Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Choleraupdate
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.37K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2024-04-08 21:52:23
" ባለፉት 9 ወራት በተፈፀመ ስርቆት 22 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ወድቀዋል " #EEP

ባለፉት 9 ወራት በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ሽቦ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ #ስርቆት 22 ምሰሶዎች መውደቃቸውን እና ከዚህ ውስጥ ሰባቱ በሰሜን ምዕራብ ሪጂን በተፈፀመ ስርቆት የወደቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል።

ባለፉት 9 ወራት በሁሉም ሪጂኖች በሚገኙ የኃይል ማስተላለፈያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የተለያየ መጠን ያለው ስርቆት እንደተፈፀመ ሲነገር በስርቆት ምክንያት ከወደቁ ምስሶዎች በተጨማሪ ከመሬት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዙ እና በሌሎች ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ደግሞ 13 ምሰሶዎች መውደቃቸው ተጠቁሟል።

እየተባባሰ የመጣው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች አካላት ስርቆት በኦፕሬሽን ሥራው ላይ ፈተና እየሆነ ይገኛል ሲባል የኦፕሬሽንና ጥገና ኃላፊዎች ችግሩ ከመደበኛ ሥራቸው ይልቅ በአስቸኳይ የጥገና ሥራዎች ላይ እንዲያተኩሩ እያስገደዳቸው ስለመሆኑ አመልክተዋል።

ወንጀሎቹን ለመከላከል የተለያዩ ሥራዎች ቢከናወኑም ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ከተቋሙ አቅም በላይ እየሆነ መምጣቱን ነው ኃላፊዎቹ ያነሱት። ችግሩን ለመፍታት ተቋሙ ከከፍተኛ የመንግስት አካላት ጋር በመወያየት ዘላቂ የሆነ መፍትሔ ማስቀመጥ ይኖርበታል ብለዋል። የተንሰራፋው ስርቆት ኃይል ከማቆራረጥ ባለፈ ተቋሙን ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረገው እንደሚገኝም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
24.7K views18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 20:01:09
የኬንያው ፕሬዝዳንት ሩቶ የስራ ማቆም አድማ ላይ ያሉ የህክምና ባለሙያዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ ጥሪ አቀረቡ

በኬንያ ደሞዝ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ይጨመርልን በማለት የስራ ማቆም አድማ ላይ ያሉ የህክምና ባለሙያዎች ወደ ስራቸው እንዲመለሱ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጥሪ አቀረቡ፡፡    
                                                                          
ፕሬዝዳንቱ 1500 አዲስ ዶክተሮችን እንደሚቀጠሩ ቃል የገቡ ሲሆን ነገር ግን ሀገሪቱ እየከፈለችው ካለው ከፍተኛ የደሞዝ ክፍያ አኳያ ለህክምና ባለሙያዎቹ የደሞዝ ጭማሪ ማድረግ እንደማይችሉ አሳውቀዋል፡፡

ከ700 በላይ የህክምና ባለሙያዎችን የወከለው የኬንያ ህክምና ባለሙያዎች ህብረት ከመጋቢት 6 ጀምሮ በሀገሪቱ አዲስ የህክምና ባለሙያዎች እንዲቀጠሩ፤ ደሞዝ እንዲጨመር እና ተያያዥ ጥያቄዎች እንዲመለሱ ግፊት ለማድረግ የስራ ማቆም አድማ ላይ መሆናቸው ነው የተገለጸው፡፡

@TikvahethMagazine
28.0K viewsedited  17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 18:47:17
#Vote

"ጥበብ እንደ የፈውስ መንገድ" (Art As path to Healing) በሚል ርዕስ በሪድም ዘ ጀነሬሽን አዘጋጅነት በትግራይ ክልል በተዘጋጀውና 59 ታዳጊዎችና ወጣት ሰአልያን በ10 ቡድኖች ያሳተፈው የሥዕል ውድድር ተመልካቾች ድምጽ እንዲሰጡበት ቀርቧል።

እስከ ሐሙስ ሚያዝያ 3 ድረስ ክፍት በሚሆነው የድምጽ አሰጣጥ ወጣቶቹ እና ታዳጊዎቹ የሰሯቸውን ሥዕሎች በሚከተለው ሊንክ በመግባት ሥራቸውን በማየት መምረጥ ትችላላችሁ።

ለመምረጥ https://redeem.tikvahethiopia.net/ ይጠቀሙ።

@TikvahethMagazine
27.9K viewsedited  15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 18:09:46
በመዲናዋ ትክክለኛ የመንገድ አጠቃቀም ያልተከተሉ ከ 700 በላይ እግረኞች በገንዘብና ማህበራዊ አገልግሎት ተቀጡ

የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመት ባለስልጣን በከተማዋ ከመጋቢት 13 ጀምሮ ትክክለኛ የመንገድ አጠቃቀም ያልተከተሉና ደንብ የተላለፉ እግረኞችን እየቀጣ ሲሆን እስካሁን 777 እግረኞች የገንዘብ እና የማህበራዊ አገልግሎት የመስጠት ቅጣት እንደተቀጡ ኢፕድ ዘግቧል።

በመቆጣጠሪያ ደንብ መሰረት እግረኞች ጥፋት ሲያጠፉ የሚጣለው ቅጣት ምን ይመስላል ?

ተገቢውን ጥንቃቄ ሳያደርግ መንገድ ያቋረጠ፤ ለተሸከርካሪ በተፈቀደ መንገድ ላይ ያለ በቂ ምክንያት የቆመ ወይም የተጓዘ ብር 40፤

እግረኛ መንገድ በሌለበት ቀኝ ጠርዙን ይዞ የተጓዘ፤ ለእግረኛ መንገድ ተብሎ ከተከለለ ውጭ የተጓዘ ብር 40 ይቀጣል።

ለእግረኛ መንገድ ላይ ንግድ ያከናወነ ወይም ቁሳቁስ ያስቀመጠና በእግረኞች እንቅስቃሴ እንቅፋት የሆነ ብር 80፤

በብረትም ሆነ በግንብ ተለይተው የታጠሩ መንገዶችን ዘሎ ያቋረጠ፤ ጆሮ ማዳመጫ የተለያዩ ድምጾችን እያዳመጠ መንገድ ያቋረጠ ብር 80፤

"ለእግረኛ ክልክል ነው" የሚል ምልከት ባለበት መንገድ ወይም እግረኛ እንዳያቋርጥ በተከለከለበት የማሳለጫ ወይም ቀለበት መንገድ ያቋረጠ ብር 80 ይቀጣል።

እነዚህን ጥፋቶች አንዱን ፈጽሞ ክፍያ መፈጸም ያልቻለ ወይም ያልፈለገ ማንኛውም እግረኛ ተመጣጣኝ የሆነ የማህበራዊ አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል።

በማስፈጸሚያ መመርያው መሰረት የ40 ብር ቅጣት የ30 ደቂቃ ማህበራዊ አገልግሎት ፤ ባለ 80 ብር ቅጣት የ1 ሰዓት ማህበራዊ አገልግሎት ቅጣት የሚያስጥል መሆኑ ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine
26.7K viewsedited  15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 18:09:28
የስብሰባ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ መኮንኖቸች ማህበር (PHOA-E) 11ኛ  ዓመታዊ ጉባኤውን ሚያዝያ 4-5 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢኒንስቲዩት (EPHI) አዳራሽ ያካሂዳል።

በጉባኤው ላይ የጤና ሚኒስቴር ፣ የጤና ቢሮ ፣ የዩኒቨርስቲ መምህራን ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች ፣ ከተለያዩ የጤናና የምርምር ተቋማት የተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች ይሳተፉበታል ተብሏል።

@TikvahethMagazine
22.6K views15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 18:08:49
ከ7 እስከ 18 ለሆኑ ልጆች የኦንላይን  ኮዲንግ  ስልጠና

ስልጠና April 13 , 2024 ቅዳሜ ይጀምራል።

ከ7 እስከ 13 ለሆኑ ህጻናት የ6 ሳምንታት የscratch ስልጠና( ጌም እና አኒሜሽን እየሰሩ ነው ሚማሩት)።

ከ14 እስከ 18 ለሆኑት የ website ስልጠና ለ 2 ወር።

የምስክር ወረቀት ያገኛሉ

ክፍያ ለ6 ሳምንት ፕሮግራም 2500 ብር ነው።
ክፍያ ለ 2 ወር ፕሮግራም 3500 ብር ነው።

በቴሌግራም መረጃ ለማግኘት ያግኙን
@koderlabtrainingcenter ወይም በ 0940121072 ይደውሉ።

ይህንን ሊንክ በመጠቀም ሬጅስተር ያርጉ።
https://forms.gle/J3CeN5XE4vQW3MF49
23.1K views15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 16:13:51
የአፍሪካ ኅብረት ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ የዘር ማጥፋትና የጅምላ ጭፍጨፋን ለመከላከል ልዩ መልዕክተኛ ሾመ

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት የዘር ማጥፋት ወንጀል እና ሌሎች ጅምላ ጭፍጨፋዎችን ለመከላከል ሴኔጋላዊውን አዳማ ዲዬንግ የመጀመሪያ የአፍሪካ ህብረት ልዩ መልዕክተኛ አድርገው ሾመዋል።

ልዩ መልዕክተኛው የተሾሙት በአፍሪካ አህጉር የጥላቻ እና የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን ለመዋጋት የተያዘውን የህብረቱን አጀንዳ ለማስፈፀም ሲሆን ዲዬንግ በቀድሞው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ባን ኪሙን የጅምላ ጭፍጨፋ መከላከል ልዩ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል ተብሏል።

@TikvahethMagazine
25.3K views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 15:20:30
#ጥቆማ

የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓይን ህክምና ክፍል እና ኤች.ሲ.ፒ ኪዩር ብላይንድስ ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር ከሚያዝያ 7 እስከ ሚያዝያ 11 ፥ 2016 ዓ/ም ድረስ ለ 5 ተከታታይ ቀናት ለ 450 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህሙማን ነፃ ህክምና እንደሚሰጥ አስታውቋል።

ስለሆነም የህሙማን ቅድመ ልየታ ስራ ከፊታችን ሐሙስ ሚያዝያ 3 ፥ እስከ 4 - 2016 ዓ.ም በሆስፒታሉ ውስጥ የሚከናወን ሲሆን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህመም ያለባችሁ ታካሚዎች በተጠቀሱት የቅድመ ልየታ እና የህክምና ቀናት በሆስፒታሉ ውስጥ በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ጥቆማ ቀርቧል።

አድራሻው አዲስአበባ ፤ ጉለሌ ክ/ከተማ ፤ ወረዳ 1፣ ከሽሮሜዳ ወደ ቁስቋም በሚወስደው መንገድ ላይ ሲሆን ታካሚዎች ለበለጠ መረጃ በሆስፒታሉ ነፃ የስልክ መስመር 998 ላይ መደወል ይችላሉ ተብሏል።

@TikvahethMagazine
26.5K viewsedited  12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 16:39:54
አንድ የታሪክ ተመራማሪ በመቅደላ ጦርነት የተሰረቁት የአፄ ቴዎድሮስ አልባሳት የት እንዳሉ ለማወቅ እየጣሩ ነው ተባለ

በእንግሊዝ አንድ የታሪክ ተመራማሪ ከ156 ዓመታት በፊት የተሰረቁት የዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ አልባሳት የት እንዳሉ ለማወቅ እየጣሩ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።

ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዝ ወረራ ወቅት እጅ አልሰጥም ብለው መቅደላ ላይ የራሳቸውን ሽጉጥ ጠጥተው ከሞቱ በኋላ ለብሰውት የነበረው የክብር ካባ እና የአንገት ልብስ ከአስክሬናቸው ላይ ተገፍፎ ተወስዷል።

አልባሳቱ ወደ እንግሊዝ ከተወሰዱ በኋላም በስታሊይብሪጅ፣ ስታምፎርድ ፓርክ ሙዚየም ውስጥ ተቀምጠው እንደነበር ሲገለፅ ሙዚየሙ በ1950ዎቹ ከፈረሰ በኋላ ግን እነዚህ ጥንታዊ ቅርሶች የት እንዳሉ አይታወቅም ተብሏል።

በጉዳዩ ላይ መጽሐፍ የጻፉት ሔቨንስ የተባሉት የታሪክ ተመራማሪ እንደሚሉት በመቅደላ ጦርነት ወቅት የተወሰዱ ቅርሶች ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአገሪቷ ውስጥ ይገኛሉ። ከሐር የተሠራው የንጉሡ ትንሽ የአንገት ልብስም ስታሊይብሪጅ ውስጥ በሚገኘው ሰታምፎርድ ፓርክ ሙዚየም ውስጥ ተቀምጦ ነበር።

ሙዚየሙ በ1950ዎቹ ከፈረሰ በኋላ የንጉሡ የአንገት ልብስ ወይም የካባው ክፍል በሆነ ሰው ቤት ውስጥ እንደሚገኝ ሔቨንስ እምነት እንዳላቸው እና የተረፉት ሌሎች ቅርሶችም ወደ ሌሎች የአካባቢው ሙዚየሞች መሰራጨታቸውን ገልፀዋል።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የታሪክ ምሁሩ ለታሜሳይድ የአካባቢ ጥናት ተቋም፣ ለመዘክሮች እና ለማንቸስተር ሙዚየም ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች የጥንታዊ ዕቃዎች ማስቀመጫዎቻቸውን እንዲፈትሹ እያሳሰቡም ነው ተብሏል።

@TikvahethMagazine
20.1K views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 14:25:58
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ የጀመረበትን 78ኛ ዓመት በማስመልከት ልዩ በረራ ሊያደርግ ነው

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በነገው እለት ምሽት በረራ የጀመረበትን 78ኛ ዓመት በማስመልከት በታሪኩ የመጀመሪያ በረራ ወዳደረገበት ካይሮ ልዩ በረራ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።

አየር መንገዱ የመጀመሪያ በረራውን በአሥመራ በኩል ወደ ግብጽ ካይሮ ያደረገው ከ78 ዓመት በፊት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1946 ነበር። (ENA)

@TikvahethMagazine
23.4K views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ