Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-12-12 02:53:34
8 viewsbisrat, 23:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 02:53:24 #ታህሳስ_3_እመቤታችን_ቤተመቅደስ_የገባችበት_ዕለት_ነው።

ኢያቄምና ሐና የሚባሉ በተቀደሰ ትዳር የሚኖሩ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፡፡ ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚወዱ ደግ ሰዎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን ሐና ልጅ መውለድ አትችልም ነበር፡፡ ልጅም ስለሌላቸው በጣም አዝነው ይኖሩ ነበር፡፡

ሁልጊዜ ወደ ቤተ እግዚአብሔር እየሄዱ ልጅ እንዲሰጣቸው ልመና ያቀርቡ ነበር፡፡ ለእግዚአብሔርም ልጅ ከሰጠኸን ለአንተ ብጽአት (ስጦታ) አድርገን እንሰጣለን ብለው ተሳሉ፡፡ እግዚአብሔርም ልጅ ሰጣቸው፡፡ ሐናም በግንቦት አንድ ቀን ከፀሐይ የምታበራ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ሕፃኗንም ማርያም ብለው ስም አወጡላት፡፡
ልጃቸው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በንጽህና ሲያሳድጉ 3 ዓመት ከሆናት በኋላ በተሳሉት ስእለት መሠረት ወደ ቤተ እግዚአብሔር መውሰድ እንዳለባቸው ተነጋገሩ፡፡ ለመንገድ የሚሆን ስንቅና ለቤተ እግዚአብሔር የሚሆን ስጦታ ሁሉ አዘጋጁ፡፡ ከዚያም ልጃቸውን ድንግል ማርያምን ይዘው ወደ ቤተመቅደስ ሄዱ፡፡በቤተ መቅደስ የካህናት አለቃ የነበረው ካህኑ ዘካርያስ ተቀበላቸው፡፡

ሐና እና ኢያቄም ለእግዚአብሔር የገቡትን ቃል ፤ የተደረገላቸውንም ድንቅ ተአምር ነገሩት፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ለእግዚአብሔር የገቡትን ቃል ባለመርሳታቸው እጅግ ተደሰተ፡፡ ነገር ግን ወዲያው አንድ ነገር አሳሰበው፡፡ምን መሰላችሁ ልጆች እመቤታችንን በዚያ በቤተመቅደስ ስትኖር ማን ይመግባታል ብሎ ነበር የተጨነቀው፡፡

ወዲያው ከሰማይ ቅዱስ ፋኑኤለ የተባለው መልአክ መጣ መልአኩ እመቤታችን አቅፎ በአንድ ክንፉ ከልሎአት ከሰማይ ያመጣውን ኅብስት እና መጠጥ መግቦአት እንደመጣው ሁሉ ወደ ሰማይ አረገ፡፡ካህኑ ዘካርያስና ህዝቡም እግዚአብሔር ምግቧን እና መጠጧን እንዳዘጋጀላት ተመለከቱ፡፡ ካህኑ ዘካርያስ በፍፁም ደስታ እመቤታችንን ተቀብሎ ወደ ቤተ መቅደስ አሥገባት ይህ ዕለት ታኅሳስ 3 ቀን ሲሆን በዓታ ለማርያም ተብሎ በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን እኛንም በእመቤታችን ጸሎት ይማረን !!! አሜን
9 viewsbisrat, 23:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 19:47:22
40 viewsbisrat, 16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 19:46:37 #ታህሳስ_1_ልደቱ_ለርዕሰ_ነቢያት_ወባህታውን_ቅዱስ_ኤልያስ።

‹‹ኤልያስ›› ማለት ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡

ነቢዩ ኤልያስ በገለአድ አውራጃ በቴስብያ፣ በእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ጸንተው ይኖሩ ከነበሩ ጻድቃን ወላጆቹ ከሌዊ ወገን ከሚኾን አባቱ ከኢያሴንዩ እና ከእናቱ ቶና ታኅሣሥ 1 ቀን ተወለደ፡፡ በተወለደ ቀንም በቤታቸው በብርሃን ተሞላ፤ እግዚአብሔር ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መርጦታልና 4 መላእክተ ብርሃን ሰገዱለት፤ በጨርቅ ፈንታም በእሳት ጠቀለሉት፡፡ እናትና አባቱም በኹኔታው ከመፍራታቸው የተነሣ ወደ እርሱ መቅረብን ፈሩ፡፡ ወላጆቹ ይህን በማየታቸው ደንግጠው ለነቢያትና ለካህናት ነገሯቸው፤
ካህናቱም ነገሩ ቢረቅባቸው "ምን ዓይነት ፍጥረት ይሆን? በእሥራኤል ይነግሥ ይሆን! ወይስ ነቢይ ይሆን?" ብለውም አድንቀዋል።


በስምንተኛው ቀን ሥርዓተ ግዝረት ሲፈጽሙለትም ስሙን ‹ኤልያስ› አሉት፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ሕገ ኦሪትን እየተማረ ካደገ በኋላ እናቱንና አባቱን፣ ዘመዶቹንም፣ ገንዘቡንም ዅሉ ትቶ በበረሃ ተቀመጠ፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱ 11፥37-38 ‹‹… ማቅ፣ ምንጣፍና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ተጨነቁ፤ ተቸገሩ፤ መከራ ተቀበሉ፤ ተራቡ፤ ተጠሙም፡፡ ዓለም የማይገባቸው እነዚህ ናቸው፤ ዱር ለዱርና ተራራ ለተራራ፣ ዋሻ ለዋሻና ፍርኩታ ለፍርኩታም ዞሩ፤›› በማለት እንደ ተገናረው ነቢዩም ከዓለማዊ ኑሮ ተለይቶ ማቅ ለብሶ በየተራራው፣ በየፍርኵታውና በየዋሻው መኖር ጀመረ /ገድለ ኤልያስ ነቢይ ዘታኅሣሥ፣ ቍ.1-9/፡፡

ወቅቱ (ከክርስቶስ ልደት 900 ዓመት በፊት) ሕዝቡና ነገሥታቱ የከፉበት፤ እግዚአብሔር ተክዶ ጣዖት የሚመለክበት ነበር። ድሮ በኢሎፍላውያን እጅ የነበሩት ጣዖታት (ዳጐንና ቤል) በዚያ ዘመን ወደ እሥራኤል ገብተው ነበር። ቅዱስ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን የጠነቀቀ: የንጽሕናና የአምልኮ ሰው ነበር።

በዚያ ወራትም እግዚአብሔር ለነቢይነት ጠራው። እርሱም "እሺ" ብሎ ታዞ የእግዚአብሔርን የጸጋ ጥሪ ተቀበለ። ቅዱሱ ብዙ ጊዜ ለጉዳይ ካልሆነ ከሰው ጋር መዋል ማደርን አይወድምና መኖሪያውን በተራሮችና በዱር አደረገ። በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ ለእርሱ ቤቱ ነበር።

#ነቢዩ_ኤልያስ_በእግዚአብሔር_ኀይል_ካደረጋቸው_ታላላቅ_ተአምራት_መካከልም_ጥቂቶቹ :-

1.ዝናም ማቆሙና ዳግመኛ እንዲዘንም ማድረጉ (1ኛ ነገ.17፥1-2፤ 18፥46-48)፤

2.የደሃዋን ቤት በበረከት መሙላቱ (1ኛ ነገ.17፥16-24)፤

3.የሞተውን ልጅ ማስነሣቱ (1ኛ ነገ.17፥20- 23)፤

4.በካህናተ ጣዖት ፊት መሥዋዕቱን ወደ እግዚአብሔር ማሳረጉና የጣዖቱ ካህናትን ማሳፈሩ (1ኛ ነገ.18፥20-40)፤ እና

5.ጠላቶቹን በእሳት ማቃጠሉ (2ኛ ነገ.1፥9- 13) ተጠቃሾች ናቸው፡፡

የሚያርግበት ጊዜ ሲደርስም ደቀ መዝሙሩን ኤልሳዕን "የምትሻውን ለምነኝ" ቢለው "እጥፍ መንፈስህን" አለው:: 3 ጊዜ ሊያስመልሰው ሞከረ። ቅዱስ ኤልሳዕ ግን በብርታት ተከተለው። ዮርዳኖስን ከፍለው ከተሻገሩ በሁዋላ ግን ቅዱስ ኤልያስን ሠረገላ እሳት ወርዶ ነጠቀው። ለኤልሳዕም መጎናጸፊያውን ጣለለት።

ዛሬ ቅዱስ ኤልያስ በብሔረ ሕያዋን ያለ ሲሆን በዘመነ ሐሳዌ መሲሕ መጥቶ በሰማዕትነት ከቅዱስ ሔኖክ ጋር ያርፋል። (ራዕይ) ለተጨማሪ ንባብ ( ከ1ነገ. 17-2ነገ. 2 / እና ዕርገተ ኤልያስ ) 

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ቀጥላ ቅዱስ ኤልያስን ታከብራለች። "ርዕሰ ነቢያት - የነቢያት ራስ፤ ርዕሰ ባሕታውያን - የባሕታውያን ራስ" ትለዋለች። እርሱ ሰማይን የለጐመ፤ እሳትን ያዘነመ፤ ፍጥረትንም በቃሉ ያዘዘና ለብቻው በጸሎት የተጋ አባት ነውና።

በየዓመቱ ታኅሣሥ 1 ቀን የነቢዩ ኤልያስ በዓለ ልደት፤ ጥር 6 ቀን ደግሞ ዕለተ ዕርገቱ በመንፈሳዊ ሥርዓት ይከበራል፡፡


"ለእስራኤል ሁሉ ሥርዓትንና ፍርድን አድርጌ በኮሬብ ያዘዝኩትን የባሪያየን የሙሴን ሕግ አስቡ። እነሆ ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላቹሃለሁ። መጥቼም ምድርን በእርግማን እንዳልመታ እርሱ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የልጆችንም ልብ ወደ አባቶች ይመልሳል" (ሚል. 4:4)

ለእግዚአብሔር ክብር እኛንም በነብዩ ጸሎት ይቅር ይበለን!!!
41 viewsbisrat, 16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 20:05:42
23 viewsbisrat, 17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 20:05:26 #ኅዳር_29_የሃይማኖት_አርበኞች_ቅዱሳን_ሰማዕታት_ታስበው_የሚውሉበት_ዕለት_ነው።

አርበኛ ማለት ስለ ሀገሩ እና ሰለ ነፃነቱ እስከ ሞት ድረስ የታገለ ማለት ሲሆን የክርስትና አርበኛ ደግሞ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ብሎ ዓለምን እና ምኞቱን የተወ በእምነት ዲያብሎስን ድል የነሳ ማለት ነው፡፡

ሰማዕት ማለትም የእውነት ምስክር ማለት ሲሆን በሃይማኖቱ ምክንያት የተገደለ ሰው ሰማዕት ይባላል፡፡ ቅዱሳን ሰማዕታት የሚባሉት “እግዚአብሔርን ካዱ ለጣኦት ስገዱ ሲባሉ “እግዚአብሔርን አንክድም ለጣዖትም አንሰግድም” በማለት በዓላውያን ነገስታት ፊት ቀርበው ሳያፍሩና ሳይፈሩ ስለፈጣሪያቸው የመሰከሩ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ተዘረዝረው የማያልቅ መከራ ተቀበለዋል ህይወታቸውንም ስለ ፈጣሪያቸው አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ ይሕንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “እስከ ሞት ተደበደቡ በሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወህኒ ተፈተኑ በድንጋይ ተወግረው ሞቱ ተፈተኑ በመጋዝ ተሰነጠቁ በሰይፍተ ገድለው ሞቱ በማለት ገልጦታል፡፡ ዕብ11:35-36 ስለ ራሱም መከራ 2ቆሮ11:23-28 ላይ ተናግሯል፡፡

ይህ ሁሉ መከራ ከእምነታቸው እንዳላናወጣቸው ሲናገር “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ወይስ ጭንቀት ወይስ ስደት ወይስ ራብ ወይስ ራቁትነት ወይስ ፍርሃት ወይስ ሰይፍ ነው? ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደተፃፈ ነው” ብሏል ሮሜ 8:35-36 እና መዝ43:22፡፡
 

በአጠቃላይ አምነታቸውን ጠብቀው፣ በወንጌል መሠረት ላይ ቆመው፣ መስቀሉን ተሸክመው፣ የቅድስናን ሥራ እየሠሩ የዓለምን እና የዲያብሎስን ምኞት ያለ ደም መፍሰስ በእምነት፣ በጸሎትና በጾም ስለ ሃይማኖታቸው የሚጋደሉ ምእመናንን የሚያጠቃልል ሐረግ ነው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ በመስቀል ላይ የከበረ ደሙን በማፍሰሱ ሰማዕታት የእርሱን ፈለግ በመከተል ስለ እውነት፣ ስለ ወንጌልና ስለመንግሥተ ሰማያት ሕይወታቸውን እንዲሰዉ ኃይል ሆኗቸዋል፡፡ በዚህ የተነሣ በማያምኑ ሰዎች ፊት ስለ ወንጌል ሲመሰክሩ የሞቱትን የወንጌል አርበኞች ሰማዕታት ቤተ ክርስቲያን ታከብራቸዋለች፡፡

ሰማዕታት በበጉ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም አማካኝነት እና የወንጌሉን ቃል በሕይወታቸው በተግባር በመኖር በመንፈሳዊ ሕይወት ዲያብሎስን እና ምኞቱን እንዴት ድል ማድረግ እንደሚቻል አሳይተውናል፡፡ ሰማዕታት የእውነት ምስክሮች፣ የክፉ ሰዎችን ዛቻ እና ማስፈራራት ሳይሰቀቁ በድፍረት ስለክርስቶስ የመሰከሩ በአጠቃላይ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ክርስትናን በእምነት፣ በፍቅር እና በትሕትና የኖሩ ናቸው፡፡ አባቶቻችን ቅዱሳን እና ሰማዕታት በዚህ ምድር ብዙ መከራ ተቀብለዋል፡፡ ታስረዋል፣ ተደብድበዋል፣ ተሰደዋል፣ ተርበዋል፣ ተገድለዋል . . . ወዘተ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነባቸው እግዚአብሔርን በማመናቸው እና የእውነት ምስክሮች ስለነበሩ ነው፡፡ ነገር ግን የእግዚብሔር ሰላም እና ፍቅሩ በልባቸው ያለ ማቋረጥ ይፈስ ስለነበረ ደስ እያላቸው መከራን ሳይፈሩ ይቀበሉ ነበር፡፡

ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ ቅዱስ ጳውሎስ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ፣ ቅዱስ ያዕቆብ፣ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ . . . ወዘተ. ቤተ ክርስቲያን ሁል ጊዜ (በይበልጥ ኅዳር 29) የምታስታውሳቸው ሰማዕታት ናቸው፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታቱ ጸሎት ይማረን !!! አሜን
23 viewsbisrat, 17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 15:27:32
19 viewsbisrat, 12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 15:27:30 #ኅዳር_26_ዕረፍቱ_ለአቡነ_ሀብተማርያም_ጻድቅ
 
#ልደቱ
አምስቱን መቅሰፍቶች የማስወገድ ስልጣን የተሰጠው ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም የነበረበት ዘመን 1486 ዓ.ም ንጉስ እስክንድር በነገሰበት ጊዜ ነው፡፡ አባቱ ፍሬ ቡሩክ እናቱ ዮስቴና ይባላሉ፡፡ ፍሬ ቡሩክና ዮስቴና በህገ እግዚአብሔር በሃይማኖት በትሩፋት በምግባር ፀንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡


የፃዲቁ አቡነ ሀብተ ማርያም እናት ቅድስት ዮስቴና ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያምን ከመውለዷ በፊት ሰው ሁሉ ዓለሙን ቢገዛ ነፍሱን ካጣ ምን ይጠቅመዋል የሚለውን የወንጌል ቃል ተረድታ መንና ወደ በረሃ ሄደች፡፡ በበረሃ ውስጥም ከሰው ተለይቶ የሚኖር ባህታዊ በዋሻ ውስጥ አገኘች፣ ''የመጣሁት ለምነና ነው ጌታ በወንጌሉ እርፍን ይዞ ወደ ኋላ የሚያርስ የለም እንዳለ ወደ ዓለም አልመለሰም'' አለችው፡፡ (ሉቃ 9፣62) ይህም ባህታዊ ''ምናኔ ምንኩስና ለአንቺ አልተፈቀደልሽም ከህጋዊው ባልሽ ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ ይተርፋል በፀሎቱም ብዙዎቹን ይጠቅማል እንደ መልአክትም ክንፈ ጸጋ ተሰጥቶታል'' በማለት ነገራት፡፡ ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባህታዊ ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች ''የፈጣሪዬ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ'' ብላ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡

ጥቂት ጊዜያት ከቆየች በኋላ ግንቦት 26 ቀን ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ተወለደ፡፡ በአባቱና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ 40 ቀን ሞልቶት በተጠመቀ ዕለትም ሀብተማርያም ተብሎ ተሰየመ፡፡ ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም በፈሪሃ እግዚአብሔር በትምህርት አደገ፡፡
ከዕለታት በአንድ ቀን ካህናቱ በቤተክርስቲያን ምህላ ሲያደርሱ ''እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ'' እያሉ ሲፀልዩ ሰምቶ በልቡናው ይህች ፀሎት በጣም ጥሩና መልካም ፀሎት ናት አለ በዚህ ፀሎት ከዓለም አሳችነት ከገሃነም እሳት እንድንባት ዘንድ አውቃለሁ የንስሐ መንገድ ናት ብሎ ተናገረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም በዚህች ፀሎት ተጠምዶ በጾምና በፀሎት በስደት የሚኖር ሆነ፡፡

#የአገልግሎት_ጥሪው
አባቱ ፍሬ ብሩክ አቡነ ሀብተማርያምን የበግ ጠባቂ አደረገው እግዚአብሔር ግን በኋላ ለብዙዎች ስውራን ቅዱሳንና በዓለም ለሚኖሩ ምዕመናን በጎች ጠባቂ ያደርገው ዘንድ ወዶ መርጦታልና ያ ቀን እስኪደርስ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ አቡነ ሀብተማርያምን ይጠብቀው ነበር፡፡
አባታችን አቡነ ሀብተማርያም ከአባቱ አጠገብ ተኝቶ ሳለ ‹‹ሀብተማርያም ሀብተማርያም›› የሚል ድምጽ በሌሊት ከሰማይ መጣ፡፡ አባቱ በአጠገቡ ተኝቶ ስለነበረ የጠራው መስሎት አባቴ ሆይ አለሁ ሲል መለሰ ከዚህ በፊት ቃል ከሰማይ ጠርቶት አያውቅም ነበርና እንደ ሳሙኤል ጌታዬ ባሪያህ ይሰማሃል ተናገር አለ፡፡ (ሳሙ3፤3) ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አናገረው፡፡

ከዚህም በኋላ አባቱ ከሀገሪቱ ታላላቅ ሰዎች አንዷን እጮኛ አጨለትና ታገባለህ አለው አባታችን አቡነ ሀብተማርያም አባቴ ሆይ እኔ ራሴን ለክርስቶስ በድንግልና ለመኖር አጭቻለሁ ተራክቦዬም ቃለ ወንጌልን መስማት እንጂ ሌላ አይደለምና ለምን እንዲህ ትለኛለህ አለ፡፡ አባቱም ያለ አቡነ ሀብተማርያምፈቃድ ሙሽራይቱን ለማምጣት ሄደ፡፡ አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም ሀገር ጥሎ ለመሰደድ ከቤት ተደብቆ ወጣ፡፡ መንፈስ ቅዱስም በመብረቅ አምሳል አባቱን ገሰፀው በዚህ ድንጋጤ ምክንያት የስጋ አባቱ ከዚህ ኃላፊ ዓለም አረፈ፡፡

#አገልግሎቱና_ተአምራቱ
አባታችን አቡነ ሀብተማርያምም የአባቱን እረፍት ሳያይ አፋር ወደምትባል ሀገር ወደ አሰቦት አቡነ ሳሙኤል ገዳም ሄደ አባ ሳሙኤል ከሚባሉ ደግ መነኩሴ ቦታ ገብቶ ኖረ፡፡ በዚያም ገዳም ውሃ በመቅዳት እንጨት በመስበር፣ ልብስ በማጠብ እህል በመፍጨት አበው መነኮሳትን ሲያገለግል ኖረ፡፡ በአባታችን ላይ መነኮሳት ተቆጥተው ሲነሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በገሃድ ተገልፃ ትገስፃቸውም ነበር፡፡

በዚህ አገልግሎት ላይ ሳለ ገዳሙ ካለበት ተራራ ላይ ወደ በረሃ ወርዶ ውሃ ቀድቶ ተሸክሞ ሲመለስ ውሃውን በእንስራ እንደተሸከመ እግሩን አደናቀፈው፡፡ የቀዳው ውሃ ሊደፋበትና እንስራውም ሊሰበርበት ሲል ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አድነኝ ትወድቅ ዘንድ አትተዋት ብሎ ፀለየ፡፡ ይህን ብሎ በተናገረ ጊዜ የውሃዋ እንስራ ሳትወድቅ ቆመች እጅም ሳይነካት ተመልሳ በትከሻው ላይ ተቀመጠች አባ ሳሙኤልም ይከተሉት ነበርና ይህን ጽኑ ተዓምር አይተው አደነቁ፡፡ (ማር. 9፡23)

እንዲሁ ከዕለታት በአንድ ቀን በሌሊት መብራት ለአባ ሳሙኤል እያበራ ሳለ መብራቱ ከእጁ ወድቆ ጠፋ፡፡ ስለ መምህሩ ስለ አባ ሳሙኤል ቁጣ፣ ፍራቻ፣ ታላቅ ድንጋጤ ደንግጦ ፈጥኖ ባነሳው ጊዜ በእግዚአብሔር ተዓምር ራሱ በራ፡፡ አባ ሳሙኤልም ይህን ተዓምራት አይተው የዚህ ቅዱስ ልጅ የዓለም ሁሉ የጥበብ መብራት ይሆናል ሲሉ ትንቢት ተናገሩ፡፡ በዚህችም ገዳም 12 ዓመት ከትህትና ጋር እየታዘዘ ቤተክርስቲያንን እያገለገለ ኖረ፡፡

ፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ከአባ ሳሙኤል ገዳም ወጥቶ እለ አድባር ወደ ተባለ ገዳም ሄደ፡፡ ከአባ መልኬጼዴቅ እጅ የምንኩስናን ስርዓት ተቀበለ፡፡ ከዚያም በመቀጠል በጥልቅ ባህር ገብቶ 150 መዝሙረ ዳዊትና አራቱን ወንጌልና ሌሎች የፀሎት መጽሐፍትን እየፀለየ አምስት መቶ ጊዜ ይሰግድ ነበር፡፡ እህል መብላትን ትቶ እንደ በረሃ ዋልያ ቅጠል መብላት ጀመረ፡፡ አርባ ቀን የሚጾምበት ጊዜና ሰማንያ ቀንም የሚጾምበት ቀን ነበር፡፡ ቅጠልም ቢሆን እህል ቀዝቃዛ ወይም ምንም አይቀምስም ነበር፡፡ ፊቱም እንደ ንጋት ኮከብ ያበራ ነበር፡፡አራቱን ወንጌላት ይጸልያል።

አባታችን አቡነ ሀብተማርያም እንዲህ ባለ ስራ ላይ ሳለ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደ እርሱ መጥቶ:- ''ልጄ ሀብተማርያም የምለምንህ ነገር አለና እሺ በለኝ በሀገሬ ላይ የታዘዙ 5 መቅሰፍቶች አሉ የአንተም አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገሬ ከነዚህ መቅሰፍታት ትድናለች ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀበር ቃል ኪዳን ግባልኝ'' አለው፡፡

በአቡነ ሀብተማርያም አጽም የራቁት መቅሰቶች እነሱም፡- 1. መብረቅ፣ 2. ቸነፈር፣ 3. ረሃብ፣ 4. ወረርሽኝ፣ 5. የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡

#ዕረፍቱ
ከዚህም በኋላ መልአኩ ለአቡነ ሀብተ ማርያም ክብሯ እንደ ጽርሐ አርያም የሆነች ቦታን አሳያቸው፡፡ ሥፍር ቁጥር የሌላቸውም ቅዱሳን መላእክት በውስጧ ተድላ ደስታ ያደርጉባት ነበር፡፡ አባታችንም መልአኩን ‹‹ይህች ክብሯ ፍጹም የሆነችን ቦታ ማን ትባላለች በውስጧ ለመኖር በእጅጉ ወድጃለሁና›› ብለው ሲጠይቁት መልአኩም ‹‹ይህችማ ቦታ የአባትህ የተክለ ሃይማኖት አጽም ያረፈባት ደብረ ሊባኖስ ናት፤ ከእርሱም ጋር በክብር እስክትነሣ ድረስ በውስጧ ትቀበርባት ዘንድ ለአንተም ተሰጥታሃለችና ደስ ይበልህ፡፡ አባትህም እንደ ኢየሩሳሌም እንደትሆንለት ቃልኪዳን ተቀብሎባታል›› አላቸው፡፡

ከዚህም በኋላ የአባታችን የአቡነ ሀብተ ማርያም ዕለተ ዕረፍታቸው በደረሰ ጊዜ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በታላቅ ምስጋና ወደ ብፁዕ አባታችን መጥቶ ‹‹ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሆይ! ዛሬ ወደ አንተ የመጣሁት ከድካም ወደ ዕረፍት እወስድህ ዘንድ ነው፣ ሰባት የጽድቅ አክሊሎችን አዘጋጅልሃለሁ›› በማለት ታላቅ የምሕረት ቃልኪዳን ከገባላቸው በኋላ ጌታችን አባታችንን ሦስት ጊዜ ሳማቸው፡፡ ያን ጊዜም ከመድኃኔዓለም ጣዕም ፍቅር የተነሣ ኅዳር 26 ቅድስት ነፍሳቸው ከሥጋው ተለየች፡፡

የጻድቁ አባታችን በረከት ረድኤት ከእኛ ጋር ይሁን!!!!
21 viewsbisrat, 12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 19:26:08 #ህዳር_24_ጻድቅ_ተክለሃይማኖት_25ተኛ_ካህናተ_ሰማይ_ሆነው_የሥላሴን_መንበር_ያጠኑበት_ዕለት_ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ “ጻድቅ” የሚለው ቃል ሕግን መፈጸም፣ እንደ ሕግ መኖርና መመራት፣ ትክክለኛነትን እና እውነተኛነትን ያመለክታል፡፡ “ጻድቅ” የሚለውም ቃል በሕግ የጸና፣ እንደ ሕግ የሚኖር እውነተኛ ሰውን የሚወክል ቃል ነው፡፡
ሰዎች አካሄዳቸውን በእግዚአብሔር ፊት ሲያደርጉና እንደ እግዚአብሔር ሕግ ሲኖሩ ጻድቃን ይባላሉ፡፡

ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትም በእግዚአብሔር ፊት እንደ እግዚአብሔር ሕግ የኖሩ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ናቸው፡፡ ጻድቁ ተክለሃይማኖት እግዚአብሔርን ከሚወዱ እና ክሚያከብሩ ከአባታቸው ጸጋዘአብ እና ከእናታቸው እግዚእ ሐረያ ታኅሣሥ 24 ቀን ተወለዱ፡፡

ጸጋዘአብ ማለት የአብ ጸጋ ማለት ሲሆን እግዚእ ሐረያ ማለት ደግሞ በጌታ የተመረጠች ማለት ነው፡፡ ጸጋ ዘአብ እና እግዚአ ሐረያ እግዚአብሔርን በፍጹም ልባቸው የሚያምኑ፣ በተለያየ ሕመም የሚሰቃዩ እና ችግረኞችን የሚረዱ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ በተለይ ለእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ሚካኤል የተለየ ፍቅር ስለነበራቸው በየወሩ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት በመታመን የመልአኩን በዓል ድሆችን በመንከባከብ ያከብሩ ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ቅዱስ ሚካኤል በሕልም ተገልጾ እግዚአብሔር የተባረከ ልጅ እንደሚሰጣቸው ነገራቸው፡፡ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ወንድ ልጅ ፍሥሐጽዮን ብለው ጠሩት፡፡ ፍሥሐጽዮን ማለት የጽዮን ደስታ ማለት ነው፡፡ ሕፃኑ ፍሥሐጽዮን መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ በሶስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐድ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብሎ አመሰገነ፡፡ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለነበር ፍሥሐጽዮን በልጅነቱ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፡፡

በአንድ ወቅት ረሃብ ነበር ቤተሰቦቹ በዚህ ምክንያት የቅዱስ ሚካኤልን ዝክር እንዳያቋርጡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ዱቄትና ዘይት በማብዛት ቤተሰቦቹ ዝክሩን ያለምንም ችጋር እንዲዘክሩ አድርጓል፡፡ ዝክር ማለት በእግዚአብሔር፣ በቅዱሳን እና በመላእክት ስም የሚደረግ መታሰቢያ ነው፡፡ ፍሥሐጽዮን እግዚአብሔርን እያገለገለ አደገ፡፡

በዐሥራ አምስት ዓመቱ ከአቡነ ቄርሎስ ሁለተኛ ዲቁና ተቀበለ፡፡ ወደ ቤት ሲመለስ ቤተሰቦቹ አንዲት ሴት እንዲያገባት እንዳጩለት ነገሩት፡፡ ነገር ግን ፍሥሐጽዮን ይህን ጥያቄ አልተቀበለውም ነበር፡፡ አንድ ቀን ፍሥሐጽዮን ከጓደኞቹ ጋር ለአደን እንደወጣ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ከዚህ በኋላ ያለውን ቀሪ ዘመኑን የሰዎችን ነፍስ በማዳን እግዚአብሔርን እንዲያገለግል መመረጡን ነገረው፡፡ መልአኩ የፍስሐጽዮንን ስም ተክለሃይማኖት (የሃይማኖት ዛፍ (ተክል)) ብሎ ለወጠው፡፡ ከዚህ በኋላ ተክለሃይማኖት ወደቤቱ ተመልሶ ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን እና ለድሆች ሰጥቶ ወደ ገዳም ሄደ፡፡

በገዳም እያገለገለ እና እየተማረ የቅድስና ማዕርግን ተቀበለ፡፡ በትጋት ወንጌልን በመስበኩ ብዙ ሰዎችን ወደ ክርስትና ተመለሱ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለብዙ ዓመታት በአገልግሎት ከቆየ በኋላ አንድ ቀን በገመድ ሲወርድ ገመድ ተበጥሶ ሲጸልይ ክንፍ ተሰጠው፡፡

ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ሃያ ዘጠኝ ዓመታትን ያሳለፈው ደብረ አሰቦ በተባለ ቦታ ቆሞ በመጸለይ ነበር፡፡ ለረጅም ሰዓታት በመቆም ይጸልይ ስለነበረ እግሩ ሊቆረጥ ችሏል፡፡ አንድ እገሩ ቢቆረጥም ጸሎቱን እና ትጋቱን አላቋረጠም ነበር፡፡ በአንድ እግሩ ለሰባት አመታት ጸልዮአል፡፡  በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው (አወጣቸው) ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበረን “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አጥነዋል


ጻድቁ ተክለሃይማኖት ዘመኑን ወንጌልን ለማያምኑ ሰዎች በመስበክ ብዙ ኢ-አማንያንን ክርስትናን እንዲቀበሉ አድርጓል፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እንዲሰፋ እና ገዳማዊ ሕይወት እንዲጠነክር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ሲሆን በዘጠና ዘጠኝ ዓመቱ ነሐሴ ሃያ አራት ቀን በክብር አርፏል፡፡
ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን እኛንም በጻድቁ ጸሎት ይማረን።
አ ሜ ን ! ! !
18 viewsbisrat, 16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 19:26:05
18 viewsbisrat, 16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ