል ጎን እንድትሰለፍ እንጠይቃለን። ኦነግ ሸኔ እና ትህነግ በጋራ ሊያጠፉህ ወስነው አንተ ግን ከአማራው ወንድምህ ጋር አፈሙዝ እንድትዟዟር እያሴሩ ነው እምቢ አማራነኝ ብላችሁ ከአማራ ወንድማችሁ ጋር ለማንነታችሁ ትፋለሙ ዘንድ በአማራነታቸው በተጨፈጨፉት የንፁሀን ደም ስም እንጠይቃችሁአለን።
የተከበራችሁ ኢትዮጵያዊያን የአማራ ህዝብ ትግል ለበላይነት የሚደረግ ሳይሆን የኢትዮጵያን አንድነት ግቡ ያደረገ ለሰላም፣ለፍትህ ፣ለእኩልነት እና ለዲሞክራሲ የሚደረግ እንዲሁም ፣ከሁሉም በላይ በህይወት መኖር የተከለከለውን የአማራ ህልውና አደጋ ለመቀልበስ የተገደድን በመሆናችን ከጎናችን በመሰለፍ የበኩላችሁን ትወጡ ዘንድ የአማራ ፋኖ አንድነት ምክርቤት በጥብቅ ያሳስባል።
የመከላከያ ሠራዊት አባላትም ከአማራ ህዝብ እና ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጎን እንጂ ከአምባገነኖች ጎን እንደማትሰለፉ እንተማመንአለን። እናንተ የኢትዮጵያ እንጅ የተረኞች የወጭ እና ወራጅ ካድሬ መጠቀሚያ አይደላችሁም። ከናንተ ጋር አብሮ ከሞተው እና በአንድ ጉድጓድ ከተቀበረው የአማራ ፋኖ እና ልዩ ሀይል ጋር በመዋጋት ታሪካዊ ስህተት እንዳትሰሩ አደራ እንላለን።
ጀግናው የአማራ ህዝብ አባቶችህ እና እናቶችህ በከፈሉት መስዋዕትነት የቆመችውን ጥንታዊት አገርህ ኢትዮጵያ ከአንተ እንደተወሰደችብህ በመረዳት ለትግሉ በፅናት እንድትቆም አደራ እያልን በደም እና በአጥንታችን የአማራን ህዝብ የህልውና አደጋ እንቀለብሳለን። የሁላችንም የጋራ ሀገር ኢትዮጵያንም ከጠባብ እና ተስፋፊወች እንታደጋትአለን።
ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ ግን የአማራ ህዝብ ጠላቶች ሚሳኤል እና ድሮን ቀርቶ ኑክሌር ቢታጠቁ ህዝባችን በጋራ በማታገል ጠላትን ድባቅ እንመታለን። ጎልያድ በዳዊት ወንጭፍ መውደቁን ልብ እንላለን። ንጉስም በሰራዊቱ ብዛት እንደማይድን እናውቃለን። በወለጋ፣ በጉምዝ በወልቃይት በራያ በግፈኞች የፈሰሰውን ደም የምናደርቀው እምቢ ማለት ስንጀምር ነው። እምቢ በል አማራ!!
እምቢ ለርስቴ እምቢ ለማንነቴ
ህልውናችን በክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ አንድነት ምክርቤት
መጋቢት 29/2015 ዓ.ም
1.4K views15:28