Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-01-06 20:18:26  #የገና_ጨዋታ_ታሪካዊ_አመጣጥ

በምድር ሥርዓት የአንድን ነገር ምስጢር መርምሮ ላገፕ ሰው ሽልማት ይለገሰዋል ከተለያዩ ምሁራንም ምስጋና ይቸረዋል የሰው ልጅ የቱንም ያህል ቢጠበብ በአዕምሮ ቢጎለምስም እግዚአብሔር ያልተጨመረበት እውቀት እግዚአብሔር የሌለበት ጥበብ ነፋስን እደመከተል ነው ምክኒያቱም ? <<የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው>> (ምሳ1፥7) ይላልና

<<ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤  እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ፥ ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ።  ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።>> (ገላ. 4፤4-6)

ጥበብን ከመንፈሳዊነት ጋር ያጣመሩ ሃይማኖት እና ምግባር የተማሩ ከሩቅ ምስራቅ ለጌታን ሊሰግዱ ወርቅ እጣን ከርቤ ሊገብሩ የጥበብ ሰዎች በፀፍፀፍ ሰማ /በሰሌዳ ሰማይ/ኮከብ እየመራቸው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። (ማቴ. 2:1-2)
ለሶስቱ የጥበብ ሰዎች 10ሺ 10ሺ 10ሺ ሰራዊት አላቸው በጥቅሉ ለሶስቱ ነገስታት 30 ሺ ስራዊት ነበራቸው።
ይህንን አሰደንጋጭ እና ድንገተኛ ነገር የሰማው ሔሮድስ ሰብአሰገልን በስውር ጠርቶ << ሂዱ፥ ስለ ሕፃኑ በጥንቃቄ መርምሩ፤ ባገኛችሁትም ጊዜ እኔ ደግሞ መጥቼ እንድሰግድለት ንገሩኝ>> አላቸው።
(ማቴ. 2:8) ሰብአሰገልም ይህንን በእሽታ ከተቀበሉት በኋላ ጉዟቸውን ቀጠሉ።

ሄሮድስ ግን ሰብአሰገልን ስላላመናቸው በሰራዊታቸው መካከል የራሱን የምስጢር ሰላይ ሩር የተባለ በድብቅ ቀላቀለባቸው ።

<< በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ። እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ። መልአኩም እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ>> አላቸው።
(ሉቃ. 2:8-12)

ከምስራቅ ታይቶ ሰብአሰገልን ይመራቸው የነበረው ኮከብ ድንገት ተሰወራቸው የሚሄዱበት ጠፍቷቸው ግራ ተጋቡ ኮከቡም እስኪግለፅ እህል አንቀምስም ብለው ሱባኤ ያዙ።

እርስ በእርሳቸውም በመካከላችን እኛ የማናውቀው ሰው አለ ስለዚህ መርምሩ ተባባሉ እርስ በእርሳቸው ሲመራመሩም ሄሮድስ በስውር የላከውም ሰላይ ሩርን አገኙት  የሩርንም አንገቱን ቆርጠው ነገስታቱ ወደዛ ወደዚህ እያመላለሱ ተጫወቱበት ,,,የገና ጨዋታ <<ሩር>> የሚል ስያሜ ያገኘው ከዚህ የተነሳ ነው።

ከዚህ በኋላ ያ ደብዛው የጠፍው ኮከብ ተገለፀላቸው ሰባሰገልም እህል ቀምሰው ወደቤተልሄም ገሰገሱ ሕጻኑንም በእናቱ እቅፍ በከብቶች ግርግም ውስጥ አገኙት ። ሳጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ እጣን ከርቤ ገበሩለት ወርቁን ለመንግስቱ እጣኑን ለክህነቱ ከርቤውን ለክቡር ሞቱ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ገበሩለት ።

እመቤታችን ድንግል ማርያምም ለሰብአሰገል የገብስ እጀራ ስጥታቸው አርባ ቀን ድረስ ሲጓዙ ያንን እየበሉ ተጉዘዋል ከሀገራቸው ሲደርሱም <<ይህንን የተቀደሰ ምግብ ወደ ከተማ ይዘን አንገባም>> ብለው ከከተማው ውጭ ቀብረውት ገቡ። የከተማው ሕዝብ የተወለደውን የአይሁድ ንጉስ አገኛችሁት ? ብለው ጠየቋቸው አዎ አግኝተን ሰግደንለት መጣን አሉ ሕዝቡም ምን ምልክት አላችሁ አሉ ? እናቱ የስጠችንን የገብስ እጀራ እየበላን መጣን የተቀደሰ ነውና ወደ ከተማ እዳናስገባ ከከተማ ዳር ቅብረነዋል ሁለት አመት የተጓዝነውን መንገድ በአርባ ቀን ጨርስንዋል>> አሏቸው ። ህዝቡም ከከተማው ዳር የተቀበረውን የተቀደሰ እንጀራ ለማየት ወጣ እጀራውም እንደ እሳት ሲነድ አይተው አምነዋል።

ብርሃነ ልደቱ በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር !!! አሜን
106 viewsbisrat, 17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 20:30:12
93 viewsbisrat, 17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 20:29:43 #ታህሳስ_29_የዓለም_ሁሉ_ጌታ_መድኃኔዓለም_ተወለደ።

በጌታችን መወለድ ዓለም ሁሉ ከነበረበት የጨለማ ሕይወት ወጥቷል፤ አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በገነት ሲኖሩ እግዚአብሔር ‹‹አትብሉ!›› ብሎ ያዘዛቸወውን እፀ በለስ በልተው ከገነት ወጡ፤ ጠላታችን ሰይጣንም መከራ ያደርስባቸው ጀመር፤ አዳምና ሔዋን አለቀሱ፤ ‹‹ማረን፣ ይቅር በለን›› ብለው እግዚአብሔርን ለመኑት፤ እግዚአበብሔርም አዘነላቸው፤ ከወጡበት ገነት ሊመልሳቸው ቃል ኪዳን ገባላችው፤ ከዚያም ለአዳም ‹‹ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድናችኋለው ..›› ብሎ ተሰፋ ሰጠው፤ የሰጠው የተስፋ ቃልም መፈጸሚያው ቀኑ ሲደርስ ከእመቤታችን ከቅድስት ደንግል ማርያም ተወለደልንና አዳነን፤ ከጠላታችን ዲያቢሎስም እስራት ነጻ አደረገን፤ ይህ እንዴትና መቼ ሆነ ቢሉ:-

የዛሬ ሁለት ሺ ዓመት ገደማ ነው፡፡ በኢየሩሳሌም ሀገር ንጉሡ ሄሮድስ ሕዝቡን ሁሉ ቤተልሄም ወደምትባል ከተማ ጠራቸው፡፡ እመቤታችንም በዚያ ጊዜ የአሥራ አምስት/15/ ዓመት ልጅ ሆኖ በሚጠብቃት በአረጋዊው /በሽማግሌው/ ዮሴፍ ቤት ትኖር ነበር፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስን ፀንሳ ልትወልድ ደርሳ ሳለ ወደ ቤተልሄም ከተማ ከአረጋዊው ጠባቂዋ ዮሴፍና ከቅድስት ሰሎሜ ጋር ሄደች፡፡

በዚያ ሲደርሱ እናታችን ማርያም ቅድስት ሰሎሜና አረጋዊው ዮሴፍ ማደሪያ ፈልገው በየቤቱ እየሄዱ “የእግዚአብሔር እንግዶች ነን ማደሪያ ስጡን፣ እባካችሁ አሳድሩን…” ብለው ቢጠይቋቸው ሁሉም “ቦታ የለንም፣ አናሳድርም፣ አናስገባም ሂዱ፡፡” እያሉ መለሷቸው፡፡ በጣም መሽቶ ስለነበረ ጨለማው ያስፈራ ነበረ፣ ብርዱ ደግሞ በጣም ከባድ ነበረ፡፡ ማደሪያ አጥተው የት እንሂድ እያሉ ሲያስቡ በድንገት አረጋዊ ዮሴፍ “ኑ ተከተሉኝ” ብሎ በመንደሩ ውስጥ ወዳለ አንድ የከብቶች ማደሪያ ቤት ወሰዳቸው፡፡ ከከብቶቹ ቤት ሲደርሱ በዚያ አህዮች፣ በሬዎች፣ በጎች፣…. ብዙ እንስሳት ተኝተው አገኙዋቸው፡፡ የበረቱ ሽታ በጣም ያስቸግር ነበረ፡፡ ነገር ግን ማደሪያ ስላልነበረ በዚያ ሊያድሩ ተስማሙ፡፡ ወደ በረቱ ሲገቡ እንስሶቹ ከተኙበት ተነሥተው በደስታ እየዘለሉ ተቀበሏቸው፡፡ በዚያም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስን ወለደችው፡፡ ይህም ታላቅ ሕፃን የሁላችንም አምላክ ነው፡፡ ወዲያውኑ የከብቶቹ ቤት በታላቅ ብርሃን ተሞላ፤ በምድር ያለው ውሃ ማርና ወተት ደንጋዮችም ትኩስ ኅብስት ሆኑ፡፡

በዚያ ሀገር ይኖሩ የነበሩ እረኞችም ሌሊት ከብቶቻቸውን ይጠብቁ ነበር፤ የእግዚአብሔር መልአክም በእረኞቹ አጠገብ ቆመ፤ የእግዚአብሔርም ብርሃን በዙሪያቸው በራ፤ በጣምም ፈሩ፡፡ መልአኩም እንዲህ አላቸው ‹‹እነሆ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምስራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ‹‹እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት የሆነ ተወልዶላችኋል፡፡ ይኸውም ጌታ እና እግዚአብሔር የሆነ መድኃኒታችን ኢያሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እናንተም ባገኛችሁት ጊዜ ምልክቱ እንዲህ ነው፡፡ ሕፃን በጨርቅ ተጠቅልሎ በበረት ውስጥ ተኝቶ ታገኙታላችሁ ድንገትም ከዚያ መልአክ ጋር ብዙ የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ እነዚህ እረኞች እርስ በርሳቸው ‹እስከ ቤተልሔም እንሂድ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን ነገር እንወቅ አሉ፡፡ ፈጥነውም ሄዱ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን አገኙአቸው፡፡ ሕፃኑንም በበረት ውስጥ አገኙት፡፡ እረኞቹም የነገሩአቸውን በአዩት ጊዜ በጣም ተደነቀው በእመቤታችን ፊት ከቅዱሳን መላእክት ጋር እግዚአብሔርን እያመሰገኑ‹‹በሰማይ ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን በምድርም ለሰው ልጆች በጎፈቃድ ሆነ›› ብለው እያመሰገኑና እያከበሩ ወደመጡበት ተመለሱ፡፡

ከሩቅ ምስራቅ የመጡ ነገሥታትም ለተወለደው ለጌታችን ሰገዱለት፤ ያመጡትንም ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ ..ሌሎችንም ሥጦታዎች አበረከቱለት፡፡

አምላካችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመወለዱ ለዓለም ሁሉ ሰላም ሆነ፤ እኛም ታዲያ አባቶቻችን ባቆዩልን ሥርዓት መሠረት ነቢያት የጾሙትን ጾም በመጾም የጌታችንን የልደት በዓል እንቀበላለን፡፡ ታዲያ በዓሉን ስናከብር ካለችን ላይ ቀንሰን የተቸገሩ ወገኖቻችንን እንረዳለን፤ ያለንን እናካፍላለን፤ በጌታችን ልደት ጊዜ ቅዱሳን መላእክትና የሰው ልጆች አብረው ደስ ብሏቸው አመስግነዋል፡፡ ስለዚህ እኛም ይህንን በዓል ስናከብር የተጣላን ታርቀን የበደልን ክሰን የቀማን መልሰን ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን በፍቅር በሰላም ሆነን ማክበር አለብን፤ ምክንያቱም የጌታችን ልደት እኛ ይቅርታ ያገኘንበት ጠላታችን ዲያቢሎስ ያፈረበት ቀን ነውና፡፡

እንግዲህ ነቢዩ ክቡር ዳዊት በትንቢቱ ‹‹..እነሆ በኤፍራታ ሰማነው በዱር ውስጥም አገኘነው…›› ብሎ እንደተናገረ እኛን ከወደቅንበት ሊያነሣን በትሕትና በቤተልሔም በኤፍራታ እንደተወለደንል እኛም እርሱን አርአያ አድርገን በሕይወታችን ምግባር ትሩፋት ሰርተን በሃይማኖታችን ጸንተን መገኘት ይጠበቅብናል።

አምላካችን ፈጣሪያችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከበዓለ ልደቱ ረድኤት በረከቱን ይክፈለን አሜን!!!

ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!!!
173 viewsbisrat, 17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 19:11:58 #የገና_ዛፍ_ታሪክና_አመጣጡ

የገናን ዛፍ ከየት እንደመጣ ምንጩን ስናጤነው ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲህ ይነግሩናል:-

የዞራስተርን የሁለት አማልክት ዕምነት
በሚያምኑት ምዕራባውያን ዘንድ ክፉውና ደጉ የተባሉ ሁለት አማልክቶች አሉ። እንደ ዕምነቱ አስተሳሰብ ከሆነ እዚህ ምድር ላይ የሆነው እየሆነው ያለውና የሚሆነውም ማንኛውም ነገር በሙሉ የሚከናወነው በእነዚህ በሁለቱ አማልክቶች ፉክክር ነው። ክፉው አምላክ ከሰለጠነ /የበላይ ከሆነ/ በምድር ላይ ክፉ የሆኑ ብዙ ነገሮች ይከሰታሉ። በተቃራኒው ደግሞ ደጉ አምላክ ከሰለጠነ በጎ ነገሮች ይከሰታሉ ማለት ነው።
ምዕራባውያኑ ታዲያ ደጉን አምላካቸውን ማለትም ጣዖታቸውን ሳተርን ብለው ይጠሩታል። በምዕራቡ ዓለም የክረምቱ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነው። ዛፎች ሁሉ ቅጠሎቻቸው ይረግፋሉ። ልምላሜ አይታይባቸውም። ፅድ ግን በተፈጥሮው ይህን አስቸጋሪ ወቅት ተቋቁሞ የማለፍ ኃይል አለው። በመሆኑም ፅድ ክፉውን ዘመን /ክረምቱን/ ተቋቁሞ መልካሙ ዘመናቸው እስኪመጣላቸው ድረስ በልምላሜ ይቆይላቸዋል። ይህም ሳተርን /ደጉ አምላካቸው/ ከክፉው አምላክ ለመሸሸግ በፅድ ውስጥ ተደብቆ ይኖራል ብለው ያመናሉ ምዕራባውያኑ። እናም ብራ ሲሆን /በእኛ መስከረም ጠባ እንደምንለው ነው/ የደጉን አምላክ ‹‹የእንኳን ደህና መጣህ›› በዓልን በድምቀት ያከብራሉ። ምስጋና ለፅዱ ይሁንና ደጉ አምላካቸውን ደብቆ ስላቆየላቸው ባለውለታ ስለሆነ የደጉን አምላክ የእንኳን ደህና መጣህ በዓል ሲያከብሩ ታዲያ ፅድን ለበዓላቸው ማድመቂያነት ይጠቀሙበት ነበር። ይኸው ትውፊታቸው ዛሬም ድረስ አለ።

በአጭሩ ከጥንት ጀምሮ እነርሱ ይኽን በዓል የሚያከብሩት ሳተርን ለተባለው ጣዖት /ደጉ አምላክ/ ያደርጉት የነበረው ሥርዓት ነው። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ታላቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትናን በአዋጅ ካስፋፋበት ጊዜ ጀምሮ በውጭው ዓለም ጥንት የነበሩ ብዙ ጣዖታዊ በዓላት ክርስቲያናዊ በዓል ሆነው አሁንም ድረስ በብዙ ሀገራት እየተከበሩ ይገኛሉ። /ነገር ግን ልደትንና ትንሣኤን ጨምሮ ሌሎችም በዓላት ቢሆኑ ሥርዓታቸውን በጠበቁ መልኩ የሚከበርባቸው አንዳንድ ሀገራት አሉ።/

በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ይኸው እስከዛሬ እኛም ይኽንኑ የባዕድና የጣኦት አምልኮ በዓላቸውን በእነሱው ልማድ መሠረት የፅድ የገና ዛፍ እየሠራን ስናከብርላቸው ኖረናል። አሁንም ትንሽ ቀን ብቻ የቀረውን የገናን በዓል በእንዲሁ ዓይነት ሁኔታ ለማክበር ሽር ጉድ እያልን ነው። አባቶቻችን ሲናገሩ ‹‹እግዚአብሔር ዓለሙን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው ሆኖ ዓለሙን ያዳነበት ጥበቡ እጅግ ረቂቅና ጥልቅ ነው›› ይላሉ። እንዴት ደስ የሚል አገላለፅ ነው!!! ታዲያ ምን ዋጋ አለው? አለመታደል ሆኖ ይሁን አሊያም አለማወቃችን ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋን ይግባውና እጅግ ድንቅ የሆነውን የጌታችንን የአምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ከእንደዚህ ዓይነቱ ምዕራባዊ የጣዖት በዓል ጋር ቀላቅለን እናከብራለን።

ይህ እጅግ አሳዘኝ ነገር ነው በእውነት!
ምዕራባውያን ስለ ዕምነት ጉዳይ እውነት የሆነውን ነገር ፍለጋ ፊታቸውን ወደ እኛ ባዞሩበት ወቅት እኛ ደግሞ እውነተኛውን ማንነታችንን ባንጥልና የአጉል ባህል ተገዢዎች ባንሆን ብሎም በአምልኮ ጣኦታቸው ተሳታፊዎች ባንሆን መልካም ነው። መልካም ነው ብቻም ሳይሆን መንፈሳዊና ሞራላዊ ግዴታዎችም አሉብን።

የአማኑኤልን የልደት በዓል የገናን ዛፍ በመጠቀም ከነጮቹ ባዕድና ጣኦት አምልኮ ጋር አንቀላቅለው፡፡ ልደቱን ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚገባው አድርጋ ታከብረዋለችና እኛም ልጆቿ እንደሚገባው መጠን ልደቱን እናክብር፡፡ የገና ዛፍ የባዕድ አምልኮ መገለጫ ነው፡፡

ማህቶተ ቤተክርስቲያን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ምንድን ነበር ያለው! ‹‹ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው? የእግዚአብሔርን ታቦት በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማነው? 2ኛ ቆሮ 6፡14-16፡፡ “በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ” 2ኛ ቆሮ 13፡5፡፡

የአባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በሃይማኖታችን ያፅናን አሜን።
30 viewsbisrat, 16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 19:11:52
22 viewsbisrat, 16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 19:03:59 #ታህሳስ_24_ልደቱ_ለጻድቅ_ተክለ_ሃይማኖት

“ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል፡፡” ማቴ.10÷41

ጻድቁ ተክለሃይማኖት እግዚአብሔርን ከሚወዱ እና ከሚያከብሩ ከአባታቸው ጸጋዘአብ እና ከእናታቸው እግዚእ ሐረያ ታኅሣሥ 24 ቀን ተወለዱ፡፡

ጸጋዘአብ ማለት የአብ ጸጋ ማለት ሲሆን እግዚእ ሐረያ ማለት ደግሞ በጌታ የተመረጠች ማለት ነው፡፡ ጸጋ ዘአብ እና እግዚአ ሐረያ እግዚአብሔርን በፍጹም ልባቸው የሚያምኑ፣ በተለያየ ሕመም የሚሰቃዩ እና ችግረኞችን የሚረዱ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ በተለይ ለእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ሚካኤል የተለየ ፍቅር ስለነበራቸው በየወሩ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት በመታመን የመልአኩን በዓል ድሆችን በመንከባከብ ያከብሩ ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ቅዱስ ሚካኤል በሕልም ተገልጾ እግዚአብሔር የተባረከ ልጅ እንደሚሰጣቸው ነገራቸው፡፡ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ወንድ ልጅ ፍሥሐጽዮን ብለው ጠሩት፡፡ ፍሥሐጽዮን ማለት የጽዮን ደስታ ማለት ነው፡፡ ሕፃኑ ፍሥሐጽዮን መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ በሶስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐድ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብሎ አመሰገነ፡፡ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለነበር ፍሥሐጽዮን በልጅነቱ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፡፡

በአንድ ወቅት ረሃብ ነበር ቤተሰቦቹ በዚህ ምክንያት የቅዱስ ሚካኤልን ዝክር እንዳያቋርጡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ዱቄትና ዘይት በማብዛት ቤተሰቦቹ ዝክሩን ያለምንም ችጋር እንዲዘክሩ አድርጓል፡፡ ዝክር ማለት በእግዚአብሔር፣ በቅዱሳን እና በመላእክት ስም የሚደረግ መታሰቢያ ነው፡፡ ፍሥሐጽዮን እግዚአብሔርን እያገለገለ አደገ፡፡

በዐሥራ አምስት ዓመቱ ከአቡነ ቄርሎስ ሁለተኛ ዲቁና ተቀበለ፡፡ ወደ ቤት ሲመለስ ቤተሰቦቹ አንዲት ሴት እንዲያገባት እንዳጩለት ነገሩት፡፡ ነገር ግን ፍሥሐጽዮን ይህን ጥያቄ አልተቀበለውም ነበር፡፡ አንድ ቀን ፍሥሐጽዮን ከጓደኞቹ ጋር ለአደን እንደወጣ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ከዚህ በኋላ ያለውን ቀሪ ዘመኑን የሰዎችን ነፍስ በማዳን እግዚአብሔርን እንዲያገለግል መመረጡን ነገረው፡፡ መልአኩ የፍስሐጽዮንን ስም ተክለሃይማኖት (የሃይማኖት ዛፍ (ተክል)) ብሎ ለወጠው፡፡ ከዚህ በኋላ ተክለሃይማኖት ወደቤቱ ተመልሶ ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን እና ለድሆች ሰጥቶ ወደ ገዳም ሄደ፡፡

በገዳም እያገለገለ እና እየተማረ የቅድስና ማዕርግን ተቀበለ፡፡ በትጋት ወንጌልን በመስበኩ ብዙ ሰዎችን ወደ ክርስትና ተመለሱ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለብዙ ዓመታት በአገልግሎት ከቆየ በኋላ አንድ ቀን በገመድ ሲወርድ ገመድ ተበጥሶ ሲጸልይ ክንፍ ተሰጠው፡፡

ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ሃያ ዘጠኝ ዓመታትን ያሳለፈው ደብረ አሰቦ በተባለ ቦታ ቆሞ በመጸለይ ነበር፡፡ ለረጅም ሰዓታት በመቆም ይጸልይ ስለነበረ እግሩ ሊቆረጥ ችሏል፡፡ አንድ እገሩ ቢቆረጥም ጸሎቱን እና ትጋቱን አላቋረጠም ነበር፡፡ በአንድ እግሩ ለሰባት አመታት ጸልዮአል፡፡

ጻድቁ ተክለሃይማኖት ዘመኑን ወንጌልን ለማያምኑ ሰዎች በመስበክ ብዙ ኢ-አማንያንን ክርስትናን እንዲቀበሉ አድርጓል፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እንዲሰፋ እና ገዳማዊ ሕይወት እንዲጠነክር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ሲሆን በዘጠና ዘጠኝ ዓመቱ ነሐሴ ሃያ አራት ቀን በክብር አርፏል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በኢትዮጵያዊው ጻድቅ ጸሎት ይማረን!!!
29 viewsbisrat, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 08:57:26
48 viewsbisrat, 05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 08:57:07 #ታህሳስ_21_ቅዱስ_በርናባስ_ሰማዕትነት_የተቀበለበት_ዕለት_ነው።

በርናባስ ማለት የስሙ ትርጉም ወልደ ፍስሐ የደስታ ልጅ ማለት ነው የተወለደው ቆጵሮስ በሚባል አገር ነው።

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአረገ በኋላ ሀብት ንብረቱን በመሸጥ ለሐዋርያት ሰጥቶአቸዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ወደ ክርስትና ዓለም ሲጠራ ከሐዋርያት ጋር ያስተዋወቀው እርሱ ነው፡፡ ከቅዱስ ጳውሎስም ጋር በመሆን በልጥራን ያስተምሩ በነበረበት ወቅት አንድ ሕመምተኛ ፈወሱ፡፡ በዚህ ጊዜ የአካባቢው ነዋሪ አማልክት በሰው አምሳል ወደ እኛ ወረዱ ኑ መስዋእት እንሠዋላቸው ብለው ላም ይጎትቱ ጀመር፡፡ እነ ቅዱስ በርናባስም እኛ እንደ እናንተ የምንሞት ሰዎች ነን ተው ብለው ከለከሏቸው የዚያ ሀገር ሰዎችም ስማቸውን በአማልክቶቻቸው ስም ቀይረው ቅዱስ በርናባስን ድያ ጳውሎስን ሄርሜን ብለው ሰይመዋቸዋል፡፡

ቅዱስ በርናባስም እንዲህ ከሀገር ሀገር እየተዘዋወረ ሲያስተምር ኖሮ ሕዝበ ክርስቲያኑን ለመጎብኘት ቅዱስ ማርቆስን አስከትሎ ወደ ቆጵሮስ በመመለስ ማስተማር ጀመረ፡፡ ከቆጵሮስ በተጨማሪም ሶርያንና ዲልቅያን ጨምሮ ሲያስተምር አሕዛብ /የማያምኑ/ ጠልተው፤ ተመቅኝተው ታህሳስ 21 ቀን በድንጋይ በመውገር ነፍሱን ከሥጋው ከለዩ በኋላ ከእሳት ጣሉት፡፡ እሳቱ ግን ሥጋውን ሳያቃጥለው ቅዱስ ማርቆስ አንሥቶ ቀብሮታል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው ጸሎት ይማረን። አሜን !!!
52 viewsbisrat, 05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 21:02:03
30 viewsbisrat, 18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 21:01:44 #ታህሳስ_20_ዕረፍቱ_ለነቢዩ_ሐጌ

ሐጌ ማለት በዓል፣ ደስታ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜ ሕዝቡ ከምርኮ የሚመለሱ ስለኾነ ይኽን ደስታ የሚያስረዳ ነው፡፡

#ነቢዩ_ሐጌ_ማነው?
ነቢዩ ሐጌ ከ ፲፪ [12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ሲሆን የተወለደው በምርኮ በባቢሎን ሲኾን ትንቢቱን ሲናገር የ፸፭ [75 ዓመት ሽማግሌ ነበር፡፡ የእስራኤል ቅሪቶች ወደ ኢየሩሳሌም በዘሩባቤል አማካኝነት ሲመለሱ ነቢዩ ሐጌም ከተመለሱት ጋር አንዱ ነበር፡፡

በ፭፻፴፰ [538 ቅ.ል.ክ. ላይ የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ አንድ አዋጅ አስነግሮ ነበር፡፡ አዋጁም አይሁድ ወደ አገራቸው እንዲመለሱና ቤተ መቅደሱን እንዲሠሩ የሚፈቅድ ነበር /ዕዝራ ፩፡፩-፲፩/፡፡ በዚኽም መሠረት የቤተ መቅደሱን ሥራ በ፭፻፴፮ [536 ላይ የቤተ መቅደሱን ሥራ ዠምረዋል፡፡ ነገር ግን አይሁድ ወደ አገራቸው ሲገቡ አገራቸው ባድማ ኾና ስለነበር፣ የዘር ፍሬ በአገሩ ስላልነበረ፣ እንዲኹም በሌሎች ችግሮች ምክንያት ቤተ መቅደሱን መሥራት ትተው ወደየግላቸው ተግባር ተሰማርተው ነበር፡፡

በመኾኑም መንፈሳዊ ሕይወታቸው ዝሎ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ነቢዩ ሐጌንና ነቢዩ ዘካርያስን የላከበት ዋና ምክንያትም የተዠመረውን ቤተ መቅደስ እንዲያጠናቅቁት ለማሳሰብ ነበር፡፡ ነቢዩ ሐጌ በሚያገለግልበት ወራት የነበረው ንጉሥ ዘሩባቤል ሲኾን፤ በዚያ ሰዓት የነበረው ሊቀ ካህናት ደግሞ ኢያሱ ይባላል /፩፡፩/፡፡

#ትንቢተ_ሐጌ
በብሉይ ኪዳን በመጨረሻ የምናገኛቸው ሦስቱን መጻሕፍት ማለትም ትንቢተ ሐጌ፣ ትንቢተ ዘካርያስና ትንቢተ ሚልክያስ ከምርኮ በኋላ ስላለው ጊዜ እንዲኹም አይሁድ ከምርኮ እንዴት ወደ አገራቸው እንደተመለሱ የሚያስረዱ ናቸው፡፡ በዚያ አንጻር ግን ደቂቀ አዳም ከዲያብሎስ ምርኮ እንደምን ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሱ የሚያስረዱ ናቸው፡፡

ነቢዩ ሐጌ በእግዚአብሔር ሰዓት የእግዚአብሔር ሰው ኾኖ የተገኘ ነቢይ ነው፡፡ አገልግሎቱን በ፭፻፳ [520 ቅ.ል.ክ. ላይ ሲዠምር ጠንካራና ፬ ተከታታይ ስብከቶችን በመስጠት ነበር፡፡

ለሕዝቡ የቤተ መቅደሱ ሥራ እንደተቋረጠ ነገራቸው፤ ሕዝቡ ከቤተ እግዚአብሔር ይልቅ የራሳቸውን ቤት በመሸላለም እንደተሳቡ ገለጠላቸው፡፡ አራቱ ስብከቶቹ በአጭሩ እንደሚከተለው የቀረቡ ናቸው፡-

1. የቤተ መቅደሱን ሥራ እንዲያጠናቅቁት አሳሰባቸው /ምዕ. ፩/፡፡

2. የኹለተኛው ቤተ መቅደስ ክብር እንዴት እንደኾነ አስረዳቸው /፪፡፩-፱/፡፡

3. የመታዘዛቸው ውጤት የኾነ በረከትን እንደሚባረኩ ነገራቸው /፪፡፲-፲፱/፡፡

4. በመታዘዛቸው ምክንያት ሊመጣ ያለው በረከት እንዴት እንደኾነ አስታወቃቸው /፪፡፳- ፳፫[23/፡፡

#እኛስ_ከዚኽ_ምን_እንማራለን?

መጽሐፉን በጥንቃቄ አንብበነው ከኾነ ቃሉ መጣ የሚለው “በነቢዩ በሐጌ እጅ” ነው የሚለው /፩፡፩፣ ፪፡፩፣ ፪፡፲/፡፡ የእግዚአብሔር ቃል የሚመጣው በነቢያት አፍ ነው፤ እዚኽ ግን የተገለጠው በነቢዩ እጅ ነው፡፡ ምን ለማለት ነው? ጄሮም የተባለ የጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን ሊቅ እንዲኽ ይላል፡- “እጆቻችንን ለመልካም ሥራ ስናነሣ ክርስቶስም በኹለንተናችን ላይ ይነግሣል፤ ዲያብሎስን ከእኛ ያርቅልናል፡፡ እጅ ሲባል መልካም ሥራን የሚያመለክት ነው፡፡ … እግዚአብሔር ወደ ሕይወታችን የሚመጣው ስለ ተናገርን አይደለም፤ መልካም ሥራን ስንሠራ እንጂ፡፡”

አይሁድ ቤተ መቅደሱን ላለመሥራት ሲያመካኙ የነበረው “ኢኮነ ጊዜሁ - ጊዜው ገና ነው” በማለት ነበር፡፡ ተወዳጆች ሆይ! ብዙዎቻችን በዚኽ መንፈስ የተያዝንበት ዘመን ቢኖር አኹን፡፡ “ጊዜው ገና ነው፤ ቤተ መቅደሱን የምሠራበት ጊዜ አይደለም፤ ገና ወጣት ስለኾንኩ አኹን ወደ እግዚአብሔር የምቀርበብበት ዘመን አይደለም” እያልን እናመካኛለንና፡፡ ነገ በሕይወት ለመኖራችን ግን እርግጠኞች አይደለንም፡፡ እንኪያስ ሰባኪው እንዳለው የጭንቅ ቀን ሳይመጣ፣ በጕብዝናችን ወራት፣ አፈርም (ሥጋችን) ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ ፈጣሪያችንን እናስብ እንጂ በማመካኘት ጊዜአችንን አናጥፋ /መክ.፲፪፡ ፩፣፯/፡፡

በተራራው ስብከቱ ላይ ጌታ፡- “አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይኽም ኹሉ ይጨመርላችኋል” እንዳለን / ማቴ.፮፡፴፫/ በሕይወታችን ላይ እግዚአብሔር የማናስቀድም ከኾነ ግን ብዙ ብንዘራም የምናስገባው ጥቂት ነው፤ ብንበላም አንጠግብም፤ ብንጠጣም አንረካም፤ ብንለብስም አይሞቀንም፤ ደመወዛችንን ብንቀበልም በቀዳዳ ኪስ እንደማስቀመጥ ነው /ሐጌ.፩፡፮/፡፡ አዝመራውን በእርሻው ሳለ ባየነው ጊዜ ብዙ ቢመስለንም ወደ ቤታችን ሲገባ በረከት የለውም፤ ሰማይ ዝናም ለዘር ጠል ለመከር ይነሣል (ይከለክላል)፤ ምድር የዘራንባትን አታበቅልም፤ የተከልንባትን አታጸድቅም፡፡ በአጭር ቃል በረከት ከእኛ ይርቃል /ሐጌ.፩፡፱-፲፩/፡፡

በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን ተብለን ተጠርተን ሳለ፣ በጥምቀት ከማይጠፋ ዘር ተቈጥረን ሳለ ምድራዊ ቤትን (ፈቃደ ሥጋን) ለመሥራት አማናዊው መቅደሳችንን (ፈቃደ ነፍሳችንን) የምንረሳ ከኾነ በዚኽ ምድር ከእኛ የባሰ ጐስቋላ ሰው የለም /ሐጌ.፩፡፲-፲፩/፡፡

ቤተ መቅደሱን (ፈቃደ ነፍሳችንን) የምንሠራ ከኾነ ግን እግዚአብሔር በረድኤቱ ከእኛ ጋር ይኾናል፤ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ላይ ትበዛለች፡፡ “ቤተ እግዚአብሔርን ከሠራችሁበት ቀን ዠምሮ እኽሉን ወይኑን በአውድማ ትርፍርፍ ብሎ ታዩታላችሁ፤ በለሱን ሮማኑን ዘይቱን የሚያፈራውን እንጨት ኹሉ ከዛሬ ዠምሮ አበረክታለኹ” ሲል ይኽን ያመለክታል /ሐጌ.፪፡ ፳/፡፡

ይኽን እንድናደርግ ሰውን በመውደዱ ሰው የኾነው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን አሜን!!!
29 viewsbisrat, 18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ