Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-01-28 19:24:03 ወደፊት የምንዳስሳቸው መፅሐፍት
፩ መድሎተ ፅድቅ
፪ መጽሐፈ ሃዊ
፫ ገድለ ሃዋርያት
፬ ገድለ ሠማዕታት
፭ የብርሃን እናት
፮ ነገረ ክርስቶስ በውዳሤ ማርያም
......ሌሎችን በቀጣይ እንመለስባቸዋለን
55 viewsእሱበ ዐይናለም, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 22:08:56
67 viewsእሱበ ዐይናለም, 19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 20:14:36
65 viewsbisrat, 17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 20:13:35 #ጥር_21_የእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_የዕረፍቷ_መታሰቢያ_ዕለት_ነው ።

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞት ነገረ ማርያም፣ ስንክሳር እና ተኣምረ ማርያም እንደሚያስረዱት፤ ጥር 21 ቀን ዐርፋለች፡፡ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የሐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ16 ዓመተ ዓለም ከኢያቄም እና ከሐና ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሣ ፤ በ15 ዓመተ ዓለም ግንቦት 1 ቀን ፤ በሦስት ዓመቷ ታኅሣሥ 3 ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ገባች ፤ ለ12 ዓመታት በቤተ መቅደስ ስታገለግል ቆይታ ፤ በ15 ዓመቷ የዓለሙን መድኃኒት በቤተ ልሔም ወለደች ፤ ለ33 ዓመት ከ3 ወር ያህል ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ከኖረች በኋላ ፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ እናቱን ‹‹እነኋት እናትህ›› ብሎ ለዮሐንስ ወንጌላዊ አደራ ሰጣት ፤ እመቤታችን በቅዱስ ዮሐንስ ቤትም ለ15 ዓመታት ያህል ቆየች፡፡ ከዚህም በኋላ ስላለው የእመቤታችን የሕይወት ታሪክ በመቀጠል እንመለከት፡-

እመቤታችን 64 ዓመት በሆናት ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ‹‹ከኀዘን ወደ ደስታ ትሔጂ ዘንድ ሙቺ›› አላት ፤ እርሷም ‹‹ልጄ ሆይ አንተን ወልጄ ያንተ እናት ሆኜ እኔ እንዳት ልሙት›› አለችው፡፡

ጌታችን በሲኦል ያለ 99,999 አሳያት ፤ እመቤታችንም የእነዚህን ነፍሳት መከራ ልቅሶና ጭንቀት ስትመለከት “አስታረቀሽ አማልደሽ አድኝን” የሚለውን ጩኽታቸውን ስትሰማ ፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ ማርልኝ›› አለችው፡፡ ጌታም መልሶ ‹‹እኔ የአዳምን ልጆች ያዳንኩት መከራን ተቀብዬ ተሰቅዬ ሞቼ ነው ፤ አንቺም ለእነዚህ ነፍሳት ካልሞትሽላቸው ወደ ገሃነም ይገባለ›› አላት፡፡

እመቤታችንም ለፍጥረታት ካላት ፍቅር የተነሣ ‹‹እነዚህ ነፍሳት ወደ ገሃነም ከሚወርደ እኔ ሰባት ጊዜ ልሙት›› በማለት ያለ መከራ ያለ ጭንቅ ጥር 21 ቀን በ49 ዓ.ም ነፍሷ ከሥጋዋ ተለየች፡፡ ሐዋርያት የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን እረፍት በሰሙ ጊዜ ጊዜ ፈጽመው አዘኑ ፤ ስለ ሰማያዊ ምሥጢር የምትነግራቸው ፤ እንደ እናት የምትንከባከባቸው እርሷ ነበረችና ኀዘናቸው ፍጹም ነበረ፡፡ በሥርዓቱም መሠረት እመቤታችንን በጨርቅ ገንዘው በአልጋ ላይ አድርገው እያለቀሱ ሉቀብሯት ጉዞአቸውን ጀመሩ፡፡ አይሁድ ድንግል ማርያም ሞተች የሚለውን ዜና በሰሙ ጊዜ ፤

‹‹አስቀድሞ ልጇ ከሞተ በኋላ ተነሥቷል ተብሎ ሀገር ሲታወክ ነበረ ፤ አሁንም ደግሞ እርሷም ሞታ ተነሣች ተብሎ በሀገሩ ሁሉ ሉወራ ነውና ቶሎ ብለን ሥጋዋን እናቃጥለው፡፡›› ብለው ተስማምተው ፤ ከመካከላቸው አካለ የገዘፈ ፈርጣማ የሆነ ታውፋንያ የተባለውን ሰው ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ እንዲያቃጥል ላኩት፡፡ እርሱም በተላከው መሠረት እመቤታችን ያረፈችበትን አልጋ በእጆቹ በያዘ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ እጆቹን ቆረጠው ፤ እጆቹም በአልጋው ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ ፤ ታውፋንያም “በድያለሁ ማሪኝ” በማለት መጮኽ ጀመረ ፤ በዚህ ሰአት እመቤታችን አማልዳው ፤ ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ የታውፋንያ እጆች እንደቀድሞው ሆኑ፡፡ የእግዚአብሔርም መልአክ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስንና የእመቤታችንን አካል ሰውሮ ወደ ሰማይ ወሰደው ፤ የድንግልንም ሥጋ በዕፀ ሕይወት ሥር አሰቀመጠው፡፡ 

ቅዱስ ዮሐንስም ወደ ቅዱሳን ሐዋርያት ተመልሶ የእመቤታችን አካል የት እንዳረፈ ቢነግራቸው እነርሱም ዮሐንስ የእርሷን የሥጋዋን መቀበር አይቶ እኛ ሳናይ ብለው መንፈሳዊ ቅንዓት አድሮባቸው ሱባኤ ገብተው  በ14ኛው ቀን ነሐሴ 14 እለተ እሐድ ፤ አምላካችን የእመቤታችንን በድን ሥጋ ሰጣቸው ፤ እነርሱም በደስታ ተቀብለው በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ በሚያስተምርበት ሀገር አስተምሮ አጥምቆ በደመና ላይ እየተጓጓዘ ሲመለስ ፤ ነሐሴ 16 ቀን ማክሰኞ እለት እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ስታርግ አግኝቷት የተገነዘችበትን ሰበን ይዞ ወደ ሐዋርያት ሄዷል። 

እንደማያውቅ ሆኖ ቅዱሳን ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ነገር ጠየቃቸው ጥር 21 ማረፏን ነሐሴ 14 ደግሞ መቃብሯን ነገሩት እርሱም‹‹እንዴት ሞት በጥር ፤ በነሐሴ መቃብር ይሆናል? እኔ አላምንም›› አላቸው እነርሱም ያምናቸው ዘንድ ወደ ጌቴሴማኒ የመቃብር ሥፍራ ወስደው ቢያሳዩት ምንም ነገር የለም ፤ ሁሉም ተመለከቱ አንዳች ነገር አላገኙም ፤ በደነገጡም ጊዜ ፤ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ‹‹አትደንግጡ እመቤታችን ተነሥታ ዐርጋለች ፤ ሥጋዋን ካላሳያችሁኝ አላምንም ያልኩት ፤ እንዳትጠራጠሩኝ ነው›› ብሎ የተገነዘችበትን ጨርቅ አውጥቶ አሳያቸው ለበረከት እንዲሆናቸውም ሁሉም ተከፋፈሉት፡፡

ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን እኛንም በእመቤታችን ጸሎት ይማረን በረከቷ ይደርብን!!! አሜን
63 viewsbisrat, 17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 19:29:12
66 viewsbisrat, 16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 19:27:16 #ርዕሰ_ገዳማውያን_አቡነ_ጳውሊ_በመጨረሻው_ዘመን_ስለሚነሱ_መነኮሳት_ይህን_ብለው_ነበር:-

<<...ሀሳሲያነ ሢመት (ሹመት ፈላጊዎች)፣ መፍቀሪያነ ንዋይ (ገንዘብ የሚወዱ) እና ከመኳንንትም ጋር በጥዋት ማዕድ የሚቀመጡ በፍጻሜ ዘመን የሚነሡ...>>

ሙሉውን ታሪክ እነሆ:-

አባ እንጦንስ የአባ ጳውሊን ዝና ሰምተው እነርሱን አግኝተው ለመጎብኘት ጥረት ካደረጉ በኋላ በዓታቸውን ፈልገው አግኙ በብዙ ምልጃም በሩን ከፍተውላቸው ተገናኝተው ሁለቱም አብረው ከጸለዩ በኋላ ስለ ተጋድሎአቸውና ስለ አኗኗራቸው ተወያዩ፡፡

የታዘዘው ቁራ ሌላ ጊዜ የጳውሊን ምግብ የሚያመጣው ግማሽ እንጀራ ነበር ዛሬ ግን ሙሉ እንጀራ ስላመጣላቸው ሁሉቱም ቅዱሳን ደስ ተሰኝተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ አባ እንጦንስም ሥጋ ወደሙን ከወዴት እንደሚቀበሉ አባ ጳውሊን ሲጠይቋቸው በየሳምንቱ ቅዳሜና እሁድ መልአክ እያመጣ ሥጋ ወደሙን እንደሚያቀብላቸው ነገሯቸው፡፡

ከዚህም በኋላ አባ እንጦንስ ለአባ ጳውሊ እንዲህ ዓይነት ጥያቄ አቀረቡላቸው:-‹‹ይህ አስኬማ በምድር ላይ ይበዛ እንደሆነ ወይም አለመብዛቱን ትነግረኝ ዘንድ እሻለሁ›› ፡፡ አባ ጳውሊም ወደፊት ስለሚመጡ መነኮሳት በመጸለይ ወደ ሰማይ ካዩ በኋላ በመጀመርያ ፈገግ አሉ፡፡ አባ እንጦንስም ‹‹ምን አየህ?›› ቢሏቸው አባ ጳውሊ ‹‹ነጫጭ ርግቦች በጠፈር መልተው አንተ እየመራሃቸው ተከትለውህ ሲሄዱ አየሁ›› አሏቸው፡፡ ‹‹ይህስ ምንድን ነው?›› ቢሏቸው ‹‹እሊህማ በዚህ በቆቡ የምትወልዳቸው ንጹሐን ጻድቃን ልጆችህ ናቸው›› አሏቸው፡፡ ‹‹ሁለተኛ አመልክትልኝ›› አሏቸው፡፡

ጳውሊም ካመለክቱ በኋላ አዝነውና ተከፍተው ተመለከቷቸው፡፡ ‹‹ምነው?›› ቢሏቸው ‹‹በክንፋቸው ጥቁር ተቀላቅሎባቸው አየሁ›› አሉ፡፡ ‹‹ምንድን ናቸው?›› ቢሏቸው ‹‹ጽድቅና ኀጢአት እየቀላቀሉ የሚሠሩ ልጆችህ ናቸው›› አሏቸው፡፡ እንጦንስም ካዘኑ በኋላ ‹‹ሦስተኛም አመልክትልኝ›› አሏቸው፡፡

አባ ጳውሊም ለሦስተኛ ጊዜ ካመለከቱ በኋላ በድንጋጤ ቃላቸውን ከፍ አድርገው ጮኹ፡፡ አባ እንጦንስም ‹‹ምነው?›› ቢሏቸው አባ ጳውሊ እንዲህ አሉ፡- ‹‹ነገር ግን በመጨረሻ ዘመን የሚነሡቱ እንደ ቁራ ጠቁረው አየሁዋቸው›› አሉ፡፡ ‹‹ምንድን ናቸው?›› ቢሏቸው ‹‹ሀሳሲያነ ሢመት (ሹመት ፈላጊዎች)፣ መፍቀሪያነ ንዋይ (ገንዘብ የሚወዱ) እና ከመኳንንትም ጋር በጥዋት ማዕድ የሚቀመጡ በፍጻሜ ዘመን የሚነሡ ኀጥአን ልጆችህ ናቸው›› አሏቸው፡፡ ይህን ጊዜ አባ እንጦንስ ‹‹ያለ ንስሓ ባይጠራቸው እስኪ አመልክትልኝ›› አሉ፡፡ አባ ጳውሊም አመለከቱ ነገር ግን የዚህ ምላሽ አልመጣላቸውም፡፡

የርዕሰ ባሕታውያን አባ ጳውሊና የርዕሰ መነኮሳት አባ እንጦንስ በረከትና ረድኤት ጸንቶ ይደርብን!!!
113 viewsbisrat, 16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 19:19:51
64 viewsbisrat, 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 19:18:52 #ጥር_18_ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_አጽሙ_የተበተነበት_ዕለት_ነው ።

የፋርሱ ፀሐይ ፣የቤሩቱ ኮከብ፣ የልዳው ሰማዕት ፣የኢትዮጵያ ገበዝ ቅዱስ ጊዮርጊስ የተወለደው ከአባቱ ዘረንቶስ (አንስጣስዮስ) እና ከእናቱ ቴዎብስታ የድሮው ፋርስ ግዛት ፍልስጥኤም (ልዳ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቹ ክርስትናን ጠንቅቀው አስተምረውት አባቱ ይሞታል:: ቅዱስ ጊዮርጊስ ፳ ዓመት ሲሞላው የአባቱን ስልጣን እጅ ለማድረግ ሲሔድ የቢሩት የሊባኖስ ሰዎች ዘንዶ/ደራጎን ሲያመልኩ አገኛቸው:: እርሱ ግን የከተማውን ሕዝብ አስተምሮ: አሳምኖ: ደራጎኑንም በፈጣሪው ኃይል ገድሎ መንገዱን ቀጥሏል::

√ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዱድያኖስና ፸ 70 ነገሥታት ዘንድ ሲደርስ ክርስቶስ ተክዶ ለጣዖት ይሠገድ ነበር:: በዚያች ሰዓት ድንግል እመቤታችን ወደ ሰማዕቱ መጥታ መከራውንና ክብሩን ነገረችው:: እርሱም በክርስቶስ ስም መሞት ምርጫው ነበርና ከእመቤታችን ተባርኮ ወደ ምስክርነት አደባባይ (ዐውደ ስምዕ) ደረሰ።

√ከዚያም ለተከታታይ ፯ 7 ዓመታት ብዙ ጸዋትወ መከራዎችን ተቀበለ፣ ፫ 3 ጊዜ ሞቶ ፫ 3 ጊዜ ተነሳ:: ከሰው ልጅ የተፈጥሮ ትዕግስት በላይ የሆነ ስቃይን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በመቀበሉ የሰማዕታት አለቃቸው: ፀሐይና የንጋት ኮከብ በሚል ይጠራል:: “ተውላጠ ጻማሁ ወሕማሙ: ዘተለዐለ ሞገሰ ስሙ” እንዲል መጽሐፍ::

√ ከ፯ ዓመታት መከራ በኋላም ከብዙ ተዓምራት ጋር ተሰይፎ ደም: ውሃና ወተት ከአንገቱ ፈሷል:: ፯ 7 አክሊላትም ወርደውለታል::

” ዝርወተ ዓጽሙ “ ይህቺ ዕለት ማለትም ጥር ፲፰18 ለሰማዕቱ ‘ዝርወተ አጽሙ’ ትባላለች:: በቁሙ ‘አጥንቱ የተበተነበት’ እንደ ማለት ነው::

ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ላይ ሰማዕታት የዚህን ዓለም ጣዕም ናቁ ስለእግዚአብሔር ክብርና ስለ መንግስተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሱ እንዲል ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: ፸ 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ::

√ በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት። ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት። ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት። በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት:: “ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ” እንዲል:: (ምቅናይ)

√ እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ “ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት” የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይህቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው:: ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና “በክርስቶስ እመኑ” ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው፣ ፸ 70ው ነገሥታት ግን አፈሩ።
የሰማዕታት ሞገሳቸው የሆነ ታላቅና ክቡር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ፯ ዓመታት ስቃይ በኋላ ሰማዕት ሆኗል::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ የእመቤታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት፤የጻድቃን የሰማዕታት ተራዳኝነት አይለየን አሜን።
142 viewsbisrat, 16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 19:09:44
93 viewsbisrat, 16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 19:07:49 እግዚአብሔር አምላካችን የሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣን በረከታቸውንና ረድኤታቸውን ያድለን!!
81 viewsbisrat, 16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ