Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-01-14 18:58:32
31 viewsbisrat, 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-14 18:58:05 #ጥር_7_ቅድስት_ሥላሴ_በሰናዖር_ምድር_ድንቅ_ተአምር_የፈጸሙበት_ዕለት_ነው፡፡

ከጥፋት ውሃ በኋላ የኖኅ ልጆች ወልደው ተዋልደው ብዙዎች ሆኑ፡፡ በዚያም ጊዜ ምድር በአንድ ቋንቋ እና በአንድ ንግግር ነበረች፡፡ ዛሬ በምድራችን ያሉ ሰዎች የሚናገሩዋቸው የተለያዩ ቋንቋዎች ድሮ አልነበሩም ከዚያም ከምሥራቅ ተነስተው ሰናዖር በተባለ ቦታ አንድ ሰፊ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ።

ብዙ ሥራዎችን ይሠሩ እና ይፈጥሩ ጀመር፡፡
ከነዚህም አንዱ ጡብ መሥራት ነበር፡፡ እርስ በርሳቸውም ‹ሳንሞት ስም ማስጠሪያ ግንብ እንገንባ› ብለው መክረው ታላቅ ግንብ ገነቡ፡፡

አለቃቸው ናምሩድ ይባላል! ‹‹ሞትን የሚያመጡብን ሥላሴ ናቸውና እነርሱን ወግተን ሞትን እናርቅ ›› ...አላቸው... ከዚያም ሆነው ጦር እየሰበቁ ይወረውሩ ጀመር ሰይጣን... ከደመና በምትሀት ደም እየቀባ ይልክላቸዋል... እነርሱም ደሙን እያዩ ‹‹ አሁን አብን ወጋነው አሁን ወልድን ወጋነው ….›› ይሉ ጀመር ቅድስት ሥላሴ ምንም እንኳ ምህረታቸው የበዛ ቢሆንም በሕዝቡ ላይ ዲያብሎስ ስለሠለጠነባቸው .... እርስ በእርስ እንዳይግባቡ ቋንቋቸውን ደበላለቁባቸው የማይግባቡ፣ የማይደማመጡ…… ሆነው ተበታትነዋል፡፡(ዘፍ.11:1-9)
ባለማስተዋል የሠሩትንም የአመጻ ሕንፃ  ነፋስ ጠራርጎ አጥፍቶታል፡፡ ይህን ያደረጉ ቅድስት ሥላሴ ስለሆኑ ጥር 7 በዓሉ ይከበራል ...

ሥልጣን ሁሉ የእግዚአብሔር መሆኑን እና በራስ ደካማ አመለካከት በመታበይ በሥላሴ ሥራ መግባት’ መጠራጠር ….. እንደሚጎዳ እንደዚሁም በጽኑ እምነት በመኖር እና በሥላሴ ስም የተጠመቅን ልጅነታችንን በኃጢአት ሳናሳድፍ በንስሐ ታጥበን እና በምግባር ጸንተን መጠበቅ እንደሚገባ የበዓሉ መልእክት ያስገነዝበናል፡፡ የአብርሐም ፣ የይስሀቅ ፣ የያዕቆብ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በፈጠረው ሁሉ የተመሰገነ ይሁን!!!

ወ ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወ ለወላዲቱ ድንግል
ወ ለመስቀሉ ክቡር !
ይምሐረነ ወ ይስሀለነ በእንተ ርትዕት ሐይማኖት ያጽንአነ! ለይኩን! ለይኩን! ለይኩን
73 viewsbisrat, 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 13:59:03
48 viewsbisrat, 10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 13:58:43 #ጥር_6_ታላቋ_ሰማዕት_ቅድስት_አርሴማ_የተወለደችበት_ዕለት_ነው።

የቅድስት አርሴማ እናት ቅድስት አትናሲያ አባቷ ቅዱስ ቴዎድሮስ ይባላሉ፤ እናትና አባቷ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ከካህናት ወገን የሆኑ መልካም ምግባር የነበራቸው ነበሩ፤ ልጅ ስላልነበራቸው ልጅ እንዲወልዱ ስዕለትን ተሳሉ፤ እግዚአብሔርም ልጅን ሰጣቸው፡፡ በሥነ ምግባርና ብሉይና አዲስ ኪዳንን እያስተማሯት አደገች፡፡

በሥነ ምግባር ታንጾ ለመኖር ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ይገባል፤ የእግዚአብሔር ወዳጅ ቅድስት አርሴማ በጥሩ ሥነ ምግባር ካደገች በኋላ ለወላጆቿ እየታዘዘች በሥርዓት ኖረች፡፡ ጾመኛ፣ ጸሎተኛ፣ ደግ ሴትም ነበረች፡፡ ለሰዎችም ታዝን ነበር፤ ካደገች በኋላ ደግሞ በድንግልና ሕይወት መኖርን መረጠች፤ መንኩሳም በገዳም ታገለግል ጀመር፡፡

እርሷ በነበረችበት ዘመን እግዚአብሔርን ክዶ የሚያስክድ ዲዮቅልጥያኖስ የተባለ ጨካኝ ንጉሥ ነበር፤ ክርስቲያኖችን ለጣዖት ስግዱ እያለ መከራ አጸናባቸው፤ ቅድስት አርሴማ እና ሃያ ሰባት ደናግል በገዳም በጾም በጸሎት በነበሩ ግዜ ጨካኙ ንጉሥ በሰይጣን ተገፋፍቶ ቅድስት አርሴማን ሊያገባት ፈለገ፡፡ እርሷ ግን በድንግልና ሕይወት መንኩሳ መኖርን መርጣ ነበርና ከጓደኞቿ ጋር ሆና አርማንያ ወደ ተባለ አገር ተሰደዱ፡፡

ለጊዜው ከጨካኙ ንጉሥ አምልጠው በገዳም ውስጥ በጾም በጸሎት ተግተው ሳለ ንጉሡ ለአርማንያ አገረ ገዢ ለንጉሥ ድርጣድስ መልእክት ላከ፤ ‹‹ አንተ አገር ተሰደው የመጡ ደናግል አሉና ይዘህ ላክልኝ ›› አለው፤ ከዚያም አፈላልገው ቅድስት አርሴማን አገኟት፤ ድርጣድስ ባያት ጊዜ ከደም ግባቷ ማማር የተነሣ ‹‹ ላግባሽ›› ብሎ ጠየቃት፤ እርሷም ‹‹ እኔ በድንግልና ሕይወት የምኖር የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ፤ ማግባት አልፈልግም ›› አለችው:: በግድ አስገድዶ ሊያገባት ሲሞክር እጁን ጠምዝዛ በዐደባባይ ጣለችው፤ በዚህን ጊዜ በጣም አፈረ፤ በእርሷ እና በጓደኞቿ ደናግል መከራ እንዲያጸኑባቸውም አዘዘ፡፡

አንበሶች እንዲበሏቸው አንበሳ ካለበት ከተቷቸው፤ አንበሶቹ ግን ሳይበሏቸው ቀሩ፤ ዳግመኛም በረኃብ እንዲሞቱ ምንም መብልና መጠጥ በሌለበት ቤት አሠሯቸው፤ እግዚአብሔርም የሚበሉትን በሞሶብ የሚጠጡትን በጽዋ ከሰማይ አወረደላቸው፤ ከእሳትም ሲጨመሯቸው ደግሞ እሳቱ አላቀጠላቸውም፤ ይህን ድንቅ ተአምር እግዚአብሔር አድርጎላቸው፤ ከግፈኞች እጅ አስጣላቸው፡፡

እግዚአብሔር ብቻ ለማምለክ ቆርጠው በተነሱ ደናግሉ ላይ ይህ ሁሉ መከራ ደርሶ ለጣዖት ባለመስገዳቸው አሁንም ንጉሥ ድርጣድን አበሳጨው፤ ቅድስት አርሴማን ለማስፈራራት ብሎ አብረዋት የነበሩትን ጓደኞቿን አንድ በአንድ በግፍ በሰይፍ ቀላቸው፤ ለሚሰውት (ለሚገደሉት) ሁሉ አክሊል ከሰማይ ይወርድላቸው ነበር፤ ቅድስት አርሴማም ‹‹ ይህን እያየች አይዟችሁ ጽኑ›› ትላቸው ነበር፡፡

ንጉሡም በቁጣ ለእግዚአብሔር ታማኝ ሆና ጸንታ የቆመችውን ቅድስት አርሴማን ‹‹ አንቺን እንደነርሱ በቀላሉ አልገድልሽም ›› በማለት ብዙ መከራ አጸናባት፣ ዓይኖቿን አወጣ፤ በብዙ ዓይነት ሥቃይም አሠቃያት፤

ስለስሙ በመመስከሯ፣ በድንግልና ሕይወት በመጽናቷ፣ የዚህን ዓለም ኑሮ ንቃ በብሕትውና በመኖሯ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦ ቃል ኪዳን ገባላት፤ ስሟን ጠርቶ የሚማጸን፣ ገድሏን የጻፈ ያነበበ፣ የሰማ፣ በስሟ የመጸወተውን እንደሚምርላት ቃል ኪዳን ሰጣት፤

በመስከረም ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀንም በሰይፍ ተሰይፋ ሰማዕትነትን ተቀብላለች፡፡ የእግዚአብሔር አገልጋይ እናታችን ቅድስት አርሴማ ለሰው ልጆች ድኅነት ፈጣሪን ተማጽና ምሕረትን አሰጥታለች፤ በዘመኗ ብዙ ድንቅ ተአምራትን አድርጋለች፤ መከራ ላደረሱባትም ጸልያለች፤ ከብዙ ዘመን በኋላም እርሷን እንድትገደል ያደረገው ጨካኙ ንጉሥ ድርጣድስ ከክፉ ሥራው ተመልሶ ንስሓ ገብቶ እርሱም ስለ ክርስቶስ መስክሮ ለክብር ሕይወት በቅቷል፡፡

በእናታችን ቅድስት አርሴማ መከራ ላደረሱባት በመጸለይዋ ሳያውቁ ይሠሩት ከነበረው ክፉ ሥራቸው እንዲመለሱ አድርጋቸዋለች፡፡

ልደቷ ጥር 6
ሰማዕትነት የተቀበለችበት መስከረም 29
ቅዳሴ ቤቷ ታህሳስ 6 ታስቦ ይውላል ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቷ ጸሎት ይማረን!!!
93 viewsbisrat, 10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 20:21:53
52 viewsbisrat, 17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 20:21:33 የድንግል ማርያም የቅድስና ጠባያት 1)የንጽህና ህይወት
እመቤታችን ድንግል ማርያም ንጽህት ቅድስት ናት እመቤታችን ከጥንት አብሶ (ከውርስ ኃጢያት) ንጽህይት ነች ይህንንም ነቢዩ ኢሳይያስ “እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆን ገሞራንም በመሠልን ነበር” እንዳለት. ኢሳ.1:9 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተናገረ የእመቤታችን የማርያም ንፅህና ከመላእክትም ይበልጣል ብሏል በዚህም ምክንያት አምላክ ከእርሷ እንዲወለድ መረጣት ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስም ነስቶ ሰው ሆነ የፀሀይ መገኛም ስለሆነች ምስራቅ ተባለች፡፡

2.የትህትና
ትህትና ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ በድንግሊቱ ሕይወት ውስጥ ተገልጧል መልአኩ ወደእርሷ በመጣ ባበሠራትጊዜ “እነሆኝ የጌታ ባሪያ…” ነበር ያለችው ሉቃ.1:38 በእርግጥም እርሷ ይህንን ያለችው እናቱም አገልጋዩም ስለሆነች ነው፡፡አምላክንም ከጸነሰች በኃላ ወደ ኤልሳቤጥ ዘንድ ሄደች መንፈስ ቅዱስም ለኤልሳቤጥ የእመቤታችንን ክብር በገለፀላት ጊዜ በትህትና “የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆነኛል?”ብላለች ሉቃ143 እመቤታችን ወደኤልሳቤጥ የኄደችው አምላክን ከጸነስች በኃላ ነው በጣም አድካሚ ወደሆነው ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ የመጣቸው ፡፡ ከዚህ በኃላ ኤልሳቤጥም እስክተወልድ ድረስ ለሦስት ወራት ያህል በዚህ ተቀምጣለች፡፡ ሉቃ139-56፡፡  ለእርሷ የተሰጣት ድንቅ የሆነ ክብር ትህትናዋ ፈጽሞ አልቀነሰውም በፀሎቷም ጊዜ “የባሪያውን ትህትና ተመልክቶአልና… ”
በክብር የተሞላ የሥጋዌን ምስጢር ለማንም አለመናገሯ ደግሞ ሌላው ድንቅየ ትህትናዋ መገለጫ ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም በቤተመቅደስ የኖረች በቅስስናናበንፅህናነው፡፡አይሁድ ግን ከቤተመቅደስ እንድትወጣ በጠየቁ ጊዜ አልተቃወመችም እንደዚህም በአንድ ሰው ጠባቂነት ስር እንድትኖር በተደረገ ጊዜም አንዳችም የተቋውሞ አሳብ አላቀረበችም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አሰራር በድንግልና እናት እንድትሆን እግዚአብሔር ሲፈቅድ ሉቃ135 ሰፊ የውይይት አጀንዳ እንዲከፈት አልፈቀደችም ይልቁንም ባልተቀየረ ቃሏእንዲህ አለች እንጂ “እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ…” ሉቃ138 ይህን በማለቷ በመታዘዟም የእግዚአብሔር እናት ሆነች፡፡ እሜታችን ቅድስት ማርያም ወደ ግብጽ እንድትሰደድ በመልአኩ በኩል በታዘዘች ጊዜ በዝምታ ነበር የወረደችው፡፡ ከግብጽ ወደ ቅድስት ሀገር እንድትመለስ ይኸው ትእዛዝ ሲደርሳት በዝምታ ነበር የፈፀመችው፡፡ከቤተልሄም ወጥታ ወደ ናዝሬት በመሄድ በዚያ እንድትኖር በታዘዘች ጊዜም ጋር የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን ብላ ነበር የታዘዘችው፡፡እናታችን ያለምንም ውይይት በመታዘዝ ሕይወት ውስጥ ያለፈች የሰው ዘር ናት፡፡
3)የትዕግስት የጽናት ሕይወት
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆቿ በሞት የተለዩአት ገና የስምንት ዓመት ብላቴና ሳለች ስለሆነ ያደገችው ያለወላጅ ነው፡፡ይህ በመሆኑም ያለወላጅ የማደግን ችግር በጽናት ተቋቁማለች በቤተመቅደስ መኖርንም የጀመረችው ገና በሕፃንነት እድሜዋ በመሆኑ ብቸኝነትንም ተጋፍጣለች፡፡በአንድ ጠባቂ ሰው ጥላ ስር ለመኖር ከቤተመቅደስ ከወጣች በኃላም የድህነትን ህይወት ተቋቁማለች፡፡ “በዚህም የመውለጃዋ ወራት ደረሰ የበኩር ልጅዋንም ወለደች በመጠቅለያም ጠቀለለችው በእንግዶችም ማረፊያ ስፍራ ስላልነበረቸው በግርም አስተኛችው” ሉቃ27 ተብሎ እንደተጻፈ አንድያ ልጇን ክርስቶስንም ከወለደች በኃላ መከራን በጽናት ተቀብላለች በጠባቂዋ በዮሴፍ ቤት በነበረች ጊዜም የኃላፊነትን ቀንበር ተሸክማለች፡፡
ድንግል ማርያም ገና በ15 አመቷ ብላቴና ሳለች የግብጽን የደርሶ መልስ አድካሚ ጉዞ በጽናት ተወጥታለች፡፡ በዚያ ከልጇ ጋር ለሦስት አመት ከስድስት ወር በስስት ስትቀመጥ የግብፅ ጣኦታት በልጀዋ ፊት እየተሰበሩ ይወድቁ ስለነበር በትንቢተ ኢሳይያስ እንደተፃፈ ጣኦት አምላኪዎች ከአንዱ ከተማ ወደሌላው ከተማ ያሳድዷቸው ስለነበር ይህንንም በትዕግስት በጽናት ተቋቁማለች፡፡ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ በልጇ ላይ የወረደውን ስድብ እንግልት ግርፋትና ህማማተ መስቀል እየተመለከተች ከመሪር እንባ ጋር በጽናት ቆይታለች፡፡

ድንግሊቱ እነዚሁ ሁሉ መከራዎች ቢገጥማትም በልጇ የሚሆን ደስታዋን ስላላጣቸው በምሥጋና ፀሎቷ ውስጥ እንዲህ ብላለች“…መንፈሴም በአምላኬ በመድኋኒቴ ሐሴት ታደርጋለች” ብላለች ሉቃ147፡፡

4)የእምነትና የመቀበል ሕይወት

እርሷ ስለተቀበለቻቸው መከራዎች አንድ ጊዜ እንኳን ይህ ለምን ሆነ አላለችም፡፡ሄሮድስ ልጇን ለመግደል አውሬ ሆኖ በተነሳበት ጊዜና ወደግብጽ ስትሰደድ እንዲሁ አይሁድ ያን ሁሉ መከራ ሥቃይ ሲያደርሱባት በአባቱ በዳዊት ዙፋን ላይ ይነግሳል ለመንግስቱም ፍፃሜ የለውም ብሎ መልአኩ የነገረኝ ቃል ወዴት ደረሰ? ብላ አልተናገረችም ሉቃ132-33፡፡ እናታችን ቅዱስት ማርያም ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስን በድንግልና እንደምትወልደው አምናለች ይህም ተከናውኖላታል፡፡ ምንም እንኳን ልጃ ኢየሱስ ክርስቶስ በበረት ቢወለድም ስለእርሱ“…ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዘብሔር ልጅ ይባላል” ሉቃ135 ተብሎ በተነገራት የምስራች ቃል አምናለች፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ልጇ ሕማማተ መስቀል እንደሚገጥመውና በመስቀል ተሰቅሎ እንደሚሞትና ሞትን ድል አድርጎ እንደሚነሳ ስላመነች ይህንን በአይኗ ተመልክታለች፡፡ ማቴ28

5)ዝምታ ፀሎትና ተመስጦ
እናታችን በእግዚአብሔር ፈቃድ ቤተመቅደስ ውስጥ ስላደገች የብቸኝነትን የዝምታን በፀሎትና ተመስጦ ራሷን ጽሙድ በማድረግ በዚህ ተምራለች፡፡ እርሷ በልጅነቷ የወላጆቿን ፍቅርና እንክብካቤ ብታጣም ፍቅሯን ሙሉ ለሙሉ ለእግዚአብሔር በማድረግ አድጋለች በዚህም በብቸኝነት ለሚኖሩ ለባህታውያን ትልቅ ምሳሌ ነች፡፡

እርሷ ድንቅ ልጇን በወለደች ጊዜ ገና ብላቴና ነች ከእድሜዋ ጋር ሲነፃፀር ከህሊና በላይ የሆነ ድንቅ ተአምራት ተከባ ነበር እርሷ የመላእክትን የእረኞች የስብሰባስገልን(ከሩቅ ምስራቅ ሐገር የመጡ የጥበበኞች ሰዎችን ድንቅ ቃላት ምሥጋና ሰምታለች ቢሆንም ግን አንድም ጊዜ በኩራት አልተናገረችም በወንጌል የተፀፈው “… ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር”፡፡ ሉቃ219እና52 ይህ ይሁንእንጂ እናታችን መናገር በሚገባት ጊዜ ስትናገር የተናገረቻቸው ንግግሮች ለትውፊታዊ ስብከቶች ምንጮች ነበሩ፡፡ሐዋርያትንና ወንጌላውያን ባቀረቧቸው ዜናዎቻቸው ላይ ከእርሷ ብዙ እንደተማሩ ገልጠዋል በተለይ ፍቅሩ እግዚእ ዮሐንስ ከፃፈው ወንጌልም እንደምንረዳው ከእርሷ ስለምስጢረ ሥላሴ ጥልቅ ነገር እንደተማረ ያስታውቃል፡፡ ድንግል ማርያም ብቸኝነትን ፀጥታን ከጸሎት ከዜማ ከመዝሙራት መፃሕፍትን ከማንበብ ያነበባቸውን ጥቅሶች በተለይም መዝሙረ ዳዊትን በተመስጦ ውስጥ ሆና በቃሏ በመውጣት ሙሉ ጊዜዋን በዚህ ታሳልፍ ነበር፡፡ በእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘንድ ያለው ዝምታ ለእኛ ትምህርት ሰጪ ነው እናም እባካችሁ እርስዋን ጥቂት በመናገርና ብዙ በመጸለይ በተመስጦ ውስጥ በመቆየት እንምሰላት፡፡

6)ሌሎች የቅድስና ጠባዮቿ

እግዚአብሔር ወላጆቿን በሕጻንነቷ እድሜ ያጣችውን ድሀ ድንግል እናት አደርጎ የመረጠው በሕልውናዋ(በአኗኗርዋ) ከሴቶች ሁሉ የምትልቅ እናት ሊያደርጋት ስለወደደነው እርሷ በጠባዮቿ ከገንዘብ ብልጽግና የሚልቁልዩ ጠባያት አሏት፡፡ ቅድስና ንፅሕና ድንግልና መንፈሳዊ ዕውቀት ሌሎችን ማገልገልና ለሐዋርያት አባቶች ያሳየቻቸው መንፈሳዊ እናትነት ከዋና ዋና ጠባዮቿ መካከል ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ በረከቷ ጸንቶ ይደርብን !!! አሜን
48 viewsbisrat, 17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 18:53:15
31 viewsbisrat, 15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 18:53:00 #ጥር_2_ጻድቁ_አቤል_በወንድሙ_ቃየን_እጅ_ተገድሎ_ሰማዕትነት_የተቀበለበት_ዕለት_ነው።

አዳምና ሔዋን ለ7 ዓመታት በገነት ከኖሩ በኋላ ሲበድሉ እግዚአብሔር የሚያህል ጌታ ገነትን የምታህል ቦታ አጥተው ደብረ ቅዱስ ወደ ተባለ ቦታ ተሰደዱ፡፡ ከዚኽ ቦታ ኾነውም የገነት ሽታ እየሸተታቸው ይኖሩ ነበር፡፡ ወደ ገነት ግን መቅረብ አልተቻላቸውም፡፡ ሦስት ዓመት ሙሉም በጣም ያለቅሱና ያዝኑ ነበር፡፡ ከዚኽ በኋላ አዳም ሚስቱ ሔዋንን አወቃትና ቃየንና እኅቱን ሉድን ወለደች፡፡ ቀጥላም አቤልንና እኅቱን አቅሌማን ወለደች፡፡

ካደጉ በኋላም አቤል እረኛ ኾነ፤ ቃየን ደግሞ ገበሬ ኾነ፡፡ እረኛ ታውቃላችኁ ልጆች? ገበሬስ? እረኛ ማለት በግ፣ ከብት ወይም ፍየል የሚጠብቅ ልጅ ማለት ነው፡፡ ገበሬ ማለት ደግሞ መሬት አርሶ እኛ የምንበላውን እኽል የሚያመርት ነው፡፡ታድያ ልጆች፥ ከዕለታት በአንዱ ቀን አዳም ሚስቱን ሔዋንን ጠራትና፡- “እኅቴ ሔዋን ሆይ! ልጆቻችን እኮ አደጉ፡፡ ብናጋባቸው ምን ይመስልሻል?” አላት፡፡ እርሷም፡- “ወንድሜ አዳም ሆይ! እንዳልክ ይኹን፡፡ በሐሳብኅ እስማማለኹ እሺ” አለችው፡፡ከዚያ በኋላ “የቃየንን መንትያ ለአቤል፥ የአቤል መንትያ ደግሞ ለቃየን ትኹን” አሉ፡፡ ቃየን ግን ቀናተኛ ስለነበር “ከእኔ ጋር መንታ የኾነችው ሉድ ቆንጆ ስለኾነች ለእኔ ትኹን፡፡ የአቤል መንታ አቅሌማ ደግሞ ቆንጆ ስላልኾነች ለአቤል ትኹን” አለ፡፡ ቃየን አባቱንና እናቱን አልታዘዝም አለ፡፡

ከዚኽ በኋላ አዳም፡- “እንግዲያውስ መሥዋዕትን ሠዉና እግዚአብሔር መሥዋዕቱን የተቀበለለት ሉድን ያግባ” ብሎ መከራቸው፡፡ አቤልም በጣም ጨዋ፣ አስተዋይ፣ የዋኅና ታዛዥ ስለ ነበር እሺ ብሎ “ከእነዚኽ በጐች ንጹሕ የኾነውን ለምን አላቀርብም?” ብሎ አሰበ፡፡ ወዲያውኑም አቀረበ፡፡ ቃየን ግን ጥሩ ልጅ ስላልነበረ ከዘራው ስንዴ መርጦ ሳይኾን “እግዚአብሔር አይበላውም” ብሎ በንቀት እንክርዳድ የበዛበትን፣ ቆሻሻ የተቀላቀለበትን አቀረበ፡፡ እግዚአብሔር ግን የአቤልን መሥዋዕት ብቻ ተቀበለና የቃየንን ሳይቀበልለት ቀረ፡፡ 

ይሔኔ ቃየን በወንድሙ በአቤል ላይ በጣም ቀና፡፡ “እግዚአብሔር አቤልን እንጂ እኔን አይወደኝም” ብሎ ተቈጣ፡፡ እግዚአብሔርም ቃየንን ጠርቶ “ምነው ፊትኅ ጠቆረ? መልካም ብታደርግስ እንደ ወንድምኽ ደጉ አቤል ይበራ ነበር” አለው፡፡ ቃየን ግን በቅን ልቦና “አምላኬ ሆይ! አዎን መልካም ሥራ አልሠራኹም፤ ከእንግዲኅ ምን ማድረግ ይገባኛል?” አላለም፡፡ እንዲያውም ቁጣው እየበረታበት መጣ፡፡

ከዚኽ በኋላ ቃየን እያዘነ ሲሔድ ሰይጣን መንገድ ላይ አገኘውና “ቃየን ምነው እያዘንክ ትሔዳለኅሳ?” አለው፡፡ ሰይጣን ወዳጅ መስሎ የቀረበው ሊያታልለው እንጂ አዝኖለት አይደለም፡፡ ከዚኽ በኋላ ቃየን “እኔ ያላዘንኩ ማን ይዘን? አባቴ አዳልቶ ቆንጆዋን እኅቴን ለአቤል ሰጠው፡፡ እግዚአብሔርም አዳልቶ መሥዋዕቴን ሳይቀበልልኝ ቀረ” ብሎ ለሰይጣኑ ነገረው፡፡ ሰይጣንም “ወንድምህን ግደለውና አንተ ቆንጆዋን አግብተኽ ትኖራለኽ” ብሎ ክፉ ምክር መከረው፡፡ ቃየንም “ለካ እንደዚኽም ይቻላል” ብሎ በሰይጣን ሐሳብ ተስማማ፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀንም ወንድሙን አቤልን ጠራውና “ና ወደ ሜዳ ሔደን እንጫወት” አለው፡፡ ከተጫወቱ በኋላ ራባቸውና ምሳ ለመብላት ተቀመጡ፡፡ ምሳቸውን ከበሉ በኋላ ውኃ ለመጠጣት አብረው ወደ ወንዝ ወረዱ፡፡ መዠመሪያ ቃየን ጠጣና አቤልን ጠጣ አለው፡፡ አቤልም ለመጠጣት ጐንበስ ሲል ቃየን ትልቅ ድንጋይ አነሣና አቤልን ጥር 2 ቀን  በድንጋይ ፈጥፍጦ ገደለው፡፡ 

ሞት ለመዠመሪያ ጊዜ በሰው ልጆች የታየው ቃየን አቤልን ከገደለው በኋላ ነው፡፡ በዚኽም ጊዜ እግዚአብሔር በደመና ውስጥ ኾኖ “ቃየን ቃየን ወንድምኅ አቤል ወዴት ነው?” አለው፡፡ ቃየን ግን በትዕቢት ኾኖ “እኔ ምን አውቃለኹ፤ እኔ የወንድሜ የአቤል ጠባቂው ነኝን?” ሲል መለሰ፡፡ እግዚአብሔርም መልሶ “እንግዲኽ ጠባቂው ካልኾንኅ ስለምን ገደልከው? አኹንም ባለ ዘመን ኹሉ በምድር ኹሉ ላይ ድንጉጥና ተቅበዝባዥ ኹን” በማለት እግዚአብሔር ቃየንን ረገመው፡፡ ከዚያን ጊዜ ዠምሮ ቃየን በጣም ፈሪ፣ ሰዎችን የሚሸሽ፣ የሚጨነቅ፣ ባጠፋው ጥፋት እግዚአብሔርን የሚያፍር ኾኖ ኖረ፡፡
 
ምንጭ :- ኦሪት ዘልደት አንድምታ

“የኃጥአን መሥዋዕት በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊ ነው፡፡ የቅኖች ጸሎት ግን በርሱ ዘንድ የተወደደ ነው” /መጽሐፈ ምሳሌ 16፡8/፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ አቤል ጸሎት ይማረን!!! አሜን
32 viewsbisrat, 15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 16:59:45
73 viewsbisrat, 13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 16:58:30 #ጥር_1_ቅዱስ_እስጢፋኖስ_የተወለደበት_እና_የሰማዕትነት_አክሊል_የተቀበለበት_ዕለት_ነው ።

#እስጢፋኖስ፦የስሙ ትርጉም በግሪክ ቋንቋ አክሊል ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው፡፡

አባቱ ስምኦን፣ እናቱ ሃና ይባላሉ፡፡ የተወለደው - ጥር 1 ቀን በእስራኤል ሃገር ውስጥ በብፅዓት / በስለት/ ነው፡፡ ልዩ ስሟ ሐኖስ በተባለ ቦት ተወለደ ከመጥምቁ ዮሐንስ እግር ሥር በመሆን ተምሯል፡፡

በደሙ የመሠረታት የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በጽርሐ-ጽዮን ከመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከተቀበለች በኋላ የትንሣኤውን ወንጌል ለትውልድ ማድረስ ጀመረች፡፡ ወንጌል እየተስፋፋ አማኞች እየበዙ መጡ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት የሚያግዟቸው ሰባት ጠቢባን ወጣቶችን መርጠው የዲቁና ሥልጣን ሰጡአቸው፡፡
ከተሾሙት ዲያቆናት መካከል ቅዱስ እስጢፋኖስ አንዱ ነው፡፡ ሐዋ. 6÷5. ቅዱስ እስጢፋኖስ ጥቅምት 17 ቀን የዲያቆናት አለቃ ሆኖ ሊቀ ዲያቆናት ተብሏል፡፡

ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፡፡ ከግሪክ አገር የመጡ አይሁድ በተከራከሩት ጊዜ በመንፈስና በጥበብ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም ዳኞች በተሰየሙበት ሸንጎ ፊት አቅርበው በሐሰት ከሰሱት፤ ሸንጎውም በድንጋይ እንዲወገር ፈረደበት፡፡ እስጢፋኖስ ግን በታላቅ ኃይልና በብዙ መረዳት ከአባቶቻቸው ታሪክ ተነሥቶ የዓለም መድኃኒት የሆነውን ክርስቶስን ሰበከላቸው፡፡ ጥላውን ከአካሉ ጋር እያጋጠመ ወደ ፍጹማን ጥበብ በጽድቅ ቃል መራቸው፡፡ አይሁድ በጣም ተቆጡ፤ ሁሉም በአንድነት ሆነው በድንጋይ ወገሩት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰውነቱ ቆስሎና ዝሎ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ባነሣ ጊዜ የልዑልን ክብር ተመለከተ፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቱ ቀኝ ቆሞ አየ፡፡ ሐዋ. 7÷55፡፡

ቅዱስ አሰስጢፋኖስ “እነሆ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅ (ኢየሱስ ክርስቶስ) በአባቱ ቀኝ ቆሞ አያለሁ” አላቸው፡፡ አይሁድ ግን ልበ-ደንዳኖች (የማይራራ ጨካኝ ልብ ያላቸው) ስለሆኑ እስጢፋኖስን ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው ደበደቡት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰውነቱ ደከመ፤ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በደረሰች ጊዜ በሞት ጣር ሆኖ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው፤ ነፍሴን ተቀበል” ብሎ ጸለየ፡፡ ነፍሱንም ለታመነው ፈጣሪ አደራ ሰጥቶ ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡

የሰማዕትነት ሕይወትን በመጀመሩ ስለ ክርስቶስ ፍቅር መራራ ሞትን በመታገሡ ቀዳሜ ሰማዕት ተብሏል፤ የቤተክርስቲያን የመጀመሪያው ሰማዕት ነውና፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን እኛንም በሰማዕቱ ጸሎት ይማረን አሜን !!!
74 viewsbisrat, 13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ