Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-11-18 19:33:47 #ኅዳር_11_ለእግዚአብሔር_በሥጋ_አያቱ_ለእመቤታችን_እናቷ_የሆነችው_የብጽዕት_ሐና_ዕረፍቷ_ነው::

"ሐና" ማለት በእብራይስጥኛው "የእግዚአብሔር ስጦታ" እንደ ማለት ነው:: "ሐና: ዮሐና: ሐናንያ" የሚሉ የዕብራይስጥ ስሞች ትርጉማቸው ተወራራሽ ነው::

ቅድስት ሐና ትውልዷ: ነገዷ ከላይ ከቅዱስ አብርሃም: ከታች ደግሞ ከነገደ ካህናት ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- *አብርሃም ይስሐቅን: ይስሐቅ ያዕቆብን: ያዕቆብ ደግሞ ሌዊንና 11 ወንድሞቹን ይወልዳል:: *ሌዊ ቀዓትን: ቀዓት እንበረምን: እንበረም አሮን ካህኑን ይወልዳሉ:: *ቅዱስ አሮን አልዓዛርን: አልዓዛር ፊንሐስን እያለ ትውልዱ እስከ ቴክታና ጰጥሪቃ ይወርዳል:: ቴክታና ጰጥሪቃም ልጅ በማጣት ኖረው: የእንቦሳዎችን: የጨረቃንና: የፀሐይን ምስጢር በሕልም ተመልክተው ሄኤሜንን ይወልዳሉ::

*ሄኤሜን ዴርዴን: ዴርዴ ቶናሕን: ቶናሕ ሲካርን: ሲካርም ሔርሜላን ይወልዳሉ:: *ሔርሜላም ከክርስቶስ ልደት 90 ዓመታት በፊት ማጣት ("ጣ" ጠብቆ ይነበብ) የሚባል ደግ ሰው ከካህናት ወገን አግብታ በስርዓተ ኦሪት ትኖር ነበር:: እግዚአብሔር ለዚህች ደግ ሴት የተባረኩ 3 ሴቶች ልጆችን ሰጣት:: የመጀመሪያዋን "ማርያም" አለቻት:: ይህቺውም የአረጋዊው ዮሴፍ ሚስትና የቅድስት ሰሎሜ ቡርክት እናት ናት:: ሁለተኛዋን "ሶፍያ" አለቻት:: እርሷም ቅድስት ኤልሳቤጥን (የመጥምቁን እናት) ወልዳለች:: በመጨረሻ የወለዷትን ግን "ሐና" አሏት:: ይህቺውም የፈጣሪ የሥጋ አያቱ: የድንግል ማርያምም እናቷ ትሆን ዘንድ የተመረጠችውና ስም አጠራሯ የከበረው እናት ናት::

ኢያቄምና ሃና ለእግዚአብሔር የታዘዘ በተቀደሰ ጋብቻ ውስጥ በብዙ ዘመናት አብረው ቢኖሩም በነዚያ ጊዜያት ወስጥ አንድ ልጅ እንኳ ስላልነበራቸው እጅግ ያዝኑ ነበር፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ እየሄዱ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው ይለምኑት ነበር፡፡

ከእለታት አንድ ቀን ኢያቄምና ሃና እርግቦች ጫጩቶቻቸውን ሲያጫውቱ ተመልክተው “ለነዚኽ ወፎች እንኳ ልጆችን የሰጠህ አምላክ ለእኛስ መች ይሆን ልጅ የምትሰጠን?” ብለው እጅግ አምርረው አለቀሱ፡፡ ከሐዘናቸውም ጽናት የተነሳ እንቅልፍ ያዛቸውና ተኙ፡፡ በተኙ ግዜም ለሁለቱም እግዚአብሔር መልካም ፈቃዱን በህልም ገለጠላቸው፡፡ ኢያቄም በህልሙ ሃና በእቅፍ ውስጥ ከፍሬዎች ሁሉ የምትበልጥ መልካም ጣፋጭ ፍሬ ይዛ ተመለከተ፡፡ ሃና የኢያቄም በትር ለምልማ፣ አብባና አፍርታ ተመለከተች፡፡ ከእንቅልፋቸውም ነቅተው ስለ ህልማቸው ተነጋገሩ፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲሆንላቸው በጸሎት ጠየቁ፡፡ እግዚአብሔር ወንድም ሆነ ሴት ልጅ ቢሰጣቸው አድጎ እኛን ያገልግለን ይታዘዘን ሳይሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ እንዲሆን እንደሚሰጡት ቃል ገቡ፡፡

ከዚህ በኋላ ነሐሴ 7 ቀን ሃና ፀነሰች፡፡ ሃና በእርጅናዋ ጊዜ መፅነሷ የተመለከቱ ዘመዶቿና ያገሯ ሰዎች ተገርመው እየመጡ ይጠይቋት ነበር፡፡ ከነዚህም ሰዎች መካከል አንዱ ዐይነ ስውር የነበረችው የአርሳባን ልጅ ናት፡፡ የአርሳባን ልጅ ወደ ሃና መጥታ እውነትም ሃና መጽነሷን ለማረጋገጥ ሆዷን ዳሰሰቻት፡፡ በአድናቆትም ሳታስበው ዐይኗን ስትነካ ዐይኗ በራላት፡፡ በሌላ ግዜም የአጎቷ ልጅ በህመም ምክንያት ይሞትና ሃና ትወደው ስለነበር ልታለቅስ ወደአረፈበት ቤት ትሔዳለች፡፡ እንደደረሰችም አስክሬኑ በተቀመጠበት መካከል አልጋ ዙሪያ ስታለቅስ ሳለ ድንገት ጥላዋ ቢያርፍበት የሞተው ሰው ተነስቶ ሃና የአምላክ እናት የምትሆን እመቤታችንን እንደምልድና በዚህም ሃና እጅግ የከበረችና ምስጋና የሚገባት መሆኗን መሰከረ፡፡ ሃና በፀነሰች ግዜ የተደረጉ ብዙ ተአምራትን አይሁድ አይተው ገና በፅንስ ግዜ ይህን ያክል ተአምራት ያደረገ ሲወለድማ ብዙ ነገር ያደርጋል ብለው በምቀኝነት ተነሳስተው ኢያቅምና ሃናን ሊገድሏቸው ተነሱ፡፡ እግዚአብሔር ግን መልአኩን ልኮ ኢያቄምና ሃና ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሸሹ አደረጋቸው፡፡ በዚያም ሆነው ግንቦት 1 ቀን ከንጋት ኮከብ ይልቅ የምታበራ እጅግ ያማረች የተቀደሰች የምትሆን ልጅን ወለዱ፡፡

ስሟን "ማርያም-የአምላክ ስጦታ" ብለው ሰይመው ለ3 ዓመታት አሳድገዋታል:: የሚገርመው በ3ቱ ዓመታት ውስጥ ቅድስት ሐና ድንግል ማርያምን ከክንዷ አውርዳት አታውቅም ነበር:: አንድ ጊዜም መላእክት ወስደውባት ፍጹም አልቅሳለች:: ሁዋላ ግን መልሰውላታል:: ሌላኛው የሚደንቀው እግዚአብሔር የዓለም ውዱን ስጦታ እመ ብርሃንን ሰጣቸው:: እነርሱም ይሕችን ውድ ስጦታ ሳይሰስቱ ለፈጣሪ መለሱለት:: ቅድስት ሐና ድንግል ወደ ቤተ መቅደስ ከገባች በሁዋላ የእናትነት ፍቅሯ እያገበራት ለ5 ዓመታት እየተመላለሰች ትጐበኛት: ትስማት ነበር:: እመቤታችን 8 ዓመት በሞላት ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ጥሪ ወደ ቅድስት ሐና ደረሰ:: ከክርስቶስ ልደት 8 ዓመታት አስቀድማ ብጽዕት እናት ሐና ኅዳር 11 ቀን ዐረፈች:: ትንሽ ቆይቶም ባለቤቷ ቅዱስ ኢያቄም ተከተላት እኛም ልጆቿ "ብጽዕት ሐና ክብር ይገባሻል!" እያልን እናመስግናት::

አምላከ ብጽዕት ሐና በምልጃዋ ከዘለዓለም እሳት ያድነን!!! አሜን
23 viewsbisrat, 16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 10:19:01 #እጅግ_ድንቅ_የሆነ_አስተማሪ_የንስሐ_ሕይወት_ታሪክ:-

ቅዱስ ኤፍሬም ዘሶሪያ እና ቅዱስ ባስልዮስ ዘአንጾኪያ በተነሱበት ዘመን የምትኖር ልቧ በኀጢአት የሰከረ ለኀጢአት ተገዚ የሆነች ኀጢአቷን የምትጽፍ  አንዲት ሴት ነበረች::

ይቸ ሴት የተለያየ ኀጢአት የምሰራ ነበረች
ትዘሙታለች
ትዋሻለች
ታማለች
ትሰርቃለች
ትገድላለች
በአል ትሽራለች
ትሰክራለች
በትእቢት የተሞላች ሴት ናት ልብሷ ኀጢአት ነበር:: ነገር ግን የምሰረውን ኀጢአቷን ሁሉ አየጻፈች ታስቀምጥ ነበር ከዕለታት አንድ ቀን የጻፈችው ኀጢአትቷን ብታየው ስንክሳር አክሎ ተመለከተችው::

ስንክሳር ማለት በ365 ቀኖች የሚውሉ የቅዱሳን ታሪክ ሰብስቦ የያዘ ትልቅ መጽሐፍ ነው የዚች ሴትም ኀጢአትም ይህን አክሎ ነበር:: እንዳየችው ደነገጠችና ኀጢአቷን ተሸክማ አባት ወደ አለበት ወደአንጾኪያ ሄደች::በዚያም አባ ባስልዮስን አገኘችው አባቴ በዚህ ያለው ኀጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው አባ ባስልዮስም ይፋቅልሽ አላት:: ገልጣ ብታየው ሁሉ ተፍቆ አንዲት ኀጢአቷ ቀርታ አየቻት በጣም ከባድ ኀጢአት ነበረች ሊሰሩአት የምትከብድ ሊነግሯት የምታሳፍር ነበረች አባቴ ይችሳ አለችው አባ ባስልዮስም ይችን ኀጢአትሽን ማስተስረይ የሚችል ልጄ ቅዱስ ኤፍሬም ነው ሂደሽ ለእርሱ ንገሪው አላት::

አባ ባስልዮስ ይሄን ያላት ኀጢአቷን መፋቅ አቅቶት አይደለም የራሱ ክብር ከሚገለጥ የቅዱስ ኤፍሬም ክብር እንዲገለጥ ፈልጎ ነው ደግሞም ስትመላለስ ንስሐ እንዲሆናት ፈልጎ ነው እሷም አባ ባሰስልዮስ እንዳላት ቅዱስ ኤፍሬም ወዳለበት ወደ ሶርያ ሄደች በባዶ እግሯ እንቅፋቱ እየመታት እሾሁ እየወጋት እግሯ ሲደማ ልብሷን ቀዳ እየጠመጠመች ተጉዛ ከቅዱስ ኤፍሬም ደረሰች አባቴ በዚህ ያለው ኀጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው ቅዱስ ኤፍሬም ግን ይሄ ለኔ አይቻለኝም ለአባቴ ለአባ ባስለዮስ እንጂ አላት::

ቅዱስ ኤፍሬም ኀጢአቷን መደምሰስ አቅቶት አይደለም በፈሊጥ ቀኖና ሲሰጣት ነው ስትመላለስ ኀጢአቷ እንዲቀልላት ነው ሂደሽ ለአባ ባስለዮስ ንገሪው እሱ ይደመስስልሻል አላት እሷም አግኝቸው አይሆንልኝም ብሎ ወደ አንተ ልኮኛል ሳትል እሽ ብላ መንገድ ስትጀምር እንደ ቀድሞው በህይወት አታገኝውም ሙቶ ካህናት ሊቀብሩት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይዘውት ሲሄዱ ታገኝዋለሽ ሳትጠራሪ የተጻፈው ኀጢአትሽን ከአስከሬኑ ላይ ጣይው አላት እርሷም እሽ ብላ ሄደች::

የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ብርድ እያሰቀያት ደረሰች ሙቶ ካህናት ፍትሀት እየፈቱት አየች የእግዚአብሔር አገልጋይ ባስልዮስ ሆይ የባሪያህን ኀጢአት ደምስስልኝ ብላ ከአስከሬኑ ላይ ጣለችው ከአስከሬኑ ድምጽ ወጥቶ ኀጢአትሽ ተደምስሶልሻል አላት ገልጣ ብታይ ተደምስሶላታል::

አምላኳን አመሰገነች ደስታ ዘመረች ከዚህ በሇላ ዓለምን ንቃ ገዳም ገብታ ኑራለች::

እንደ ዚች ሴት ኀጢአቱን የሚያስታውስ ማን ነው? ወደ ካህን ሂዶ ንስሐ የገባስ ስንቱ ነው? ስለኀጢአቱ በረሃ የተንከራተተ ማን ይሆን?

የዚችን ሴት መጨረሻ ያሳመረ የሁላችንም ጨረሻ ያሳምርልን ኀጢአቷን የደመሰሰ የሁላችንም ኀጢአት ይደምስስልን አምላኬ ሆይ ያለ ንስሐ አትጥራኝ!!!
124 viewsbisrat, 07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-09 18:55:16 #ሕዳር_1_ጻድቁ_ንጉሥ_ነአኩቶ_ለአብ_የተሰወረበት_ዕለት_ነው::

ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ በዛግዌ ሥርወ መንግስት ከነገሡ 11 ነገሥታት 10ኛው ንጉሥ ነው:: እርሱን በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን የወለዱት ቅዱሱ ንጉሥ ሐርቤ (ገብረ ማርያም) እና መርኬዛ ናቸው::

ዘመኑ ቅድስና በላስታ ዙሪያ የመላበት በመሆኑ ቅዱስ ሐርቤ ከመመነኑ በፊት ነበር ነአኩቶ ለአብን የወለደው:: እናቱ መርኬዛ እርሱን ልትወልድ ምጥ ተይዛ ሳለ ጀሮዋ ቅዳሴን ይሰማ ነበር:: ቅዳሴው ሲጀመር የጀመራት ምጥ ድርገት ሲወርዱ (ሥጋ ወደሙ ሲሰጥ) ተፈታላትና ልጇን ተገላገለች:: ሕጻኑን አንስታ ስትታቀፈው ዲያቆኑ ማቁረቡን ፈጽሞ "ነአኩቶ" እያለ ሲዞር ሰማችው:: እዚያው ላይም "ነአኩቶ ለአብ" (አብን እናመስግነው) ስትል ስም አወጣችለት::

ወዲያው ግን አባቱ ቅዱስ ሐርቤ መንግስቱን ለቅዱስ ላሊበላ ሰጥቶ በርሃ በመግባቱ ቅዱሱ ሕጻን ወደ አጐቱ ላሊበላ ቤተ መንግስት ውስጥ ገባ::

የቅዱስ ላሊበላ ቤት ደግሞ በቅድስና ያጌጠ ነውና ከርሱና ከሚስቱ (ቅድስት መስቀል ክብራ) ሕጻኑ ነአኩቶ ለአብ ምናኔና ፍቅረ ክርስቶስን ተማረ:: በዘመኑ ብዙ ሊቃውንት ስለ ነበሩ ቅዱሳት መጻሕፍትን በደንብ አጠና:: ክህነት ተቀብሎ ቤተ ክርስቲያንን ሲያገለግልም እድሜው 30 ደረሰ:: በወቅቱ ቅዱስ ላሊበላና ባለቤቱ መስቀል ክብራ ልጃቸው ይትባረክ እያለ ንግሥናቸውን ለቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አወረሱ::

ቅዱሱ ነአኩቶ ለአብም ምን እንደሚሠራ ሲያስብ አንድ ነገር ተገለጠለት:: ቤተ መንግስቱን እንደሚገባ ካደራጀ በኋላ በቤት ውስጥ አንድ ጉድጓድን በቁመቱ ልክ አስቆፈረ:: በውስጡም በ4 አቅጣጫ ጦሮችን ተከለባቸው:: ድንግል ካህን ነበረና ቀን ቀን ሃገር ሲያስተዳድር: ቅዳሴ ሲቀድስ: በጾም ይውላል:: ሌሊት ደግሞ ወዳስቆፈረው ቦታ ገብቶ ያለማቋረጥ እየጸለየ ይሰግዳል:: ወደ ምድር ሲሰግድ በፊቱ ያለው ጦር ይወጋዋል:: ቀና ሲል ደግሞ የጀርባው ይቀበለዋል:: እንዲህ እያለ የፈጣሪውን ሕማማት ይካፈላል:: በተለይ ዐርብ ዐርብ ሲሆን ደሙ: እንባውና ላበቱ ተቀላቅሎ ይፈስ ነበር:: እርሱ መስቀሉን ተሸክሞ ጌታውን ይከተል ዘንድ መርጧልና::
ከተጋድሎው ጐን ለጐን ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አብያተ ክርስቲያናትንም ያንጽ ነበር:: በተለይ በ1211 ዓ.ም አካባቢ ያነጻት አሸተን ማርያም ልዩ ናት:: እርሷን ካነጸ በኋላ ከቤተ መንግስቱ በደመና ሠረገላ ተጭኖ እየሔደ ያጥናት: ይቀድስባትም ነበር:: ታዲያ አንድ ቀን አጥኖ ከቤተ መቅደስ ሲወጣ ብዙ ሥውራን ቅዱሳን መቅደሱን ከበው ተመለከተ:: እርሱም "ወገኖቼ! ከወዴት መጣችሁ?" ቢላቸው "መዐዛ እጣንህን አሽተን መጣን" ሲሉ መለሱለት:: በዚህ ምክንያትም እስከ ዛሬ ድረስ "አሽተን (አሸተን) ማርያም" ስትባል ትኖራለች:: ዛሬ ታቦቱ ያለበት ገዳሙም በእርሱ የታነጸ ሲሆን እጅግ ተአምረኛ ቦታ ነው::

ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ የነገሠ በ30 ዓመቱ ነው:: ለ40 ዓመታት በእንዲህ ያለ ቅድስና ኑሮ 70 ዓመት ሞላው:: በዚህ ጊዜም ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ሰላምታንም ሰጠው:: "ወዳጄ ነአኩቶ ለአብ! አንተ ስለ እኔ ፍቅር ለ40 ዓመታት መከራን ተቀብለሃልና ሞት አያገኝህም:: ክፍልህ ከነ ኤልያስ ጋር ነውና:: የሚያከብርህን አከብረዋለሁ:: ደጅህን የሳመውን: ይህ ቢያቅተው በሩቁ ሆኖ በአድናቆት የተመኘህን: መታሰቢያህን ያደረገውን ሁሉ እምርልሃለሁ" አለው:: ቀጥሎም "ይሕች ቤት አንተ ስትደማ እንደኖርክባት እርሷም እስከ ምጽዓት ድረስ ለመታሰቢያህ ስትደማ ትኑር" አለው:: እነሆ ዛሬም ድረስ ከመቅደሱ ጠበል ይንጠበጠባል:: ለዚህም ደግሞ እኛ ኃጥአን ምስክሮች ነን:: ሳይገባን የቅዱሱን ደጅ ተመልክተናልና:: ቅዱስ ነአኩቶ ለአብም የዚህን ዓለም ተጋድሎውን ፈጽሞ ወደ ብሔረ ሕያዋን መላእክት ወስደውታል:: የተሰወረበትን ዕለት ስንክሳር ሕዳር 1 ሲያደርገው አንዳንድ መዛግብት ደግሞ በ3 ነው ይላሉ:: በዙፋኑም ላይ የአጐቱ የላሊበላ ልጅ አፄ ይትባረክ ተተክቷል::

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ ንጉሥ ጸሎት ይማረን!!! አሜን
26 viewsbisrat, 15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 18:12:17
2 viewsbisrat, 15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 18:11:56 #ጥቅምት_28_ከተስዓቱ_ቅዱሳን_አንዱ_የአባ_ይምዓታ_ዕረፍታቸው ነው::

=>ጻድቁ አባ ይምዓታ ሃገራቸው የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ነው::

ዘጠኙ ቅዱሳን ተወልደው ያደጉት ምንም በአንድ የሮም ግዛት ሥር ቢሆንም መነሻ ቦታቸው ግን የተለያየ ነው::

ሁሉንም አንድ ያደረጋቸው መንፈስ ቅዱስ በኪነ ጥበቡ ነው:: በምክንያት ደረጃ እንግለጸው ከተባለ ደግሞ የአንድነታቸው ምሥጢር:-
1.የቀናች ሃይማኖታቸው ተዋሕዶ::
2.ዓላማ (የእግዚአብሔር መንግስት) እና 3.ገዳማዊ ሕይወት ነው::

አባ ይምዓታን ጨምሮ ሁሉም ቅዱሳን ዘራቸው ከቤተ መንግስት ነው:: እነርሱ ግን ምድራዊውን ክብር ንቀው ሰማያዊውን ክብር ገንዘብ ማድረግን መርጠዋል:: አስቀድመው ቅዱሳት መጻሕፍትን ያጠኑት አበው በተለያየ ጊዜ እየመነኑ ከሮም ግዛት ወደ ግብጽ በርሃዎች ወርደዋል::

በምናኔ ቅድሚያውን አባ ዸንጠሌዎንና አቡነ አረጋዊ ይይዛሉ:: ዘመኑ የተዋሕዶ አማኞች የሚሰደዱበት 5ኛው መቶ ክ/ዘመን ነበርና እምነትን ላለመለወጥ ዘጠኙ ቅዱሳን ስደትን መረጡ::

በወቅቱ ደግሞ ለስደት መጠለያ የምትሆንና ከኢትዮዽያ የተሻለች ሃገር አልነበረችም:: ስለዚህም በ470ዎቹ ዓ/ም አልዓሜዳ በኢትዮዽያ ነግሦ ሳለ ቅዱሳኑ በአረጋዊ መሪነት መጡ::

ንጉሡም ሲጀመር የእግዚአብሔር እንግዳ ስለሆኑ: ሲቀጥል ደግሞ ቅድስናቸውን ተመልክቶ መልካም አቀባበልን አደረገላቸው:: ማረፊያ ትሆናቸውም ዘንድ አክሱም ውስጥ አንዲት ቦታን ወስኖ ሰጣቸው:: ይህች ቦታ "ቤተ ቀጢን" ትባላለች:: አባ ይምዓታና 8ቱ ቅዱሳን ወደ ሃገራችን እንደ ገቡ የመጀመሪያ ሥራቸው ቁዋንቁዋን መማር ነበር::

ልሳነ ግዕዝን በወጉ ተምረው እዛው አክሱም አካባቢ ሥራቸውን አንድ አሉ:: በወቅቱ በአቡነ ሰላማ: በአብርሃ ወአጽብሐና በአቡነ ሙሴ ቀዳማዊ የተቀጣጠለው ክርስትና በተወሰነ መንገድ ተቀዛቅዞ ነበርና እነ አባ ይምዓታ እንደ ገና አቀጣጠሉት::

ሕዝቡን በራሱ ልሳን ለክርስትና ይነቃቃ ዘንድ ሰበኩት:: የካደውን እየመለሱ: የቀዘቀዘውን እያሟሟቁ ለዓመታት ወንጌልን ሰበኩ:: ቀጣዩ ሥራቸው ደግሞ መጻሕፍትን መተርጐም ሆነ::

ከሃገራቸው ያመጧቸውን ቅዱሳት መጻሕፍት ተከፋፍለው ወደ ግዕዝ ልሳን ተረጐሟቸው:: በዚህም ለሃገራችን ትልቁን ውለታ ዋሉ:: ይህ ሁሉ ሲሆን እነ አባ ይምዓታ የሚመገቡትም ሆነ የሚጸልዩት በማሕበር ነበር:: በመካከላቸውም ፍጹም ፍቅር ነበር:: ጸጋ እግዚአብሔር አልተለያቸውም::

የነ አባ ይምዓታ ቀጣዩ ተግባራቸው ደግሞ ገዳማዊ ሕይወትን ማስፋፋት ሆነ:: ይህንን ለማድረግ ግን የግድ መለያየት አስፈለጋቸው:: እያንዳንዱም መንፈስ ቅዱስ ወደ መራው ቦታ ሔደ::
*ዸንጠሌዎን በጾማዕት::
*ገሪማ በመደራ::
*ሊቃኖስ በቆናጽል::
*አረጋዊ በዳሞ::
*ጽሕማ በጸድያ::
*ሌሎችም በሌላ ቦታ ገዳማትን መሠረቱ::

*አባ ይምዓታ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ምርጫቸው ገርዓልታ (እዛው ትግራይ) ሆነ::

ጻድቁ ወደ ቦታው ሲሔዱ ወንዝ (ባሕር) ተከፍሎላቸዋል:: ወደ ቦታው ደርሰውም ገዳም አንጸዋል:: በቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠርተው በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፍርተዋል:: የአቡነ ይምዓታ ገዳም ገርዓልታ እንደምናየው እጅግ ድንቅና ማራኪ ነው:: ገዳሙ ከባሕር ወለል በላይ በ2300 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ያለበት የተራራው ርዝመት ብቻውን 300 ሜትር ነው::

ቤተ መቅደሱ በር ላይ ለመድረስ በጭንቅና በፍርሃት ሆኖ ተራራውን እንደዝንጀሮ በእጅ እየቧጠጡ መውጣት ይጠይቃል:: እርሱም ቢሆን በገዳሙ አባቶች እገዛና ድጋፍ ነው::

ቤተ መቅደሱ እጅግ የሚደንቀው በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ ብቻ አይደለም ውስጡ ያሉት የግድግዳ ላይ ሥዕሎችም በ6ኛው መ/ክ/ ዘመን የተሣሉ እጅግ ድንቅና ጥንታዊ ናቸው::

ጻድቁ በዚሁ ራሳቸው ባቀኑት ገዳመ ገርአልታ ለዘመናት ተጋድለው ጥቅምት 28 ቀን ዐርፈዋል::
3 viewsbisrat, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-04 21:47:21
30 viewsbisrat, 18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-04 21:45:27 #ጥቅምት_27_የመድኃኔዓለም_ክርስቶስ_የስቅለቱ_መታሰቢያ_በዓል_ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ደኅንነት በሰው ባህርይ ተገለጠ ፥ በዓለም በሰዎች መካከል ተመላለሰ ፥ ዓለም ከጥፋት ይድን ዘንድ ዓለሙ የሚድነበትን ሁሉ ሠራ፥ አስተማረም ። ዓለም የሚድነውም በአንድ በራሱ በእግዚአብሔር ልጅ መሥዋዕትነት ነበረ ። ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ በመስቀል ላይ እስከ አቀረበባት ዕለት ድረስ ፥ ብዙ ሠርቶአል፥ አስተምሯል ፥ ተናግሯልም።

በመስቀል ላይ ሁኖ (ተቸንክሮ) የተናገራቸው ቃላተ ርኅራኄ ሰባት ናቸው ። እነርሱም:-

1. " አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው"

መላእክት በቀትር ፈጣሪያቸውን ሊያመሰግኑ ሲመጡ ኢየሱስ ክርስቶስ ራቁቱን በቀራንዮ አደባባይ በእንጨት ላይ ተሰቅሎ ፊቱ ደም ለብሶ ሲያዩት ደንግጠው እንደ ሻሽ ተነጸፉ እንደ ቅጠል ረገፉ፡፡ ከዚህ በኋላ መልአኩ ሚካኤል ዝም ሲል መልአኩ ገብርኤል ግን በጣም ተበሳጭቶ አይሁድን በሰይፍ ሊያጠፋቸው ሰይፉን አነሣ የዚህን ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስ እነርሱን ተዋቸው አታጥፋቸው የሚሠሩትን እና የሚደርጉትን ስለማያውቁ ነው ብሎታል፡፡ ገብርኤል ግን የአንተ ቸርነት አያልቅም ብሎ ተቆጥቶ ሰይፉን ወረወረው ሰይፉም የቤተ መቅደሱን መጋረጃ ለሁለት ከፍሎ ወደ መሬት ገባ እስካሁንም ድረስ ወደታች ሲሄድ ይኖራል፡፡ በዚህም በነቢዩ ኢሳይያስ  "እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ" ተብሎ የተነገረው ትንቢት ፍጻሜ አገኘ (ኢሳ.53:12)።

2."አምላኬ አምላኬ ሆይ ስለምን ተውከኝ?"

ጌታችን ይህን የተናገረበት ምክንያት አንደኛ ራሱን መስዋዕት አድርጎ ስላቀረበላቸው ምእመናን ተገብቶ ነው ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው (ዮሐ 17:11) ብሎ ያቀረበውን ያስቧል። አንድም በመዝሙረ ዳዊት 22:1 የተጠቀሰውን ትንቢት አይሁድ ስለሚያውቁ ፥ መሲሕ ክርስቶስ መሆኑንና ትንቢት መፈጸሙን መግለጡ ነው ።
ሁለተኛ ለአቅርቦተ ሰይጣን ነው ። ሰይጣንም ይህንን ቃል ከጌታችን ሰምቶ መሲሑ ክርስቶስ መስሎኝ ነበር እሩቅ ብእሲ ነው ብሎ ነፍሱን ከሥጋው ለይቶ ለመውሰድ ሲቀርብ በእሳት አውታር ወጥሮ ኃይሉን አጥፍቶ በነፍሳት ላይ ያለው ሥልጣኑን ገፎ ጥሎታል ።
መናፍቃን ግን አብ በልጁ ስለ ጨከነበት፥ ፊቱን ስለ አዞረበትና ስለ ተወው ጸሎት ማሰማቱ ነው ይላሉ ።

3. "ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ"

ከጌታ ጋር 2 ወንበዴ ሽፍቶች አብረው ተሰቅለው ነበር፡፡ አንደኛው በቀኝ ያለው ጥጦስ በሰማይ 3 በምድር 4 ተአምራት ሲደረጉ አይቶ "ጌታ ሆይ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ" እያለ ሲጸልይ ጌታ ወደ የማናይ አንገቱን ዘንበል አድርጎ "ግብጽ ስንወርድ የነገርሁህ ሁሉ ደረሰ" አለው፡፡ "ስለዚህ ከሞቴ በቀር የቀረኝ የለምና አንተ አዳምን ቀድመህ ገነት ትገባለህ" ብሎ ደመ ማኅተሙን ሰጥቶት አዳምን ቀድሞ ገነት ግብቷል፡፡
መናፍቃን ይህን ሥልጣኑን ባለመገንዘብ ዛሬም አብን / ወደ አብ እየለመነ ያማልደናል ይሉናል።

 4."እነሆ ልጅሽ ፥ እነኋት እናትህ"
 ጌታችን የተሰቀለ ዕለት እመቤታችን በከተማው ውላ ነበርና ጌታችን ዮሐንስን ጠርቶ እናቴን ጥራልኝ መከራየን ትመልከት አለው፡፡ ዮሐንስም ሄዶ እመቤታችንን እነሆ ልጅሽን ሰቀሉት ሲላት እርሷም ደንግጣ በሐዘን እያለቀሰች እየወደቀች እየተነሣች ከተሰቀለበት ቦታ ደርሳለች፡፡ በዚያም ራቁቱን ተሰቅሎ ስታይ ምርር ብላ አለቀሰች መልአኩ ጌታን ትወልጃለሽ ብሎ ያበሰረኝ ብሥራት ሞት ሆኖ በገደለኝ ነበር እያለች አለቀሰች፡፡ ጌታም እናቴ ሆይ ብታለቅሽ ብታለቅሽ አይታክትሽምን እኔ ካልሞትሁላቸው 5500 ዘመን በዲያብሎስ ቁራኝነት የተያዙ ነፍሳት አይድኑም ዛሬ መከራው ሐዘኑ እንደበዛብሽ ነገ ዘመዶችሽ ብርሃን ለብሰው ከሲዖል ሲወጡ ስታዪ ደስታሽ ይበዛልና ተዪ አታልቅሽ አላት፡፡ የታመመ ሰው ልጄን ሚስቴን አደራ እንዲል እንዲሁ ጌታም እናት ትሆነው ዘንድ እርሱም ልጅ ይሆናት ዘንድ ለዮሐንስ አደራ ብሎታል፡፡ ይህን ቃል የተናገረው ለዚሁ ነው፡፡
ምእመናንንም ለቅድስት ድንግል ማርያም የአደራ ልጆች ፥ ድንግል ማርያምንም ለምዕመናን የአደራ እናት አድርጎ ሰጠ ። ይህም ለእመቤታችን ከአንድ ልጅዋና ከደቀ መዛሙርቱ በቀር ምንም ዘመድና ረዳት እንዳልነበራት ያስረዳል ። መናፍቃን ግን ሌሎች ልጆች ወልዳለች ፤ ለዮሐንስም እንዲንከባከባት ተሰጠች እንጂ ለምእመናን አልተሰጠችም ብለው ክህደትን ያስተምራሉ።

5. "#ተጠማሁ" 
ሲላቸው ወሃቤ ማየ ሕይወት ለሆነው ክርስቶስ አይሁድ መጣጣ አቀመሱት። ይህም የሆነው "በመብሌ ሐሞት ጨመሩ ለጥማቴም ሆምጣጤ አጠጡኝ (መዝ 69:21) ተብሎ የተነገረውን ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው ። አንድም ከሰው ልጅ ምግባር ፈልጌ አጣሁ ሲል ነው ።

6."#አባት_ሆይ_ነፍሴን_በእጅህ_አደራ_እሰጣለሁ"
ብሎ በራሱ ሥልጣን ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው የለየበት ቃል ነው (ዮሐ 10:11-17 ተመልከት) ። በዘመነ ኦሪት ጊዜ የነበሩ ሰዎች ነፍስ ከሥጋቸው እየተለየች ሲዖል ትወርድ ነበር አሁን ጌታ ከተሰቀለ በኋላ ግን ገነት ይገቡ ጀመር፡፡ ስለዚህ ነፍሳችን እንደ ኦሪቱ ሲዖል ብቻ ሳይሆን ገነት መንግሥተ ሰማያትም እንደምትገባ ሲናገር ነው፡፡ አንድም አዳምን ተቀድሞ ጥጦስ ገነትን በደመ ማኅተሙ ከፍቶ ገብቷልና ገነት መግባት መጀመሩን ያሳያል፡፡

7. "ሁሉ ተፈጸመ"
ተፈጸመ ብሎ የተናገረው የመጨረሻው ቃል ነው ። አምላክ የመጣበት የድኅነት ሥራ በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰስ ሥጋውን በመቁረስ እንደፈጸመው እንደደመደመው ሲናገር ነው፡፡ በመጻሕት የተጻፈው በነቢያት የተነገረው ሁሉ ደረሰ ሁሉ ነገር ተፈጸመ ሲል ነው፡፡

እነዚህን ሰባቱን የርኅራኄ ቃላትን መጋቢት 27 ዕለት በመስቀል ላይ ሆኖ ተናግሮ እራሱን ወደቀኝ ዘንበል አድርጎ ነፍሱን ከሥጋው በገዛ ሥላጣኑ ለየ፡፡

#ምስጋና_ይሁን_ለአብ_ምስጋና_ይሁን_ለወልድ_ምስጋና_ይሁን_ለመንፈስ_ቅዱስ፡፡ አሜን!!!
27 viewsbisrat, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 19:15:24
38 viewsbisrat, 16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 19:15:10 #ቅዱሳት_ሥዕላት_በቤተክርስቲያን_ለምን_አስፈለጉ?

ቅዱሳት ሥዕላት ጥልቅ የሆነ መንፈሳዊ መልእክት ያስተላልፋሉ፡፡

የክርስትና አንደበት ናቸው፡፡

በመጀመያዎቹ ክርስቲያኖች ዘመን ቅዱሳት ሥዕላት ማስተማሪያ ነበሩ፡፡

ቅዱሳት ሥዕላት በጸሎት ጊዜ ሐሳባችንን ሰብስበን በእግዚአብሔር ፊት መቆማችንን አስበን እንድንጸልይ ይረዱናል፡፡

የእግዚአብሔር መገለጫዎች ናቸው፡፡
ለመንፈሳዊው የክርስትና መልእክት መገለጫ የሆኑት ቅዱሳት ሥዕላት ከዓለም ፎቶዎችና ምስሎች ይለያሉ፤ የእግዚአብሔር ኃይሉና ክብሩ ይገለጥባቸዋልና፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የቅዱሳት ሥዕላት የአሣሣል ዘይቤና የኅብረ ቀለም ምርጫ ትውፊትን መሠረት ያደረገ ነው፡፡

የክርስትናው ትምህርት ማንፀባረቂያ በመሆናቸው ምሳሌዎችን በማመሳጠር ይሣላሉ፡፡

የሰማዕታት በቀይ ቀለም፣ የክርስቶስ በነጭ ቀለም፣ የድንግል ማርያም ነጭ፣ ሰማያዊ እና ቀይ በሆነ የቀለም ምርጫ ይሣላሉ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስን ጋሻ አስይዞና ቅዱስ ሚካኤልን እግሩን አራቁቶ መሣል የቤተ ክርስቲያን ትውፊት አይደለም፡፡

በቤተ ክርስቲያን የሥዕላት አደራደር ክብርንና ምስጢርን መሠረት ያደረገ ነው፡፡

ከላይ፡- የሥላሴና የክርስቶስ ስቅለት
በግራ፡- የእመቤታችን ሥዕለ አድኖና የቅዱሳን መላእክት ሥዕል በቀኝ፡- የሐዋርያት፣ የዮሐንስ መጥምቅ፣ የቅዱሳንና የሰማዕታት በቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ የሰጎን እንቁላልና የመስቀል ምልክት ይደረጋል፡፡

 ቅዱሳት ሥዕላት የክርስትና ጥልቅ መልእክት ገላጮች ናቸው፡፡ በጸሎት ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት መቆማችንን እንድናስተውል ይረዱናል፡፡ በቤተ ክርስቲያን የሥዕላት አሣሣልና አቀማመጥ ትውፊትን መሠረት ያደረገ ነው፡፡

የሠራዊት አምላክ ሆይ ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው፡፡ ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትናፍቃች፡፡” (መዝ.83÷1)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
38 viewsbisrat, 16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 20:20:18
26 viewsbisrat, 17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ