#ጥቆማ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓይን ህክምና ክፍል እና ኤች.ሲ.ፒ ኪዩር ብላይንድስ ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር ከሚያዝያ 7 እስከ ሚያዝያ 11 ፥ 2016 ዓ/ም ድረስ ለ 5 ተከታታይ ቀናት ለ 450 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህሙማን ነፃ ህክምና እንደሚሰጥ አስታውቋል። ስለሆነም የህሙማን ቅድመ ልየታ ስራ ከፊታችን ሐሙስ ሚያዝያ 3 ፥ እስከ 4 - 2016 ዓ.ም በሆስፒታሉ ውስጥ የሚከናወን ሲሆን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህመም ያለባችሁ ታካሚዎች በተጠቀሱት የቅድመ ልየታ እና የህክምና ቀናት በሆስፒታሉ ውስጥ በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ጥቆማ ቀርቧል። አድራሻው አዲስአበባ ፤ ጉለሌ ክ/ከተማ ፤ ወረዳ 1፣ ከሽሮሜዳ ወደ ቁስቋም በሚወስደው መንገድ ላይ ሲሆን ታካሚዎች ለበለጠ መረጃ በሆስፒታሉ ነፃ የስልክ መስመር 998 ላይ መደወል ይችላሉ ተብሏል። @TikvahethMagazine 26.5K viewsedited 12:20