Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethiopia — TIKVAH-ETHIOPIA
ርዕሶች ከሰርጥ:
Gbe
Questionandanswer
Globalbankethiopia
Bankinethiopia
Oursharedsuccess
Furtheraheadtogether
Mpesasafaricom
Addisababa
Update
Genocide
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethiopia
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.34M
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-04-16 22:15:23
#Update

“ ከታገቱ ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም ሰባት ወራት ይሆናቸዋል። እንደቀላል ነገር በወጡበት ቀሩ ” - የታጋች ባለቤት

ከ6 ወራት በፊት ወደ ባቱ (ዝዋይ) ለስራ ጉዳይ እየተጓዙ በታጣቂዎች ታገቱ ከተባሉ 6 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች መካከል 3ቱ ቢለቀቁም 3ቱ ግን እንዳልተለቀቁ ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የሚችለውን ሁሉ እንደሞከረ ከ2 ሳምንታት በፊት ገልጾልን ነበር።

በወቅቱ #እንባ እየተናነቃቸው ቃላቸውን የሰጡን የአንዱ ታጋች እህት ፣ “ በስልክ እንኳን ‘አለሁ በሕይወት’ እንዲለን ድምጹን ያሰሙን። 2.8 ሚሊዮን ብር ተከፍሎ 3ቱ ሠራተኞች ግን ከእገታ አልተለቀቁም ” ማለታቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ ሠራተኞቹ የአገር ልማት ሥራ ላይ ሲደክሙ ነው ይሄ ችግር የደረሰባቸው። ግለሰቦቹን በማገት የሚመጣ ለውጥ የለም። በሰላም እንዲለቋቸው የሚል ጥሪ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ ” ነበር ያለው።

አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ከ3ቱ ታጋቾች መካከል የሁለት ልጆቻቸው አባት የታገተባቸው ወ/ሮ ቤተልሄም ገዛኸኝ ፥ ታጋቾቹ አሁንም እንዳልተለቀቁ ገልጸዋል።

ከባለቤታቸው በተጨማሪ አንድ የሁለት ልጃቸው እናት የሞቱባቸው አባትና አንድ ሁለት ቤተሰቦቹን የሚያስተምር ሠራተኞች እንደሚገኙበትና ከታገቱ ከ6 ወራት በላይ ቢያስቆጥሩም ፣ አሁንም ያሉበት እንደማይታወቅ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በንግግራቸው መሀል #የሚያለቅሱት ወይዘሮ ቤተልሄም በሰጡት ቃል ፣ “ በሕይወቱ ስለመኖሩም እየተጠራጠርኩ ነው። ሁለቱ ልጆቹ በትምህርታቸው ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ደርሶባቸዋል። አንዷ ተመራቂ፣ አንዱ ማትሪክ ተፈታኝ ናቸው። እኔም የስኳርና የደም ግፊት ሕመምተኛ ነኝ ” ብለዋል።

ለመንግሥት ጭምር ባስተላለፉት መልዕክትም፣ “ ሞቷልም፣ አለም ቢባል እኮ አንድ ነገር ነው። እንዲህ አድርጉ የሚሉን ነገር ካለም ቢጠቁሙን መፍትሄ ነው” ብለው፣ “እንደ ቀላል ነገር በሀገራቸው ላይ ታግተው በወጡበት ቅርት ሲሉ ዝም ማለት በጣም ይከብዳልና ሁሉም ርብርብ ያድርጉልን ” ሲሉ ጠይቀዋል።

“ ከታገቱ ሚያዚያ 19 ቀን 2016 ዓ/ም 7 ወራት ይሆናቸዋል። እንደቀላል ነገር በወጡበት ቀሩ። እቃ እንኳን ሲጠፋ ዝም አይባልም እንኳን ሰው። እንደ ሰው ትኩረት ይሰጣቸው ” ሲሉም አክለው አሳስበዋል።

“ እንዲያው በእግዚአብሔር፣ በሁሉም ልጆች ባሏቸው አባቶች፣ እህት፣ ወንድም ባላቸው ሰዎች ሁሉ ስም ሁሉም ሰዎች እንደራሳቸው አይተው የሚችሉትን ነገር ሁሉ ይተባበሩን። ያጣሩ። ከእግዚአብሔር በታች ሰዎችን ነው የምለምነው ” ነው ያሉት።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
268.8K views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 21:56:59
#Rwanda #UK

ዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን እንደተቃረበ ቪኦኤ ዘግቧል።

የዕቅዱ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስደተኞቹን #በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና በላይኛው ምክር የቀረበውን ተቃውሞ ለመቋቋም የታለመው ይህ ሕግ በዚህ ሳምንት በሃገሪቱ ፓርላማ ይድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‘ የሩዋንዳ ዕቅድ ’ የሚል ቅጽል የተሰጠው ይህ ውጥን ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ‘ሕገ ወጥ ስደተኞችን ወደዚያች አገር የሚያጓጉዙ ጀልባዎች እንቅስቃሴ’ ለማስቆም ለገቡት ቃል ‘ወሳኝ እርምጃ ነው’ ተብሏል።

የሱናክ ቃል አቀባይ ዴቭ ፓሬስ ምን አሉ ?

" የእንግሊዝ ፓርላማ በያዝነው ሳምንት በሕገ ወጥ አስተላላፊዎች ከፍተኛ እንግልት እና ብዝበዛ የሚፈጽምባቸውን ሰዎች ህይወት የሚታደግ ህግ የማጽደቅ እድል ያገኛል።

አሁን ባለው አካሄድ መቀጠል እንደማንችል ግልፅ ነው። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜው አሁን ነው። " ብለዋል።


በአነስተኛ ጀልባዎች ተጓጉዘው የእንግሊዝ ቻናልን በማቋረጥ ከዚያ የሚደርሱትን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሩዋንዳ ለማዛወር እና በቋሚነትም ኑሯቸውን በዚያ እንዲያደርጉ በማቀድ ሁለቱ አገሮች የተፈራረሙት ስምምነት 2 ዓመታት አስቆጥሯል።

በፍርድ ቤት የታገደው ዕቅድ እንግሊዝን በትንሹ 470 ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣት እንደሚችል ቪኦኤ በዘገባው አስፍሯል። #VOA

@tikvahethiopia
242.5K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 21:54:41
#Ethiopia

የመጋቢት ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት 26.2 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አሳወቀ።

በወሩ ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ፦

ምግብ ነክ ዕቃዎች (food items) 29 በመቶ ድርሻ ይዘዋል።

ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) 22 በመቶ በመሆን ተመዝግቧል።

በአጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ #በየካቲት_ወር ከነበረበት 28.2 በመቶ ወደ 26.2 በመቶ በመሆን መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አመላክቷል።

@tikvahethiopia
226.6K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 21:54:15
ቴሌብር ኢንጌጅ ምንድነው ?

(ኢትዮ ቴሌኮም)

ኩባንያችን የዲጂታል ሕይወትን በማቅለል እልፍ ጉዳይ በአንድ መተግበሪያ መከወን በሚያስችለው " ቴሌብር ሱፐርአፕ " ደንበኞች ከመገበያየት እና ገንዘብ ከማስተላለፍ ባሻገር መረጃን በነጻ በመለዋወጥ ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እና ቢዝነሳቸውን የሚያጠናክሩበት ቴሌብር ኢንጌጅ የተሰኘ አገልግሎት አስጀመረ፡፡ 

አዲሱ ቴሌብር ኢንጌጅ የቢዝነስ እና ግለሰብ ደንበኞች #ያለምንም_ተጨማሪ_የኢንተርኔት_ክፍያ ለተናጠል ወይም ለጋራ ፦
- የጽሁፍ፣
- የፎቶ፣
- ድምጽ፣
- ቪዲዮ እና ፋይሎችን ለማጋራት የሚያስችል ሲሆን ከዚህም ባሻገር ለበዓል ወይም ለተለያዩ ማህበራዊ ሁነቶች የተናጠል ወይም የቡድን መልካም ምኞት መልእክት ከገንዘብ ስጦታ ጋር መላክ የሚያስችላቸውን አዲስ ገጽታ አካቷል፡፡

በተጨማሪም በጭውውቶች ወቅት ገንዘብ ለመጠየቅ፣ ለመላክ እና ለመቀበል፣ ቢል ለማጋራት እንዲሁም ጥቅል ወይም የአየር ሰዓት መግዛትን ጨምሮ በርካታ የዲጂታል አገልግሎቶችን በአንድ መተግበሪያ እንዲያከናውኑ ያስችላል፡፡

ኩባንያችን ለክቡራን ደንበኞቹ አዳዲስ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አማራጮችን በማስተዋወቅ የቢዝነስ ተሞክሮአቸው እና የዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ላይ ተጨማሪ ምቾት እና ቅልጥፍና በመጨመር ለዲጂታል ኢትዮጵያ እውን መሆን ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረጉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ለተጨማሪ ማስፈንጠሪያውን https://bit.ly/3W3291x ይጠቀሙ፡፡

#telebirrEngage
#Ethiotelecom
232.8K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 20:03:48
#Genocide

የዘር ፍጅት (ጄኖሳይድ) እንዳይፈጸም በመከላከል እና ሲፈጸምም በማስቆም ላይ የሚሰራው ተቋም " የጄኖሳይድ ዎች " ባደረገው ምርምር የሰው ልጆች ልባቸው ሲደድር የሚጠናወታቸው የዘር ጭፍጨፋ አባዜ 8 ደረጃዎች አሉት።

እነዚህም #በተደራጀ እና #ተቋማዊ በሆነ መንገድ የሚፈጸሙት ናቸው።

ደረጃዎቹ :-

1ኛ. መከፋፈል (Classification) - እኛና እነርሱ ብሎ በመከፋፈል ለየት ይላሉ ተብለው ሚታሰቡትን የኅብረተሰብ ክፍሎች #በቀልድም_ጭምር በማንቋሸሽ በሰዎች መካከል ያለውን ልዩነት አለማክበር።

2ኛ. የሚታይ መገለጫ መስጠት (Symbolization) - ይህ የጥላቻ ግልጽ መገለጫ ሲሆን ይሁዲዎች በናዚ ጀርመን ቢጫ ኮከብ ያለበት ልብስ እንዲለብሱ እንደተደረገው ነው፡፡

3ኛ. ከሰው ክብር ዝቅ ማድረግ (Dehumanization) - ይህ ተግባር ከራስ የተለዩትን ሰብዓዊ ክብርም ሆነ መብት በመንፈግ ይፈጸማል፡፡ በሩዋንዳ አክራሪ ሁቱዎች የቱትሲ ዘውግ ተወላጆችን " #በረሮ ፣ #እባብ " ይሏቸው እንደነበረው መሆኑ ነው፡፡ ይህ ሂደት ገዳዮቹ ' እየገደልን ያለነው ሰው አይደለም፤ ታዲያ ድርጊታችን ምኑ ላይ ነው ጥፋትነቱ ? ' እንዲሉ መንገዱን ይጠርግላቸዋል፡፡

4ኛ. ማደራጀት (Organization) - በጥላቻ ላይ የተመሠረቱ መንግሥታት አንድን ሕዝብ የሚያጠፋላቸውን ኃይል #ያሰለጥናሉ፡፡

5ኛ. በተቃራኒ ጎራዎች ማሰለፍ (Polarization) - ሕዝቡ በዘውጉ ከጨፍጫፊው እና ከተጨፍጫፊው ወገን ሚናውን እንዲለይ ይደረጋል፡፡ በብዛት ይህ የሚሆነው በጥላቻ ቡድኖች ውትወታ በመገናኛ ብዙሃን የጥላቻውን መርዝ በመርጨት ነው፡፡ አንዱን ዘውግ ከሌላው ለይቶ በማውጣት " ጠላት ነው " ብሎ ማወጅ ፤ ይህ የገዳዩን ዘውግ አባላት በቀላሉ ለማሳመንና ለህሊናው እንዲቀለው ለማድረግ ጥቅም ላይ የሚውል ነው።

6ኛ. ዝግጅት (Preparation) - ሰለባዎቹ በልዩነቶቻቸው ተለይተው ይፈረጃሉ፡፡ የጭፍጨፋው ንድፍ አውጭዎች ሰዎችን በመኖሪያ አድራሻቸውና በሌሎችም መለያዎች ይፈርጁና ለፍጅት ያዘጋጇቸዋል፡፡

7ኛ. ፍጅት (Extermination) - በታቀደና ሆነ ተብሎ በተመቻቸ ዘመቻ የጥላቻ ቡድኖቹ ሰለባዎቻቸውን ይጨፈጭፋሉ፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በዘር ፍጅት ማንነታቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ተጨፍጭፈዋል፡፡

8ኛ. ክህደት (Denial) - ግድያውን የፈጸሙትም ሆኑ ቀጣይ ትውልዶች ምንም ዓይነት ጥፋት ያልተፈጸመ በማስመሰል ክህደት ይፈጽማሉ፡፡

ከዚህ የጭፍጨፋ ሂደት እንደምንረዳው የዘር ፍጅት በአንድ ሌሊት ያለምንም ዝግጅት ስለማይፈጸም ራሳችንን ከላይ ከተጠቀሱት በሌላው ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ከስተቶች ፈጽሞ ማራቅና የዕለት ከዕለት ድርጊቶቻችንን መገምገምም ያሰፈልገናል።

እነዚህን የዘር ፍጅት አመላካች ሂደቶች በማናቸውም ደረጃ በእንጭጩ መቅጨት ከተቻለ የከፋ እልቂትን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ይችላል።

ሁቱትሲ
ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛና ስቲቭ ኤርዊን
በመዘምር ግርማ

#Rwanda2024 #Kwibuka #Remembering

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
2016 ዓ/ም

@tikvahethiopia
152.7K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:34:01
#Kwibuka

" ክፍፍል እና ፅንፈኝነት ካልተገታ በማናቸውም ቦታ ወደ ዘር ማጥፋት ሊያመራ ይችላል " - ፖል ካጋሜ

ከ30 ዓመታት በፊት በሩዋንዳ በ100 ቀናት ብቻ እስከ 1,000,000 ሚደርሱ ሰዎች የተጨፈጨፉበት የሩዋንዳ ዘር ፍጅት እየታሰበ ይገኛል።

የዘር ፍጅቱ የተፈፀመበትን 100 ቀናት ታሳቢ በማድረግ ከሚያዚያ 7 (እ.ኤ.አ) አንስቶ ለ100 ቀናት የዘር ጭፍጨፋው ሰለባዎች ይታሰባሉ ፤ ይህም ኪውቡካ /Kwibuka/ ይባለል።

ከሳምንት በፊት በኪጋሊ በነበረ ስነስርዓት ላይ ፕሬዜዳንት ፖል ካጋሜ ፤ ከዘር ፍጅቱ በህይወት የተረፉ ዜጎች ለብሄራዊ አንድነት ሲሉ ስላደረጉት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።

" እጅግ የሚከብደውን የእርቀ ሰላም ሸክም እናተ እንድትሸከሙ ጠየቅናችሁ እንሆ ለሀገራችን ስትሉ ይሄንን በየቀኑ ማድረጋችሁን ቀጥላችኃል ስለዚህ እናመሰግናችኃለን " ነው ያሉት።

ፖል ካጋሜ ፥ አሁንም ድረስ በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት #የጎሳ_ፖለቲካ እየተባባሰ መሄዱን እና የብሄረሰብ ማጽዳት አደጋ መደቀኑን በማንሳት አስጠንቅቀዋል።

" ሩዋንዳ ውስጥ የደረሰው መከራ ማስጠንቀቂያ ሊሆን ይገባል። ክፍፍል እና ፅንፈኝነት ካልተገታ በማናቸውም ቦታ ወደ ዘር ማጥፋት ሊያመራ ይችላል " ብለዋል።

ሩዋንዳ መከራ ውስጥ በገባችበት ጊዜ በርካታ ሀገራት የሰላም አስከባሪ ልጆቻቸውን ሩዋንዳ መላካቸውን እና እነዛም ወታደሮች ለሩዋንዳ እንደደረሱላት ገልጸዋል።

" ነገር ግን #በጥላቻም ይሁን #በፍራቻ ያልደረሰልን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ በወቅቱ በነበረው የሁቱ መንግሥት መሪነትና የሁቱ ብሄረሰብ አባላት በሆኑ ጽንፈኛ አክራሪዎች እንዲሁም በመንግሥት በሚደገፈው የ " ኢንተርሀምዌ '  ሚሊሻ አማካኝነት እስከ 1,000,000 ቱትሲዎች ፣ ለዘብተኛ ሁቱዎችና ትዋዎች ተጨፍጭፈዋል።

Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994
AP / VOA

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
232.6K views11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:21:07
#ሊቢያ #ግሪክ

እንደ ጣሊያን የባሕር ጠረፍ ጥበቃ መረጃ ፥ ባለፈው ሳምንት የሜዲትሬንያን ባሕርን አቋርጠው ወደ #አውሮፓ ለመሻገር በመሞከር ላይ የነበሩ ፍልስተኞች ጀልባቸው ተገልብጦ 1 ህጻንን ጨምሮ 9 ሰዎች ሞተው አስክሬናቸው ተገኝቷል።

15 የሚሆኑ ፍልሰተኞች የደረሱበት አይታወቅም። 22 ሰዎችን ደግሞ መታደግ ተችሏል።

ከላምፔዱሳ ደሴት 50 ኪ.ሜ. ላይ ማዕበል በማየሉ ነው አደጋው የደረሰው። ላምፔዱሳ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሞክሩ ፍልሰተኞች የመጀመሪያ ማረፊያ ነች፡፡

በሌላ በኩል ፤ ባለፈው ሳምንት ግሪክ የ3 ታዳጊዎችን አስከሬን ስታገኝ ፤ 19 ፍልሰተኞችን ደግሞ ታድጋለች።

ፍልሰተኞቹ ይጓዙበት የነበረው ጀልባ ከቋጥኝ ጋራ በመጋጨቱ አደጋው ሊደርስ የቻለው።

ግሪክ ከአፍሪካ፣ እስያ እና መካከለኛው ምሥራቅ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሹ ፍልሰተኞች አማራጭ ናት።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
212.7K views11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:20:26
#ጠብታ_አንቡላንስ

በድንገተኛ እንዲሁም መጀመሪያ ደረጃ የህክምና ዘርፍ የሚታወቀው ጠብታ አንቡላንስ በአዲስ አበባ ለሚገኙ 10 ትምሀርት ቤቶች በዚህ ዓመት የመንገድ ደኅንነት እና የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ሥልጠና እንደሚሰጥ አስታውቋል።

በሁለት ትምህርት ቤቶች ሥራውን በይፋ የጀመረው ተቋሙ ተማሪዎችን ስለድንገተኛ ህክምና ማስተማር እንዲሁም ሞያዊ ልምድ እና መነቃቃት በመፍጠር ማብቃትን ዓላማው አድርጎ የተቀረጸ ፕሮጀክት መሆኑን የጠብታ አንቡላንስ መስራች አቶ ክብረት አበበ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ያንብቡ : https://t.me/tikvahethmagazine/21985?single

@tikvahethiopia
192.2K views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:20:15
#4WCOMPUTERS

አዲስና በብዙ አማራጭ የአሜሪካ የአውሮፓ የዱባይ ላፕቶፖችን በተመጣጣኝ እና ከገበያዉ በተሻለ ዋጋ ከመልካም መስተንግዶ ከተሟሉ ሶፍትዌሮች ጋር ይዘን እንጠብቆታለን። በተጨማሪ የ1 ዓመት ዋስትና እንዲዉም የ30 ቀን የመሞከሪያ ግዜ እንሰጣለን። የተለያዩ ዓይነት ላፕቶፓች ለማየት ና ለመምረጥ ሊንኩን ይጠቀሙ t.me/computers4w

ስልክ፦ 0911867992
አድራሻ - መገናኛ ማራቶን ህንፃ 1ኛ ፎቅ -ፎርደብሊ ኮምፒውተር
189.7K views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:20:08
ከተጠቀሱት የባንክ አማራጮች ወደ M-PESA በመላክ እስከ 50 ብር ስጦታ እንፈስ!

M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!

የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom  #FurtherAheadTogether
196.1K views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ