Get Mystery Box with random crypto!

የአፍሪካ ኅብረት ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ የዘር ማጥፋትና የጅምላ ጭፍጨፋን ለመከላከል ልዩ መልዕክ | TIKVAH-MAGAZINE

የአፍሪካ ኅብረት ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ የዘር ማጥፋትና የጅምላ ጭፍጨፋን ለመከላከል ልዩ መልዕክተኛ ሾመ

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት የዘር ማጥፋት ወንጀል እና ሌሎች ጅምላ ጭፍጨፋዎችን ለመከላከል ሴኔጋላዊውን አዳማ ዲዬንግ የመጀመሪያ የአፍሪካ ህብረት ልዩ መልዕክተኛ አድርገው ሾመዋል።

ልዩ መልዕክተኛው የተሾሙት በአፍሪካ አህጉር የጥላቻ እና የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን ለመዋጋት የተያዘውን የህብረቱን አጀንዳ ለማስፈፀም ሲሆን ዲዬንግ በቀድሞው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ባን ኪሙን የጅምላ ጭፍጨፋ መከላከል ልዩ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል ተብሏል።

@TikvahethMagazine