Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-12-01 19:15:25 #ኅዳር_23_ዕረፍቱ_ለነቢዩ_አብድዩ

“አብድዩ” ማለት “ገብረ እግዚአብሔር - የእግዚአብሔር አገልጋይ” ማለት ነው፡፡ ይኽ ስም በዘመኑ የታወቀ ስም ነበር፡፡

ነቢዩ አብድዩ ነገዱ ከነገደ ኤፍሬም ሲኾን አባቱ አኪላ እናቱም ሳፍጣ እንደሚባሉ የቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት ያስረዳል፡፡ ነቢዩ አብድዩ የአክአብ ቢትወደድ ነበር፡፡ ኤልዛቤል ነቢያት ካህናትን ስታስፈጃቸው ኃምሳውን በአንድ ዋሻ ኃምሳውን በአንድ ዋሻ አድርጐ ልብስ ቀለብ እየሰጠ ይረዳቸው የነበረውም ይኸው ነቢይ ነው /1ኛ ነገ.18፡ 3-13/፡፡

አክዓብ ሞቶ አካዝያስ ከነገሠ በኋላም አብድዩ ቢትወደድ ኾኖ ኖሯል፡፡ ነቢዩ አብድዩ ከጨዋነት ወደ ነቢይነት የተመለሰው በነቢዩ ኤልያስ አማካኝነት ነው፡፡ በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ ምዕራፍ 1 ከቊጥር 13 ላይ የተጠቀሰውና ንጉሥ አካዝያስ የላከው ሦስተኛው አለቃም ይኸው አብድዩ ነው፡፡

በነቢዩ አብድዩ የተጻፈው ትንቢተ አብድዩ ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በጣም ትንሿና 21 ቊጥሮችን ብቻ የያዘች ባለ 1 ምዕራፍ መጽሐፍ ነች፡፡ ነገር ግን ትንሽ ስለኾነች እግዚአብሔር ወደ እኛ እንዳትደርስ አላደረጋትም፡፡

ነቢዩ አብድዩ መቶውን የእግዚአብሔርን ነቢያት ገንዘቡን ሃብትና ንብረቱን ጨርሶ ተበድሮም ክፉውን ዘመን ካሻገራቸው በኋላ ብድሩን ሳይከፍል ኅዳር 23 አረፈ።

አበዳሪው ባለጸጋ የነቢዩ አብድዩን ቤተሰብ ብድሩን እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ በመምጣት አስጨነቃቸው ባለቤቱ ብድሩን ለመክፈል ሁሉንም የቤቷን ዕቃ ከዘይት ማሰሮ በስተቀር ሽጣ ግማሹን እንኳ መክፈል አቃታት።  ዘመድ አዝማዷንም ጠይቃ ብድሩን መክፈል የምትችልበትን ገንዘብ ማግኘት አልቻለችም።

አበዳሪው ግን ልጆቿን በባርነት መውሰድ የሚችልበትን ማረጋገጫ ከሃገረ ገዢው ዘንድ ተቀብሎ የበለጠ ጭንቀት ውስጥ ከተታት። ከጥቂት ቀናት በኋላ ልጆቿ በባርነት ሊወሰዱባት ስለሆነ ጽኑዕ በሆነ ሃዘን ውስጥ ሆና “የአብርሃም የይስሐቅ የእስራኤልም አምላክ እግዚአብሔር ሆይ ስለ ባለቤቴ መልካም ስራ ብለህ እባክህ እርዳኝ” እያለች አምላኳን ተማጸነች።

የለመኑትን የማይነሳ ውለታን የማይረሳ አምላክ እግዚአብሔር ከጭንቀቷ ያወጣት ዘንድ ነቢዩ ኤልሳዕን ላከላት። እርሷም ወደ ቅዱስ ኤልሳዕ "ባሌ ባሪያህ ሞቶአል፤ ባሪያህም እግዚአብሔርን ይፈራ እንደ ነበረ አንተ ታውቃለህ፤ ባለ ዕዳ ልጆቼን ባሪያዎች አድርጎ ሊወስዳቸው መጥቶአል" ብላ ጮኸች። ነቢዩ ኤልሳዕም "አደርግልሽ ዘንድ ምን ትሻለሽ? በቤትሽ ያለውን ንገሪኝ አላት። እርስዋም  "ለእኔ ለባሪያህ ከዘይት ማሰሮ በቀር በቤቴ አንዳች የለኝም" አለች።  እርሱም "ሄደሽ ከጐረቤቶችሽ ሁሉ ከሜዳ ባዶ ማድጋዎችን ተዋሺ፤ አታሳንሻቸውም ገብተሽም ከአንቺና ከልጆችሽ በኋላ በሩን ዝጊ፥ ወደ እነዚህም ማድጋዎች ሁሉ ዘይቱን ገልብጪ፤ የሞላውንም ፈቀቅ አድርጊ" አለ።
ነቢየ እግዚአብሔር ኤልሳዕ ያላትን ሁሉ አድርጋ በተአምራት ማድጋዎቹ በዘይት ተሞሉ። " መጥታም ለእግዚአብሔር ሰው ነገረችው፤ እርሱም  "ሄደሽ ዘይቱን ሽጪ ለባለ ዕዳውም ክፈዪ፤ አንቺና ልጆችሽም ከተረፈው ተመገቡ" አላት።  (2ኛ ነገ. 4:7)

ይህ የነቢዩ አብድዩ መልካምነት ከእርሱ አልፎ ለልጆቹ ተርፎ ከጭንቀትና ከባርነት ሊያወጣቸው ችሏል።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ጸሎት ይማረን !!! አሜን
33 viewsbisrat, 16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 19:15:21
30 viewsbisrat, 16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 19:39:16
35 viewsbisrat, 16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-28 19:37:42 #ኅዳር_21_የእመቤታችን_ምሳሌ_ታቦተ_ጽዮን_አክሱም_የደረሰችበት_ዕለት_ነው::

“ጽዮን” ማለት “ጸወን – አምባ – መጠጊያ” ማለት ነው:: አንድም በምሥጢሩ “ማሕደረ አምላክ” ማለት ነው::

ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም: ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል::

ኅዳር 21 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል ነው ብለን በተለየ መልኩ የምናከብርበት ምክንያት፡-

#1. በብሉይ ኪዳን ታቦተ ጽዮን የፈጸመችውን ልዩ ልዩ ገቢረ ተአምራትን ለማሰብ፤

#2. ቀዳማዊ ምኒልክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል የበኲር ልጆች ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛርያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበት ዕለት በመሆኑ፤

#3. በሦስት መቶ ሠላሳ ዓመተ ምሕረት በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ይሁን ተብሎ ዐዋጅ የታወጀበት፤

#4. ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ምሳሌ ራእይ ያየበት፤

#5. ነቢዩ ሕዝቅኤል በተቆለፈችው ቤተ መቅደስ፤

#6. ዕዝራ በቅድስት ሀገር ምሳሌ ራእይ ያየበት፤

#7. አብርሃና አጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተመቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያናትን ስታቃጥል ታቦተ ጸዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሐይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል እናከብራለን፡፡

የወላዲተ አምላክ አማላጅነት የቅዱሳን ተራዳኢነት ከእኛ አይለየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!!!
31 viewsbisrat, 16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-24 18:59:32
38 viewsbisrat, 15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-24 18:59:04 #ዘመን_አይሽሬው_የቅድስት_ኪዳነ_ምህረት_ድንቅ_ተአምር:-

ልመናዋ ክብሯ በእኛ ለዘላለም በእውነት ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ያደረገችው ተአምር ይህ ነው፡-

ስሙ ስምዖን የሚባል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር እጅግ ባለጸጋ ሰው ነበር፡፡ እንደ አብርሃም እንግዶችን እየተቀበለ ድኆችን እየመገበ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡

የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ሰይጣን በዚህ ሥራው ቀናበትና ሊፈትነው በሦስት አረጋዊ ሽማግሌዎች ተመስሎ ‹‹ሥላሴ ነን›› ብሎ እንደ አብርሃም እንደተገለጠለት ሆኖ ተገለጠለት፡፡ ‹‹ሰይጣን ራሱ የብርሃን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣል›› እንዳለ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡፡ 2ኛ ቆሮ 11፡14፡፡ ስምዖንም የዕውነት ሥላሴ መስለውት ተቀበላቸውና ተንከባከባቸው፡፡ የሚበሉት ምግብ ሲያቀርብላቸው እነርሱ ግን ‹‹ምግብ አንበላም፤ የምንጠይቅህን ግን ትፈጽምልን ዘንድ ቃል ግባልን›› አሉት፡፡ ስምዖንም የሚጠይቁትን ለመፈጸም ቃል ገባላቸው፡፡ እነርሱም ቃል ካስገቡት በኋላ ‹‹እንግዲያውስ የምትወደን ከሆነ አንድያ ልጅህን ሰዋልን›› አሉት፡፡ ስምዖን መጀመሪያ ላይ ቢደነግጥም በኋላ ግን ‹‹አብርሃም ልጁን ሊሠዋ አልነበረምን፣ እኔንም ሊፈትኑኝ ይሆናል›› ብሎ ለማረድ ወሰነ፡፡ አንድያ ልጁንም ሊሠዋው በተዘጋጀ ጊዜ ‹‹ተው›› የሚል ድምጽ የሚሰማ መስሎት ቢጠብቅ የሚሰማው ድምጽ ስላጣ አንድያ ልጁን አረደው፡፡ እንዲመገቡም ይዞላቸው ቀረበ፡፡ እነርሱም ‹‹መጀመሪያ አንተ ቅመስልን›› ሲሉት ቀመሰው ነገር ግን ወዲያው እነዚያ ሰዎች ከእርሱ ተሰወሩበት፡፡

ስምዖንም ሰይጣን በፈተና እንደጣለውና እንደተጫወተበትም ሲያውቅ አእምሮውን ሳተ፡፡ ከዚያ በኋላ ምግብ የሚባል ነገር አላሰኘውም፡፡ ይልቁንም የሰው ሥጋ የሚበላ ሆነ እንጂ፡፡ በመጀመሪያ የራሱን ቤተሰቦች አንድ በአንድ በላ፡፡ ቀጥሎም ጎረቤቶቹን፣ ጓደኞቹን ሁሉ በላ፡፡ አንት የውኃ መንቀልና ጦር ብቻ ይዞ ከቤቱ ወጥቶ በመሄድ በመንገድ ላይ ያገኘውን ሰው ሁሉ እየገደለ ይበላ ጀር፡፡ የበላቸውም ሰዎች ቁጥር በአጠቃላይ 78 ሆነ፡፡

ከዚህም በኋላ በመንገድ ሲጓዝ ተቀምጦ የሚለምን በደዌ የታመመ አንድ ደኀ አገኘና ሊበላው ፈለገ፡፡ ነገር ግን ወደ እርሱ በተጠጋ ጊዜ ቁስሉን አይቶ ተጸየፈው፡፡ ደኀውም ሰው ‹‹ስለ እግዚአብሔር ብለህ ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ›› አለው፡፡ ስምዖንም ዝም ብሎት ሄደ፡፡ አሁንም ድኀው ‹‹በውኃ ጥም ልሞት ነውና ስለ ጻድቃን ብለህ ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ›› አለው፡፡ ስምዖንም ዝም ብሎት ሄደ፡፡ ዳግመኛም ለ3ኛ ጊዜ ድኀው ‹‹ስለ አዛኝቷ አምላክን ስለወለደች ስለ ድንግል ማርያም›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ ስምዖን የእመቤታችንን ስም ሲጠራ ሲሰማ ሰውነቱን አንዳች ነገር ወረረው፡፡ ወደ ድኀውም ተመልሶ ‹‹አሁን የጠራከውን ስም እስኪ ድገመው? ስለ ማን አልከኝ?›› አለው፡፡ ድኀውም ‹‹ስለ አዛኝቷ አምላክን ስለወለደች ስለ ድንግል ማርያም›› አለው፡፡ ስምዖንም ‹‹ይኽቺስ ደግ እንደሆነች፣ በምልጃዋም ከሲኦል ነፍሳትን እንደምታወጣ ከህፃንነቴ ጀምሬ ሰምቼው ነበር እናትና አባቴ ይነግሩኝ ነበርና›› አለው፡፡ ድኀውም ‹‹አሁንም በእርሷ ተማጽኜብሃለሁ›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ ስምዖን ‹‹በል ንሣ አምላክን ስለወለደች ስለ ክብርት ድንግል ማርያም እንካ ጠጣ›› ሰጠው፡፡ ከማነሷም የተነሣ ከጥሪኝ ውኃ በቀር ወደ ጉሮሮው አልወረደም፡፡

በለዔ ሰብእም ከዚያች ጊዜ በኋላ አእምሮው ተመለሰለት፡፡ እንዲህም አለ፡- ‹‹በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቼ ስለ ኃጢያቴ አለቅሳለሁ፣ ሥጋዬ ከአጥንቴ እስኪጣበቅ እጾማለሁ፣ ወዮሊኝ ወዮታ አለብኝ›› አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ዋሻ ገብቶ ምግብ ሳይበላ ውኃም ሳይጠጣ 21 ቀን ኖረና በረኀብ ሞተ፡፡

የጨለማ አበጋዞች ሰይጣናትም እያስፈራሩ እጅግ እያስደነገጡ ነፍሱን ወደ ሲኦል ሊወስዷት መጡ፡፡ ክብርት እመቤታችንም ፈጥና በመካከላቸው ተገኘችና አንዳች የሠራት በጎ ነገር እንዳለች መረመረች፡፡ እነርሱም እመቤታችንን ‹‹ከሰማይ በታች ከዚህ ኃጢአት የበለጠ አለን?›› አሏት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ስለስሟ ብሎ ለድኀው ምጽዋት አድርጎ የሰጣትን ያችን ጥርኝ ውኃ በጎኑ አይታ ደስ አላት፡፡

ያችንም ነፍስ በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ከእግዚአብሔር ፊት አደረሷት፡፡ ‹‹ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት የሥቃይ ቦታ ውሰዷት›› የሚል ድምጽ ከዙፋኑ ወጣ፡፡ ክብርት እመቤታችንም ‹‹ልጄ ወዳጄ ይህችን ነፍስ ማርልኝ›› እያለች ሰገደች፡፡ ጌታችንም ‹‹እናቴ ሆይ! ሰባ ስምንት ነፍሳትን የበላ እንዴት ይማራል?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ልጄ ሆይ! የካቲት 16 ቀን በጎለጎታ የገባህልኝ ቃልኪዳንህን አስብ እንጂ፤ ‹ስምሽን የጠራውን፣ መታሰቢያሽን ያደረገውን፣ በስምሽም ቀዝቃ ውኃ ያጠጣውን፣ የተራበ ያለበላውን እምርልሻለው› ብለኸኝ የለምን?›› አለችው፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችንም ‹‹እውነት ነው መሐላዬን አላፈርስም›› አላት፡፡ ወዲያውም መላእክቱን ‹‹እስኪ ሚዛን አምጥታችሁ ያችን ጥርኝ ውኃ በአንድ ሚዛን፣ እነዚህንም 78 ነፍሳት በአንድ ሚዛን አድርጋችሁ በሚዛን አስቀምጡ›› ብሎ አዘዛቸው፡፡

መላእክትም በሚዛን ቢያስቀምጧት ጥርኝ ውኃዋ ከሰባ ስምንቱ ነፍሳት ይበልጥ መዝና ተገኘች፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ‹‹ስለ አንቺ ስል ምሬያታለው›› አለ፡፡ ያችም ነፍስ አምላክን በወለደች በክብርት እመቤታችን አማላጅነት ድና ወደ መንግሥተ ሰማያት ገባች፡፡

የበላኤ ሰብእ እመቤት የብርሃን እናቱ ቅድስት ኪዳነ-ምህረት ወላዲተ አምላክ ከቃልኪዳኗ ረድኤት በረከት ትክፈለን!
37 viewsbisrat, 15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 21:49:50 #ኅዳር_15_ጾመ_ነቢያት_የሚጀመርበት_ዕለት_ነው።

ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ በዓለ ልደት ዋዜማ ድረስ የሚጾም፤ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንደኛው ጾም ነው፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤

ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡

#የጾመ_ነቢያት_ስያሜዎች

#፩ኛ_የነቢያት_ጾም:- ይህ ጾም የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎት በጌታችን መወለድ ፍጻሜ ያገኘበት ወቅት በመኾኑ ‹‹ጾመ ነቢያት›› እየተባለ ይጠራል፡፡

#፪ኛ_የአዳም_ጾም:- ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ ስለ ተፈጸመበትም ‹‹ ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡

#፫ኛ_የስብከት_ጾም:- ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም ‹‹ጾመ ስብከት›› ተብሎ ይጠራል።

#፬ተኛ_የልደት_ጾም:- የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ ‹‹ጾመ ልደት›› በመባል ይታወቃል።

#፭ተኛ_የሐዋርያት_ጾም:- ቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?›› በማለት ነቢያት የጾሙትን ከልደተ ክርሰቶስ በፊት ያለውን ጾም ጾመዋልና ‹‹ጾመ ሐዋርያት›› ይባላል፡፡


#፮ተኛ_ጾመ_ፊልጶስ:- ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡

ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ስለ ተሰወረባቸው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ ሱባዔ ይዘው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በለመኑት ጊዜ እግዚአብሔር ልመናቸውን ተቀብሎ በ፫ኛው ቀን መልሶላቸው ሥጋውን (አስከሬኑን) በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት ‹‹ጾመ ፊልጶስ›› እየተባለ ይጠራል፡፡

#፯ተኛ_የማርያም_ጾም:- ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ካበሠራት በኋላ እመቤታችን ‹‹ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?›› በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማዋለችና ይህ ጾም ‹‹ ጾመ ማርያም›› በመባልም ይታወቃል፡፡

 በአጠቃላይ በዚህ በገና ጾም ነቢያትም ሐዋርያትም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛ ምእመናንም እንደ እነርሱ በረከትን እናገኝ ዘንድ ይህንን ጾም መጾም እንደሚገባን የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሥርዐት ሠርተውልናል፡፡

በዚህም መሠረት የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ዅላችንም በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር_ወወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር!!! አሜን
55 viewsbisrat, 18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 20:32:49
13 viewsbisrat, 17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 20:32:43 #ኅዳር_12_ሊቀ_መላዕክት_ቅዱስ_ሚካኤል_ዱራታኦስና_ቴዎብስታን_የረዳበት_ዕለት_ነው::

ዱራታኦስ እና ቴዎብስታ በተቀደሰ ትዳር ተወስነው: ሕጉን ትዕዛዙን ፈጽመው: ለነዳያን ራርተው: ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለው የሚኖሩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ናቸው::

ይልቁኑም የጌታችንን: የእመቤታችንን እና የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ ያለማስታጐል ያደርጉ ነበር:: ከጊዜ በሁዋላ ግን ሐብት ንብረታቸው አልቆ ተቸገሩ::
ግን የጨነቃቸው መቸገራቸው ሳይሆን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ ሊያቆሙ መሆናቸው ነው:: አማራጭ ሲያጡ ተቀምጠው ተመካከሩ:: የቅዱሱ መልአክ ዝክር ከሚቀር ልብሳቸውን (ያውም የክብር ልብሳቸውን) ሊሸጡ ተስማሙ::

በዚህ መሰረት ቅዱስ ዱራታኦስ ወደ ገበያ ሲሔድ ወዳጁ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወረደለት:: መንገድ ላይም የጦር መኮንን ሃገረ ገዢ መስሎ ተገናኝቶ አጫወተው:: ችግሩን ጠይቆም መፍትሔውን ነገረው:: "እኔ እዋስሃለሁና ለበዓል የሚያስፈልጉህን ነገሮች ሁሉ ገዝተህ አሰናዳ" አለው:: "እኔ ወደ ቤትህ መጥቼ ስለምስተናገድ አንድ አሣ አምጥተህ አቆየኝ:: እኔ ሳልመጣ ግን አትረደው" አለው::

ቅዱስ ዱራታኦስ የተባለውን ሁሉ ፈጽሞ ወደ ቤቱ ሲሔድ ድንቅ ነገርን ተመለከተ:: ሚስቱ ቅድስት ቴዎብስታ በቤቱ መካከል ሁና ቤቱ በበረከት ሞልቷል:: ማሩ: ቅቤው: እሕሉ ሁሉ በየሥፍራው ሞልቷል:: ባልና ሚስቱ ደስ ብሏቸው:: ነዳያንን ሲያበሉ: እንግዳ ሲቀበሉ ዋሉ:: በሁዋላ ያ መኮንን (ቅዱስ ሚካኤል) በቤታቸው መጥቶ ተስተናገደ::

በእርሱ ትዕዛዝ የአሣው ራስ (ሆድ) ሲከፈት በውስጡ 300 ዲናር ወርቅ (እንቁ) ተገኘ:: ቅዱሳኑ ይህን ተመልክተው ሲደነግጡ ቅዱስ ሚካኤል ክንፉን ዘርግቶ ራሱን ገለጸላቸው:: ደንግጠው በግንባራቸው ተደፉ:: እርሱ ግን "በተገኘው ሃብት እዳችሁን ክፈሉ:: ከዚህ በሁዋላ ግን በምድር አትቸገሩም:: በሰማይም ክፍላችሁ ከእኔ ጋር ነው" ብሎ ባርኩዋቸው ወደ ሰማይ ዐረገ:: እነርሱም በሐሴትና በበጐ ምግባር ኖረው ዐርፈዋል:: ለርስቱም በቅተዋል::

ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ በኢዮር: ኃይላት በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል::

ቅዱስ መጽሐፍ ስለ እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17, ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7) ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም "እመቤቴ ሆይ! ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ::

#ለእግዚአብሔር_ክብር_ይሁን_እኛንም_በመልአኩ_አማላጅነት_ይቅር_ይበለን!!! አሜን
14 viewsbisrat, 17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-18 19:34:06
21 viewsbisrat, 16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ