Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-05-08 11:23:29
158 viewsbisrat, 08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 11:23:17 የደጉዋ እናት ልደት/
በኢየሩሳሌም አገር የሚኖሩ ኢያቄምና ሃና የተባሉ
በጣም ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ ኢያቄምና ሃና
ለእግዚአብሔር የታዘዘ በተቀደሰ ጋብቻ ውስጥ
በብዙ ዘመናት አብረው ቢኖሩም በነዚያ ጊዜያት
ወስጥ አንድ ልጅ እንኳ ስላልነበራቸው እጅግ
ያዝኑ ነበር፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ እየሄዱ
እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው
ይለምኑት ነበር፡፡
ከእለታት አንድ ቀን ኢያቄምና ሃና እርግቦች
ጫጩቶቻቸውን ሲያጫውቱ ተመልክተው
“ለነዚኽ ወፎች እንኳ ልጆችን የሰጠህ አምላክ
ለእኛስ መች ይሆን ልጅ የምትሰጠን?” ብለው
እጅግ አምርረው አለቀሱ፡፡ ከሐዘናቸውም ጽናት
የተነሳ እንቅልፍ ያዛቸውና ተኙ፡፡
በተኙ ግዜም ለሁለቱም እግዚአብሔር መልካም
ፈቃዱን በህልም ገለጠላቸው፡፡ ኢያቄም
በህልሙ ሃና በእቅፍ ውስጥ ከፍሬዎች ሁሉ
የምትበልጥ መልካም ጣፋጭ ፍሬ ይዛ
ተመለከተ፡፡ ሃና የኢያቄም በትር ለምልማ፣
አብባና አፍርታ ተመለከተች፡፡ ከእንቅልፋቸውም
ነቅተው ስለ ህልማቸው ተነጋገሩ፡፡
የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲሆንላቸው በጸሎት
ጠየቁ፡፡ እግዚአብሔር ወንድም ሆነ ሴት ልጅ
ቢሰጣቸው አድጎ እኛን ያገልግለን ይታዘዘን ሳይሉ
ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ እንዲሆን
እንደሚሰጡት ቃል ገቡ፡፡
ከዚህ በኋላ ነሐሴ 7 ቀን ሃና ፀነሰች፡፡ ሃና
በእርጅናዋ ጊዜ መፅነሷ የተመለከቱ ዘመዶቿና
ያገሯ ሰዎች ተገርመው እየመጡ ይጠይቋት
ነበር፡፡ ከነዚህም ሰዎች መካከል አንዱ ዐይነ
ስውር የነበረችው የአርሳባን ልጅ ናት፡፡ የአርሳባን
ልጅ ወደ ሃና መጥታ እውነትም ሃና መጽነሷን
ለማረጋገጥ ሆዷን ዳሰሰቻት፡፡ በአድናቆትም
ሳታስበው ዐይኗን ስትነካ ዐይኗ በራላት፡፡ በሌላ
ግዜም የአጎቷ ልጅ በህመም ምክንያት ይሞትና
ሃና ትወደው ስለነበር ልታለቅስ ወደአረፈበት ቤት
ትሔዳለች፡፡ እንደደረሰችም አስክሬኑ
በተቀመጠበት መካከል አልጋ ዙሪያ ስታለቅስ ሳለ
ድንገት ጥላዋ ቢያርፍበት የሞተው ሰው ተነስቶ
ሃና የአምላክ እናት የምትሆን እመቤታችንን
እንደምልድና በዚህም ሃና እጅግ የከበረችና
ምስጋና የሚገባት መሆኗን መሰከረ፡፡
ሃና በፀነሰች ግዜ የተደረጉ ብዙ ተአምራትን
አይሁድ አይተው ገና በፅንስ ግዜ ይህን ያክል
ተአምራት ያደረገ ሲወለድማ ብዙ ነገር ያደርጋል
ብለው በምቀኝነት ተነሳስተው ኢያቅምና ሃናን
ሊገድሏቸው ተነሱ፡፡ እግዚአብሔር ግን መልአኩን
ልኮ ኢያቄምና ሃና ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሸሹ
አደረጋቸው፡፡ በዚያም ሆነው ግንቦት 1 ቀን
ከንጋት ኮከብ ይልቅ የምታበራ እጅግ ያማረች
የተቀደሰች የምትሆን ልጅን ወለዱ፡፡ ስሟንም
ማርያም አሏት፡፡ እንኳን ለእመቤታችን
ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም
አደረሳችሁ፡፡
136 viewsbisrat, 08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 07:08:16
156 viewsbisrat, 04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 07:07:55 ዳግማይ ትንሣኤ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በአይሁድ ዘንድ ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን የሚባሉ ሁለት የተለያዩ ማኅበሮች ነበሩ ፤ ፈሪሳውያን ፋሬስ በተባለው ሰው ስም ፈሪሳውያን ተብለዋል ፤ ሰዱቃውያን ደግሞ ሳዶቅ በሚባል ሰው ሰዱቃውያን ተብለዋል፡፡ 
ፈሪሳውያን የሚባሉት ከሞት በኋላ ትንሣኤ አለ ብለው ያምናሉ ነገር ግን ከሞት በኋላ ልክ አሁን እንዳለው ኑሮ ጋብቻ በመመስረት የሚኖር አድርገው ነው የሚቀበሉት ፤ ሰዱቃውያን ደግሞ የሰው ልጅ ከሞተ በኋላ ደግሞ አይነሣም ብለው ያምናሉ፡፡


በመግቢያው ላይ የተጠቀሱት ሁለቱም ማኅበራት ጌታችንን ለመክሰስ ምክንያት ይፈልጉ ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀርበው እንዲህ ብለው ጠየቁት ‹‹መመህር ሆይ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ ፤ ሰባት ወንድማማቾ በእኛ ዘንድ ነበሩ ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ ዘርህም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት ፤ እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም እስከ ሰባተኛው ድረስ እንዲሁ ሆነ፡፡ በመጨረሻ ሴቲቱ ሞተች ፤ ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ 
ቀንስ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች?›› ብለው ጠየቁት፡፡ ጌታችንም ሲመልስ ‹‹የሰው ልጆች በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም፡፡›› አላቸው ፤ በዚህም ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንን ዝም አሰኛቸው፡፡ ጌታችን ሲመልስ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ፤ ነገር ግን ኑሮ እንደ መላእክት እንጂ በምድር እንዳለው ኑሮ እንዳልሆነ በመንገር ለሁለቱም መልስ ሰጥቷል፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለመግደላዊት ማርያም ታያት እርሷም ለሐዋርያት ንገሪ በላት መሠረት ነገረቻቸው ፤ ሐዋርያትም አይሁድን ፈርተው በተዘጋ ቤት በፍርሃት ተሰብስበው ሳሉ ፤ ጌታችን በሩን ሳይከፈት በመካከላቸው ተገኘ ‹‹ሰላም ለኩልክሙ›› ‹‹ሰላም ለእናንተ ይሁን›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም እፍ ብሎ የክህነት ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡ 

ጌታ ለሐዋርያቱ እንዲህ ባለ መልክ ሲገለጥ ከ12ቱ ሐዋርያት መካከል ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ፤ ቅዱስ ቶማስ በሌላ ስሙ ዲዲሞስ ይባላል፡፡ ጌታችን ይህን ሰው ከሰዱቃውያን መካከል ነበረ ለሐዋርያነት የመረጠው፡፡ (ሰዱቃውያን ምን ብለው የሚያምኑ ሕዝቦች ናቸው?) 

በሌላው ጊዜ ቅዱስ ቶማስ ወደ ሐዋርያት ሲመጣ ፤ ጌታን ከሞት ተነሥቶ አይተነዋል አሉት፡፡ ቅዱስ ቶማስ ሰዱቃዊ ስለነበረ ከሞት በኋላ መነሣት የሚለውን ነገር አይቀበልም ነበር ፤ ስለዚህም እንዲህ አላቸው ፤ ‹‹የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም›› አላቸው፡፡ ሁሉም ቢነግሩትም አላምን ማለቱ አስገርሟቸው ነበር፡፡ 

ጌታችን ከታያቸው ከስምንት ቀን በኋላ በድጋሜ ሐዋርያት በተዘጋ ቤት ተሰብስበው ነበር ፤ እንደ ቀድሞው አይጨነቁም ነበረ እረኛቸው ከሞት ተነሥቷልና፡፡ በዚህ ሁኔታ ሳሉ ጌታችን ቀድሞ እንዳደረገው ደጃፉ ሳይከፈት በመካከላቸው ተገኝቶ ‹‹ሰላም ለኩልክሙ›› ‹‹ሰላም ለእናንተ ይሁን›› በማለት ዳግም ተገለጠላቸው ለሁለተኛም ጊዜ ታያቸው፡፡ ቅዱስ ቶማስ ይህን ሲመለከት ልቡ ደነገጠ ፤ ጌታችንም ማንም ሳይነግረው ቶማስ በልቡ መጠራጠሩን አውቆ ‹‹ጣትህን ወደዚህ አምጣና በጎኔ አግባው ፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን›› አለው፡፡ ቶማስም ጣቱን ወደ ጌታ ጎን አስገባ ፤ በደሰሰውም ጊዜ እጆቹ ተኮማተሩ ያን ጊዜ ‹‹ጌታዬ አምላኬ›› ብሎ መለሰለት፡፡ ቶማስም እምነቱ ጸናለት፡፡
131 viewsbisrat, 04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 19:43:22
118 viewsbisrat, 16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 19:42:43 ሰሙነ ትንሣኤ ክፍል ፪
አዳም ሐሙስ
አዳም የመጀመሪያ ሰውና የሰው ሁሉ አባት ነው፤
በ፮ኛው ቀን የተፈጠረ የሰው ሁሉ ምንጭ ስለሆነ
የሰው ዘር ሁሉ ከእርሱ ተገኝቷል፡፡ በዚህ ዕለት
ለአዳም የተሰጠው የተስፋ ቃል ስለመፈጸሙ፤
(ዘፍ. ፫÷፲፭) አዳም ከነልጆቹ በክርስቶስ ሞትና
ትንሣኤ ነጻ ስለመውጣቱ ይታሰብበታል፡፡
ክርስቶስ በተነሳበት በአምስተኛው ቀን ሐሙስ
አዳም ይባላል፤ ጌታችን አዳምን ከአምስት ቀን
ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ
ብሎ ቃል ገብቶለት እንደነበር በቀሌምንጦስ
ተጽፏል፡፡
አዳምና ሔዋን በገነት ፯ ዓመት ከቆዩ በኋላ
ትእዛዙን በመተላለፋቸው ከኤደን ገነት
አስወጣቸው (ኩፋ.፬፥፲፮፤ዘፍ.፫፥፳፫) «ብዙ
ተባዙ» ያለው ቃል እንዳይቀር በምድር ላይ
ወርደው ልጆችን ወለዱ ይላል፡፡ የተወለዱትም
ልጆችም በቁጥር ፷ እንደሆኑ (፩መቃ. ፳፰፥፮)
የተወለዱት ልጆች ደጎችና ክፉዎች እንደ ነበሩ
በአቤልና በቃየል ታውቋል፤ (ዘፍ. ፬፥፰)፤ አዳም
በዚህ ዓለም ፱፻፴ ዓመት ኑሮ ቅድመ ልደተ
ክርስቶስ በ፵፻፭፻፸ ሚያዚያ ፮ ዐርፏል፡፡
ዐርብ– ቤተ ክርስቲያን
ዐርብ የእግዚአብሔር ቅድስት ማደሪያ በሆነችው
ቤተ ክርስቲያን ተሰይማለች፤ ይህም ሁሉም
ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመባት ዕለት
በመሆኗ ነው፤ ዕለተ ዐርብ፤ የሥራ መከተቻ፤
ምዕራብና መግቢያ በሚሉት ስያሜዎችም
ትጠራለች፡፡
በዕለቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በመልዕልተ መስቀል ያደረገውን ተአምር
በመስቀሉ ድኅነትን እንዳሳየ፤ በቀራንዮ የሕንጻዋ
መሠረት እንደተተከለላትና ሥጋ መለኮት
እንደተቆረሰላት፤ ልጆቿን ከማሕፀነ ዮርዳኖስና
ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ የምትወልድበት ማየ
ገቦ እንደፈሰሰላት ተገልጾባታል፤
(ኤፍ.፪፥፲፱፤ራዕ.፩፥፮-፰)፡፡
ቅዳሜ– ቅዱሳት አንስት
ቅዳሜ ቅዱሳት አንስት ተብሎ ይጠራል፤ ይህም
ስያሜ በስቅለት ዕለት በልቅሶና በዋይታ
የሸኙትን፤(ሉቃ. ፳፫፥፳፯) በዕለተ ትንሣኤ ሽቱና
አበባ ይዘው ወደ መቃብር የገሰገሱትን፤ ከሁሉም
ቀድሞ ጌታችን በዕለተ ሰንበት ተነሥቶ
ለተገለጸላቸው ማርያም መግደላዊት፤ የታናሹ
ያዕቆብ እና የዮሳ እናት ማርያም፤ የዘብዴዎስም
የልጆቹ እናት ሰሎሜንም መታሰቢያ ለማድረግ
ነው፤«ከሳንምንቱ በመጀመሪያዩቱ ቀን ያዘጋጁትን
ሽቶ ይዘው እጅግ ማልደው ወደ መቃብሩ
ሄዱ፤ሌሎች ሴቶችም አብረዋቸው ነበሩ (ሉቃ.
፳፬ ፥ ፩ )፡፡
እሑድ– ዳግም ትንሣኤ
«ያም ከሳምንቱ የመጀመሪያው ቀን በመሸ ጊዜ
ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለ ፈሩ ተሰብስበው
የነበሩት ቤት ደጁ ተቆልፎ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ
መጥቶ በመካከላቸው ቆመና÷«ሰላም ለእናንተ
ይሁን» አላቸው፤ ማቴ.፳፥፲፱፡፡ ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ተሰውሮ ከሰነበተ
በኋላ በዕለተ እሑድ በዝግ ቤት እንዳሉ ዳግም
ተገለጸላቸው፤ስለዚህም ዳግም ትንሣኤ ተባለ፡፡
( ምንጭ :-መዝሙረ ማኅሌት ወቅዳሴ፤ ሥርዓተ
አምልኮ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፤ የዮሐንስ ወንጌል
አንድምታ፤ ምዕ. ፳፥፳፬)
116 viewsbisrat, edited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 21:11:15
144 viewsbisrat, 18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 21:10:54 ሰሙነ ትንሣኤ
ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ ድረስ ያሉ ቀናት
መጠሪያቸው የሚከተለውን ይመስላል፡፡
እሑድ፦ በዓለ ትንሣኤ ሲሆን ። ጌታችን
መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ሦስት ሌሊት
ሦስት መዓልት በከርሠ መቃብር አድሮ መነሳቱን
የምናስታውስበትና የመስቀል መርገምነቱ ቀርቶ
ትንሣኤነቱ የታወቀበት፤ ሙስና መቃብር
የተሻረበት ትንሣኤያችንን በትንሣኤው
ያረጋገጥንበት ዕለት ነው።
ሰኞ፦ ፩ኛ ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት (መሻገሪያ፣ መሻገር) ማለት
ነው። ምሳሌው ቀድሞ እስራኤላውያን ባሕረ
ኤርትራን ተሻግረው ምድረ ርስት ገብተዋል።
ምሳሌውም ፈርዖን የዲያብሎስ፣ ሠራዊቱ
የሠራዊተ ዲያብሎስ፣ ግብፅ የሲኦል፣ ባሕረ
ኤርትራ የባሕረ ሲኦል፣ እስራኤል የምእመናን፣
ሙሴ የወልደ እግዚአብሔር፣ በትረ ሙሴ
የመስቀል ምሳሌ እስራኤላውያን በሙሴ መሪነት
ተሻግረው ምድረ ርስት እንደገቡ ነፍሳትም
በክርስቶስ መሪነት ባሕረ ሲኦልን ተሻግረው ገነት
የመግባታቸው ምሳሌ ነው። በዚህም ማዕዶት
ይባላል።
፪ኛ ዕለተ አብርሃም (ዕለቱ ለአብርሃም) ይባላል።
አብርሃም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ከነዓን ገብቷል።
በዚህም አንጻር ምእመናንም ባሕረ ሲኦልን
ተሻግረው ገነት የመግባታቸው ምሳሌ ነው።
አንድም አብርሃም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ቢሄድ
መልከጼዴቅ ኅብስተ አኰቴት ጽዋዐ በረከት ይዞ
ተቀብሎታል። ነፍሳትም ባሕረ ሲኦልን ተሻግረው
ቢሄዱ ኅብስተ በረከት ጽዋዐ አኰቴት ወልድን
የማግኘታቸውና ወደ ቀድሞ የበረከት ርስት
የመመለሳቸው ምሳሌ ነው። ስለዚህ ትንቢቱ
ምሳሌው መድረሱን ለማጠየቅ ዕለቷ ማዕዶት
ትባላለች።
ማክሰኞ፦ ቶማስ ይባላል።
ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ የጌታችንን ጐን
የዳሰሰበትና እጁ የደረቀችበት እንደገና መልሳ
የዳነችበት መታሰቢያ ነው። ለቶማስ ታሪክ
መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ዕለቱ ቶማስ ይባላል።
ምንም እንኳን ታሪኩ የዳግማይ ትንሣኤ ቢሆንም
አበው ታሪክ ከታሪክ እንዳይደራረብ ብለው ነው።
ዩሐ20፤27-29
ረቡዕ፦ አልዓዛር ይባላል። ዮሐ ፲፩፥ ፵
አልዓዛር ጌታችን በጥንተ ስብከት ያስነሳው ሲሆን
ታሪኩ በዮሐንስ ወንጌል በሙሉነት ተመዝግቧል።
ከሞት የተነሳው መጋቢት ፲፯ ቀን ነው። በዚሁ ቀን
መታሰቢያ እንዳያደርጉለት የግርግር ወራት ሆነ
በ፳፪ም ሆሳዕና ሆነ፤ በ፳፫ም ርግመተ በለስ
አንጽሖ ቤተ መቅደስ ሆነ በዓሉ ከበዓል ይዋል
ብለው አበው የውኃ በዓል ከውኃ ብለው ቃና
ዘገሊላን ከጥምቀት ጥግ እንዳዋሉ ትንሣኤው
ከትንሣኤ ጋራ እንዲሄድ አደረጉ። አንድም
አልዓዛር በትንሣኤ ሥጋ እንደተነሣ እኛም ትንሣኤ
ልቡና፣ እንነሣለንና። ይቀጥላል . . .
130 viewsbisrat, 18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 18:41:43
126 viewsbisrat, 15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 18:41:27 ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
መግደላዊት ማርያምና የጌታችን ትንሳኤ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም።" (ዮሐ.20:13)

=>ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ማርያም ተገልጦ የጠፉትን ነፍሳት በሚያድንበት ዘመን ከእሥራኤል አውራጃዎች በአንዱ (በመግደሎን)
ማርያም የሚሏት ሴት ትኖር ነበር:: መግደላዊት እያሉ የሚጠሯት ሐዋርያት (ወንጌላውያን) ናቸው:: ለምን እንዲህ ብለው ጠሯት ቢሉ:- በዘመኑ ማርያም የሚባሉ ብዙ ሴቶች ነበሩና ከእነሱ ለመለየት ነው:: አንድም ሃገሯ (ተወልዳ ያደገችበት) ነውና:: +ማርያም መግደላዊት ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ነበረች ከዚህም የተነሳ ሰዎች ያደንቁዋት: ወንዶች ይከተሏት ነበር:: በዚህም 7 አጋንንት ተጠግተው 7 ዓይነት ኃጢአትን ያሠሯት ነበር:: በተለይ ደግሞ በዝሙት: በትውዝፍት (ምንዝር ጌጥ) እና ትዕቢት በእጅጉ የታወቀች ነበረች:: +በእንዲህ ያለ ግብር ጸንታ ለዘመናት ኖረች:: በዚያ ወራት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋችንን ተዋሕዶ ያስተምር ነበርና ስለ እርሱ ሰማች:: "ጌታ ኃጥአንን አይጸየፍም (ይቀበላል): አጋንንትንም ያስወጣል" ብለውም ነገሯት:: ጥሪው የእግዚአብሔር ነውና ማርያም መግደላዊት አልዘገየችም:: +ወደ እርሱ ሔዳ ጌታ ባያት ጊዜ ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና አቀረባት:: በቸርነቱም ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ የሞሉትን 7 የአጋንንት ነገድ አስወጣላት:: በዚያች ሰዓት ዕለቱኑ እንደተወለደ ሕጻን ከነበረባት ችግር ሁሉ ንጹሕ ሆነች:: ጌታም ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ ትሆን ዘንድ መርጦ ተከታዩ አደረጋት:: +ቅድስት ማርያም ከዚህች ቀን ጀምሮ ፍጹም ተቀየረች:: እርምጃዋ ሁሉ የተባረከና የንጽሕና ሆነ:: ጌታን እስከ ዕለተ ሕማሙ ድረስ በመዓልትም: በሌሊትም በቅን አገለገለችው::
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጌታችን ስለ እኛ መከራን በተቀበለባት በዚያች ዕለተ ዐርብም ከጠዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ከጐኑ ነበረች:: +ከግርፋቱ እስከ ስቅላቱ እያለቀሰች ተከትላዋለች:: በእግረ መስቀሉ ያለቅሱ ከነበሩ ቅዱሳት አንስትም አንዷ እርሷ ነበረች:: (ዮሐ. 19:25)
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የተባሉትም እግዚአብሔር የባረካቸው ደጋግ ሰዎች የጌታችንን ቅዱስ ሥጋ ከጲላጦስ ተቀብለው እያመሰገኑ በንጹሕ በፍታ ወይም የመግነዝ ጨርቅ ሲከፍኑት፤ በአዲስ መቃብርም አኑረው የመቃብሩን ደጃፍ ሲዘጉ መግደላዊት ማርያም በመቃብሩ አንጻር ተቀምጣ ትመለከት ነበር፡፡ አይሁድ የጌታችን መቃብርን እንዲጠብቁ ጠባቂ ወታደሮችን አዝዘው ነበር፡፡ መግደላዊት ማርያም እሑድ ዕለት በጠዋት የጌታችንን ቅዱስ ሥጋ ለመቀባት ያዘጋጀችውን ሽቱ ይዛ ሌሎቹንም ሴቶች አስከትላ ወደ መቃብሩ ወጣች፡፡ ወደመቃብሩ ስትደርስ የመቃብሩ ድንጋይ ተንከባሎ ነበር፡፡ በድንጋጤ ወደ ውስጥ ስትገባም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አላገኘችውም፡፡ የጌታችንን ሥጋ ማን እንደወሰደው ልታውቅ አልቻለችም፡፡ እየሮጠችም ወደ ሐዋርያት መጥታ “ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም” አለቻቸው፡፡ ጴጥሮስና ዮሐንስ ይህን በሰሙ ጊዜ ወጥተው ወደ መቃብሩ ሮጡ፡፡ ወደ መቃብሩ ውስጥ ሲመለከቱም የተከፈነበትን ጨርቅ ብቻ ተመለከቱ፡፡ ስለዚህም ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡ መግደላዊት ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ ውጭ ቆማ ቆየች፡፡ ድንገት ወደ መቃብሩ ዝቅ ብላ ብትመለከት ሁለት መላእክት የጌታችን ሥጋ በነበረበት ቦታ ላይ ተቀምጠው አየች፡፡ እነርሱም ለምን እንደምታለቅስ ጠየቋት፡፡ እርስዋም “ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም” አለቻቸው፡፡ ይህንንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል አንድ ሰው ቆሞ አየች፡፡ የአትክልት ቦታው ጠባቂ መስሏት፡፡ ሰውየው “ለምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ?” አላት እርሷም ,,የጌታዬን ሥጋ አንተ ወስደኸው ከሆነ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ” አለችው፡፡  ያነጋግራት የነበረው ሰው ግን የአትክልት ቦታ ጠባቂው አልነበረም፡፡ ማን እንደሆነ አወቃችሁ?  የሚወደን ስለ እኛ የሞተልን ከሙታንም መካከል ተለይቶ በሦስተኛው ቀን የተነሣው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር፡፡ በመጨረሻም በስሟ ማርያም ብሎ ሲጠራት አወቀችው፡፡ ከሙታን ተለይቶ እንደተነሣ ለሐዋርያት በሙሉ እንድትነግር ላካት፡፡ እርሷም በደስታ ወደ ሐዋርያት ተመልሳ ነገረቻቸው::
ጌታችንም ከእመቤታችን ቀጥሎ ከፍጥረት ወገን ትንሳኤውን ያየችና የመጀመሪያዋ የትንሳኤው ሰባኪ ትሆን ዘንድ አደላት::
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ክርስቲያኖች በሙሉ በትንሣኤ በዓል በደስታ እንዘምር አምላካችንንም እናመስግን፡፡  ይህ ታሪክ የሚገኘው ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20 ቁጥር 1 ላይ ነው፡፡

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ!!!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
129 viewsbisrat, 15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ