Get Mystery Box with random crypto!

አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center

የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_center — አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center
የሰርጥ አድራሻ: @amhara_media_center
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.55K

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-12 02:01:58
አቶ ስንታየሁ ቸኮል በዛሬው ዕለት በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር ተፈቷል።
1.6K views23:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 18:15:24
ደብረብርሃን
3.2K views15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 17:52:53
በኮምቦልቻ ዛሬ ቢያንስ 2 ሰው ሲገደል ስምንት ቆስለዋል
3.2K views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 17:30:22
የ ኦሮሙማ ሰራዊት በኮምቦልቻ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የነበሩ 2 አማራዎችን ገደለ። ከ12 የሚበልጡ ተጎድተዋል

የአማራ ሚዲያ ማእከል
ሚያዝያ 3 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

አምስተኛ ቀኑን በያዘው ህዝባዊ እንቢተኝነት ዛሬ ረፋድ ላይ በኮምቦልቻ ከተማ “የልዩ ኃይል አባላት የተያዙ አሉ” የሚል መረጃ በመሰራጨቱ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ግጭት ውስጥ መገባቱን ነዋሪዎች ለአዲስ ዘይቤ መግለጻቸዉን በመጠቆም ዘግባለች።

በኮምቦልቻ አንድ ጤና ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ የአዲስ ዘይቤ ምንጮች እንደገለፁት አንድ ሰው እዛው ተኩስ የተከፈበት ስፍራ ላይ ህይወቱ ማለፉን እና ሌላ አንድ ሰው በአምቡላንስ ወደጤና ጣቢያ እየተወሰደ ህይወቱ አልፏል ብለዋል።

በተጨማሪም 12 የሚሆኑ ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ኮምቦልቻ ጠቅላላ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የሚገልፁት ነዋሪዎች፣ አምቡላንስ በተደጋጋሚ ሲመላለስ እንደነበረና የተጎጂዎች ቁጥር ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ለአዲስ ዘይቤ ተናግረዋል።

በአሁኑ ሰዓት በኮምቦልቻ ከተማ ከመደበኛ ጊዜው የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ መኖሩን ነዋሪዎች ነግረውናል።ህዝባዊ እንቢተኝነቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
3.2K views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 17:29:48
የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ
ለሁሉም የአማራ ልጆችና ሀገር ወዳድ ለሆናችሁ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፥

በሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ፭ ዓመታት ጀምሮ ያለማቋረጥ በአማራ ሕዝብ የመኖር ተፈጥሮዊ መብት ላይ የብልጽግ/ኦነግ መንግሥት በወለጋና በአርሲ የዘር ጭፈጨፋ ተካሂዶባታል አሁን ደግሞ ትጥቅ ማስፈታት በሚል ሰበብ ጦርነት ታውጆበት ሕጻናትን በእድሜ የገፉ አረጋውያን ወንዶችና ሴቶችን በመጨፍጨፍ የመኖሪያ ቤቶችን ሳይቀር በከባድ መሣሪያ በማውደም ላይ ይገኛል።

ስለዚህ ይህንን በአማራ ሕዝብ ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማጋለጥ እንዲሁም የአሜሪካም ሆነ የአውሮፓ መንግሥት እጃቸውን እንዲያነሱልን ለማውገዝ ሰኞ Montag April 17,2023 (ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፭) ዓ ም በፍራንክፈርት ከተማ
አሜሪካ ኮንስላት ፊት ለፊት ከቀኑ ፲፩ (11:00) ሰዓት ጀምሮ የተቃውሞ ሰልፍ ስለሚካሄድ በቦታው ትገኙ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን

ወደ ተቃውሞ ሰልፉ በባቡር ለመምጥት ለምንፈልግ ከ ፍራንክፉርት ባኖፍ (Frankfurt HBF) U-Bahn (U5) * Richtung *Preungesheim የሚለውን በመያዝ ከ ፩፭ (15ደቂቃ) በኃላ Gießner Straße የሚለው ፌርማታ ስንደርስ በመውረድ ትንሽ በእግር ተራምደን መዳረሻውን ማለትም የአሜሪካ ኢምባሲን እናገኘዋለን።

ከ ባኖፍ በተጨማሪ ከ አKonstablerwache U5 ን መያዝም ይቻላል።

በመኪና በቀጥታ ወደ ሰልፉ ቦታ መምጣት ለምትፈልጉ አድራሻው ይኸው

Americanisches Generalkonsulat

Gießener Str. 30, 60435 Frankfurt am Main

የአማራ ማኅበር በጀርመን
3.0K views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 16:05:35
3.0K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 16:05:19 ሰከን ብሎ በማሰብ እንጂ ሀገርን ወደ ቀውስ በመግፋት ስልጣንን ማጽናት አይቻልም!

የአማራ ሚዲያ ማእከል
ሚያዚያ 3 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ፣ ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የተሰጠ መግለጫ

ኢትዮጵያ ሀገራችን በብዙ መከራ ውስጥ እያለፈች ሲሆን በተለይም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ኢትዮጵያውያን በሁለት ጎራ ተሰልፈን ባደረግነው ውጊያ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ውድ ሕይወታቸውን አጥተዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን የአካል ጉዳተኞች ሆነዋል፤ ብዙዎች የሥነ ልቡና ስብራት ደርሶባቸዋል፤ ልጆች ያለአሳዳጊ ወላጅ፤ ሚስቶች ያለባል ባሎችም ያለሚስት፣ ወላጆች ያለጧሪ ቀባሪ ቀርተዋል፤ መሰረተ ልማቶች ወድመዋል፤ ሀገራችን በዲፕሎማሲው መስክ ተጽዕኖ እንዲያርፍባት ገጽታዋም በአሉታዊ መልኩ እንዲነሳ አድርጓል፤ ለከፋ የፖለቲካ እና ማኅበረ ኢኮኖሚ ቀውስ ዳርጓታል።

ይህ ኹሉ ከሆነ በኋላ ከነችግሩም ቢያንስ በድርድር ችግሩን ለመፍታት በተደረገው ጥረት ለጊዜውም ቢሆን ጦርነቱ ጋብ እንዲል መደረጉ ጥሩ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ከክልሎች ልዩ ኃይል "ማፍረስ" ጋር በተገናኘ በተለይም በአማራ ክልል ውጥረት ነግሷል፡፡ እንደ ሀገር የኢትዮጵያ ሕዝብ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ለርሃብ እና ለከፋ የሕይወት ዉጣ ውረድ የተዳረገ ሲሆን በተለይም የጎሳ ፓለቲካ በወለደው ጽንፈኝነት በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ሕዝባችን ሰላም አጥቷል፤ ነፃነቱን ተነፍጓል፤ በተለይም የአማራ ሕዝብ ርዕዮተ ዓለማዊ ማዕቀፍ ባለዉ ሁኔታ የሐሰት ትርክት ተቀነባብሮበት በጠላትነት ተፈርጆ ላለፉት 32 ዓመታት እንደ ዱር እንስሳ ተገድሏል፣ ተሰድዷል፣ ተፈናቅሏል፣ ንብረቱን ተዘርፏል፣ መኖሪያ ቤቶቹ ፈርሰውበታል ዛሬም ይኸው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

እናት ፓርቲ፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ ይህን እንደ ሀገር የገባንበትን አደገኛ ሁኔታ በማስወገድ ኹሉም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የሀገራችን ክፍል ያለአድሎ በእኩልነት መኖር እንዲችልና የተረጋጋች ለሁሉም ዜጋ ምቹ ኢትዮጵያን ለመገንባት ከፋፋይ ከሆነው የሕግ መንግስቱን አንቀጾች ማሻሻል ጀምሮ የችግሮቻችን አልፋና ኦሜጋ የሆነውና በጎሳ ላይ የተመሠረተ የፌደራል ሥርዓት ማስተካከል፣ ገለልተኛ የሕዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ማደራጀት ብሎም ከሕግ ውጪ የሆኑ አደረጃጀቶችን ወደ ሕጋዊ መስመር እንዲገቡ ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለን እናምናለን፡፡

የክልሎች የልዩ ኃይል አደረጃጀት ኢሕገመንግስታዊና የሀገር የጸጥታ ስጋት ስለሆነ የሀገራችንን ዳር ድንበራችን የሚያስከብር አንድ ጠንካራ መከላከያ ሰራዊት፣ ውስጣዊ የጸጥታ ችግሮች እንዳይፈጠሩ የሚያደርግ የፌደራል ፖሊስ እና ክልሎች ደግሞ መደበኛ ፓሊስ ብቻ እንዲኖራቸው ሊደረግ እንደሚገባ በማመን ይህን አቋም ግልጽ በሆነ ሁኔታ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ጭምር ስናንጸባርቅ እንደ ነበር ይታወሳል፡፡

አገር በጎሳ ተከፋፍላ ከፍተኛ ደም አፋሳሽ ጦርነት ባስተናገደችበት ሁኔታ ክልሎች ልዩ ኃይልን እንደ ህልውና ማረጋገጫ እየወሰዱ እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡ ለዋቢነት ህወሃት የአማራን ክልል በወረረበት ወቅት የክልሉ ልዩ ኃይል የተጫወተው ሚና፤ ሕወሃት በተመሳሳይ መልኩ የአፋርን ክልል በድጋሚ በመውረር ሰፊ አካባቢን በተቆጣጠረበት ወቅት የክልሉ ልዩ ኃይል ያለ መከላከያ ሠራዊት ድጋፍ ብቻውን ክልሉን ከህወሃት ነፃ ለማውጣት ያደረገውን ተጋድሎ፤ በቅርቡ አልሸባብ በሶማሌ ክልል በኩል አገራችን ላይ በሰነዘረው ጥቃት የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል የሶማሌን ክልል ሳይሆን የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ለማስከበር ያደረገው ተጋድሎና የፈጸመው ጀብድ በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የትብብሩ አባል ፓርቲዎች የክልል ልዩ ኃይል አላስፈላጊነት ላይ ወጥ የሆነ አቋም ያላቸው ሲሆን መፍረሱና በልዩ መልኩ ማደራጀት ላይ ከሁሉ አስቀድሞ ለእንደዚህ ዓይነት አደረጃጀት የዳረገውና የጎሳ ፌዴራል ሥርዓትን የደነገገው ሕገ መንግሥት ተለውጦ አገር ከጎሳ አደረጃጀት ስትላቀቅ መሆኑን ያምናሉ፡፡ ይህን ማድረግ ደግሞ የአገራዊ ምክክርና የአገራዊ መግባባት ውጤት ሲሆን አገር ያዝ ለቀቅ እያደረገች የምትከተለው አገራዊ መግባባት ሊከናወን ከቻለ ይህን ተከትሎ በሚለወጠው የጎሳ አደረጃጀትና የህገ መንግሥት ማሻሻያ የክልል ልዩ ኃይሎች ተፈጥሯዊ በሆነ መልኩ እንደሚከስሙ ወይም እንዲከስሙ ማድረግ እንደሚገባ እምነታችን ነው፡፡

አካሄዱ ከላይ እንደገለጽነው መሆን ሲገባ ከሰሞኑ የአማራ ክልልን ልዩ ኃይል ግልጽነት በጎደለው ሁኔታ "በአንድ በኩል ልዩ ኃይል ለማፍረስ በሚመስል መልኩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ መልሶ ለማደራጀት" ነው በሚል የተምታታ አገላለጽና ይህንኑ ተከትሎ ልዩ ኃይሉ በእጁ ያሉትን መሣሪያዎች ወደ ግምጃ ቤት እንዲያስገባ በጽሑፍ ትዕዛዝ ከመተላለፉ ጋር ተያይዞ በክልሉ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች በከባድ መሣሪያ ጭምር የታገዘ ጥቃት በፀጥታ ኃይሎች እየደረሰ እንደሆነ ለመገንዘብ ችለናል፡፡ የክልሉ ሕዝብ “ከፍተኛ የጸጥታ ስጋት እንዳለብን እየታወቀ እስከአሁን እልባት ያላገኙ የማንነት ጥያቄዎች መልስ ባላገኙበት፣ ሕወሀት ለጦርነት ዝግጅት እያደረገ ባለበት ሁኔታ፣ የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ባልሆነበት፣ ከዚህ በኋላ ሕዝባችንን ለመከራ የሚዳርግ ቀውስ እንደማይፈጠር መተማመኛ ባልተደረሰበት፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ባልተፈጠረበት ሁኔታ እና በተለየ መልኩ ከሁሉ ክልሎች በፊት የአማራ ክልልን ልዩ ኃይል ትጥቅ ለማስፈታት የፌደራል መንግሥቱ የጀመረው እንቅስቃሴ ስጋት ፈጥሮብናል“ በሚል ድርጊቱን አየተቃወመ ይገኛል፡፡

አካሄዱ በዚህ መልክ ከቀጠለ አገራችንን ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ የሚያስገባ መሆኑ ታውቆ ሕዝባዊ ተቃውሞው ከዕለት ወደዕለት እየተባባሰ ከፍተኛ ውጥረት እየፈጠረ ባለበት በአሁኑ ወቅት የፌዴራል መንግሥት የጀመረውን አካሄድ ቆም ብሎ በአስቸኳይ በመመርመር አገርን ወደ ቀውስ ከመግፋት ተቆጥቦ ሰከን ብሎ ችግሮችን በማጤን የተጀመረው የጥፋት ጉዞ እንዲገታ የትብብሩ አባል ፓርቲዎች አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ፡-
የፌደራል መንግሥቱ ከሚያደርገው ግብታዊ እና ስሜታዊ እንቅስቃሴ በመቆጠብ ነገሮችን በሰከነ ሁኔታ በመመልከት ቀደም ሲል የጠቀስነው አገራዊ ምክክር ተደርጎ ህገ መንግሥታዊ ማሻሻያ እስኪደረግ አገርን ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ እየከተተ ያለውን አካሄድ እንዲያቆም አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡ አያይዘን መንግሥት ከሴራ እና ሕዝብን ከሚያስቆጡ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ አገር በዚህ መልኩ ቀጥላ ሊከሰት ለሚችለው ሁለንተናዊ ቀውስ የፌደራል መንግሥቱ ተጠያቂ እንደሚሆን እናሳስባለን።

ሕዝባችን እንደወትሮው ሁሉ አንድነቱን አጠናክሮ ነገሮችን በሰከነ ሁኔታ እንዲመለከት አገርን የበለጠ ጉዳት ላይ ከሚጥሉና ሕዝባችንን እርስ በርስ ከሚያጋጩ አካሄዶች፤ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የግልም ሆነ የአገር ሀብት ላይ ጉዳት ከማድረስ በእጅጉ እንዲቆጠብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ

እናት ፓርቲ፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ
ሚያዝያ ፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
2.9K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 16:05:19
ህዝባዊ እንቢተኝነት በባህር ዳር
2.7K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 16:03:39
መስከረም አበራ “ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ፖሊስ ወንጅሏል።

ከትላንት በስቲያ እሁድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለችው የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዋ መስከረም አበራ፤ “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ በፍርድ ቤት 13 የምርመራ ቀናት ተፈቀደባት። መስከረምን ፍርድ ቤት ያቀረባት የፌደራል ፖሊስ፤ “ተጠርጣሪዋ ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

ፖሊስ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 3፤ 2015፤ በመስከረም ላይ ውንጀላውን ያቀረበው፤ ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። በችሎቱ መስከረምን ወክለው የቀረቡት ጠበቃዋ አቶ ሄኖክ አክሊሉ በበኩላቸው ፍርድ ቤቱ የደንበኛቸውን የዋስትና መብት እንዲጠብቅ ጠይቀዋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
2.9K views13:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 23:18:06
በምስራቅ ጎጃም ዞን የአነደድ ወረዳ የአምበር ከተማ 'የሰዋች ለሰዋች የመሰናዶና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት' የፊዚክስ መምህር የሆነው መምህር በላይ ነጮ በአነደድ ወረዳ ፖሊስና ሚኒሻ ተደብድቦ ራሱን ስቶ ሆስፒታል ገብቷል።

የአማራ ሚዲያ ማዕከል
ሚያዚያ 2 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የኢ-ሰብአዊ ድብደባው መንስኤ ብልፅግናን የሚቃወም መፈክር ይዘህ ወጣቱን አስተባብረህ አደባባይ ወጥተሀል የሚል ነው::

ብልፅግናን ለምን ትቃወማለህ በሚል ኢ- ሰብአዊ በሆነ የተደበደበው መምህር በላይ የቲቢ ታማሚ ነው። መምህር በላይ አሁን ላይ መራመድ አይችልም። ሁለቱም እግሮቹ ከጥቅም ውጭ ሆነዋል።
ይህን ግፍ የፈፀሙት:-

1.አስራደ ታምሩ:- የአነደድ ወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ሀላፊ ሲሆን የኦሮሞና የአማራ ተወላጅ ነው። አማራውን አምርሮ የሚጠላ ሰው ነው።

2.ይሄነው ሙሉአዳም:- የአነደድ ወረዳ የሚሊሻ ፅ/ቤት ሀላፊ

3.ማማሩ ገድፍ:- የአነደድ ወረዳ የገቢዋች ሀላፊ።
እነዚህ ሰዋች ህግ ኖሮ በህግ እንዲጠየቁ ሳይሆን ማህበረሰቡ በተለይም ወጣቱ እንዲያውቃቸው ነው።

ምንጭ ምንአልባት ይታየው
3.9K views20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ