#ጋዜጠኛ ሰናይት አያሌው ፍ/ቤት ቀርባ የ5 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባት!
የአማራ ሚዲያ ማእከል
ሚያዝያ 11 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በቀን 05/08/2015 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤቷ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ማንነታቸው ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ታፍና የተወሰደችው የአሻራ ሚዲያ ጋዜጠኛ የሆነችው ሰናይት አያሌው ከ6 ቀናት በኋላ ፍ/ቤት የቀረበች ሲሆን ፖሊስ ተጨማሪ 7 ቀናት እንዲሰጠው ቢጠይቅም ፍ/ቤቱ የ5 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ በመስጠት ለሚያዚያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ፍትህ ለጋዜጠኛ ሰናይት አያሌው!
ምንጭ አሻራ ሚዲያ