Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethiopia — TIKVAH-ETHIOPIA
ርዕሶች ከሰርጥ:
Gbe
Questionandanswer
Globalbankethiopia
Bankinethiopia
Oursharedsuccess
Furtheraheadtogether
Mpesasafaricom
Addisababa
Update
Genocide
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethiopia
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.34M
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2024-04-14 21:51:53
" እውቀቱ ሳይኖራቸው ቤተክርስቲያንን ወክሎ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ማስተላለፍ አይገባም " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፥ የዲጀታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ የራሷን ሕግና መመሪያ እንደምታዘጋጅ አሳወቀች።

ይህ የተሰማው " ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን " በሚል በቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መመሪያ በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ ነው።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፥ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት እና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ባለማስተላለፍ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

" ቤተክርስቲያንን ሳያውቁ ተገቢው ሙያና እውቀት ሳይኖራቸው የሃይማኖት አስተምህሮ ለማስተላለፍ እና በየማኅበራዊ ሚዲያው እና ዲጂታል ሚዲያው ለመንቀሳቀስ የሚሞክሩ አሉ " ሲሉ የጠቆሙት ብፁዕነታቸው " እውቀቱ ሳይኖራቸው ቤተክርስቲያንን ወክሎ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ማስተላለፍ አይገባም " ሲሉ አሳስበዋል።

" ማኅበራዊ ሚዲያውና ዲጀታል ሚዲያው  ከቤተክርስቲያን ይልቅ ለግለሰቦች እና ለቡድን ፍላጎቶች የመቆም ዝንባሌ በሰፊው ይታያል " ያሉ ሲሆን " ቅድሚያ ለቤተክርስቲያን መስጠት ይገባል ፤ ገንዘብ መስብሰብን ዓላማ ያደረገ የዲጂታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ ሥራ በመንፈሳዊ ቅኝት ያልተቃኘ በመሆኑ እርምት የሚሻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ብፁዕነታቸው በዲጂታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ የሚያገለግሉ እና የሚገለግሉ የቤተክርስቲኒቱ ልጆች ለቤተክርስቲያን ከማይጠቅሙ አጀንዳዎች ራሳቸውን እንዲያርቁ መክረዋል።

በዲጂታል ሚዲያና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም በሕሙማን እና በቤተክርስቲያን ስም የሚከናወኑ ልመናዎች ለተባለው ዓላማ ስለመዋላቸው ማረጋገጥ ከእያንዳንዱ እርዳታ ሰጪ ይጠበቃል ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን በጣስ መልኩ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ በዲጂታል ሚዲያ የሚያስተላልፉ አገልጋዮች እና ሌሎች የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው አስጠንቅቀዋል።

" በቀጣይ የዲጀታል ሚዲያና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ የቤተክርስቲያኗ የራሷን ሕግና መመሪያ እንዲዘጋጅ ይደረጋል " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
290.2K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 18:30:06
" ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ ትራክተኖችና ማሽነሪዎችን እንዳናስገባ ተከልክለናል " - አስመጪዎች

ከባድ ተሽከርካሪዎችን ፣ ትራክተሮችን እና ማሽነሪዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ አስመጪዎች ፣ መንግሥት ምንም ዓይነት መመርያ ሳያወጣ ማስገባት አትችሉም በመባላቸው በሥራቸው ላይ እንቅፋት መፈጠሩን ተናገሩ።

አስመጪዎቹ ይህን የተናገሩት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ነው።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት " የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም " እንዳላቸው ገልጸው ጉዳዩን ፦ 
- ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣
- ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣
- ለገንዘብ ሚኒስቴርና ለጉምሩክ ኮሚሽን በአካል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

ከዚህ በፊት በነዳጅ የሚሠሩ አውቶሞቢሎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉን መስማታቸውን ያስታወሱት አስመጪዎቹ፣ አውቶሞቢሎች እንዳይገቡ የተከለከለበት ዋነኛ ምክንያት እንደ አማራጭ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ ተሸከርካሪዎችን ማስገባት እንደሚቻል በማመን ነው ብለዋል፡፡

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከባድ ተሸከርካሪዎችንና ትራክተሮችን ማስገባት አትችሉም ካለ ከሳምንት በላይ እንደሆነ ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ለተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ቅሬታቸውን በአካል ሲያስረዱ፣ ተቋማቱም እንዲህ ዓይነት መመርያ አለመኖሩን እንደገለጹላቸው ተናግረዋል።

ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል።

ክልከላው ሥራ ላይ እንቅፋት እንደፈጠረባቸውና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችንም ሆነ ትራክተሮችን የሚሸጡ ነጋዴዎች ዋጋ ጨምረው በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

አስመጪዎቹ ፥ ከባድ ተሽከርካሪዎችና ትራክተሮችን ጨምሮ ሌሎች ተሽከርካሪዎች እንደ አውቶሞቢሎች በኤሌክትሪክ እንደማይሠሩ ተናግረው  " ችግሩን መንግሥት በአፋጣኝ በመረዳት ክልከላው ሊያነሳልን ይገባል  " ብለዋል፡፡

መንግሥት ከባድ ተሽከርካሪዎች ሆነ ትራክተሮች በመመርያ ቢከለክል በአገር የመጣ ጉዳይ መሆኑን በማመን ሌላ አማራጭ እንደሚፈልጉ የገለጹት አስመጪዎቹ ችግሩን የፈጠረው አንድ የመንግሥት ተቋም መሆኑ ሁኔታውን የተወሳሰበ እንዲሆን አድርጎታል በማለት አስረድተዋል።

ሪፖርተር ጋዜጣ ፥ ጉዳዩን በተመለከተ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን በስልክ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም ሳይሳካ እንደቀረ አመልክቷል። #ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia
295.4K views15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 18:28:13
#SavetheChildren

“ በሚያሳዝን ሁኔታ 70 ሰዎች በኮሌራ ሕይወታቸውን አጥተዋል። 9 ሰዎች በኩፍኝ ሞተዋል ” - የህጻናት አድን ድርጅት

በሶማሌ ክልል በተለይም #የጎርፍ_አደጋ በደረሰባቸው ወረዳዎች በተፈናቀሉ ወገኖች የተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆነ የክልሉ የህጻናት አድን ድርጅት (Save the children) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የድርጅቱ ምሥራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ አህመድ ፣ የኮሌራ ወረርሽኙ እንደቀጠለ መሆኑን በሴፕተምበር 2023 ወረርሽኙ ከተከሰተ ጀምሮ በድምሩ 7, 480 ሰዎች እንደተጎዱ ገልጸዋል።

ዳይሬክተሩ በሰጡት ቃል፣ “ በሚያሳዝን ሁኔታ 70 ሰዎች በኮሌራ ሕይወታቸውን አጥተዋል። 9 ሰዎች ደግሞ በኩፍኝ ሞተዋል ” ብለዋል።

በተጨማሪም ከ2024 መጀመሪያ ጀምሮ 533 ሰዎች በኩፍኝ በሽታ እንደተያዙ፣ 9ኙ ሰዎች ለሞት የተዳረጉት በጎዴ ከተማ፣ ጎዴ ወረዳ፣ በራኖ አካባቢዎች መሆኑን አስረድተዋል።

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ምንድናቸው ?

በጎርፍ ለተጎዳ ማህበረሰብ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚደረግ ምላሽ፣ የአደጋ ጊዜ መጠለያ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ ለማደረግ አቅርቦቶችን ማጎልበት። የኮሌራ ክትባቶች ከፍተኛ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ላሉ የህብረተሰብ ክፍሎች መስጠት ይገባል።

የጎርፍ መጥለቅለቅ፣ መሠረታዊ እና አስፈላጊ የጤና አገልግሎቶችን ለማቅረብ ወሳኝ በሆኑ የጤና ተቋማት ላይ ጉዳት እንዳደረሰ በመገንዘብ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የጤና መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ መዋዕለ ነዋይ ሊፈስ ይገባል።

#ህፃናት በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሆናቸው ልዩ እንክብካቤ ያስፈልጋቸዋል። 

#ጥሪ ፦

(አቶ አብዲራዛቅ አህመድ)

" ለለጋሽ ማህበረሰቡ አንድ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። ወረርሽኝ እና ተደጋጋሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሚያመጣውን ከፍተኛ ጉዳትና ተጽዕኖ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመቀነስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
262.1K views15:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 18:27:48
#DStvEthiopia

የሳምንቱ ምርጥ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ
አርሰናል ከ አስቶን ቪላ ጋር የሚያደርጉትን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ፍልሚያ ዛሬ ከምሽቱ 12፡30 በቀጥታ በበዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ!

ኡናይ ኤምሪ የቀድሞ ቡድኑን ማሸነፍ ይችላል? አርሰናል የሊጉ መሪ ሆኖ መቀጠል ይችላል?

የፕሮግራም መቋረጥ እንዳያጋጥምዎ የአገልግሎት ክፍያዎን ቀድመው ይፈፅሙ። ክፍያ ሲፈፅሙ ዲኮደሩ መብራቱን ያረጋግጡ።

የዲኤስቲቪን ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!https://bit.ly/2WDuBLk

#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
249.4K views15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 22:10:34
 #Update

"...ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን ነው። በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችም አሉ " - የዓድዋ ከተማ ፓሊስ

የዓድዋ ከተማ ፓሊስ በታጋቿ ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥቷል።

መጋቢት 10/2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታ ዓዲ ማሕለኻ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች 24 ቀናት ተቆጥሯል።

የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ዋና አዛዥ ተስፋይ  ኣማረ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት መረጃ ፥ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባትን የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችን በቁጥጥር ስር ለመዋል ፓሊስ ጥረት እንያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።

የታዳጊዋ መታገት በማስመልከት በተሰቦችዋ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩ ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው የገለፁት የፓሊስ ዋና አዛዡ ፥ " ' ፓሊስ ለእገታው ትኩረት አልሰጠውም ' ተብሎ በማህበራዊ የትስስር ገፆችና በሚድያዎች የሚሰራጨው መረጃ ልክ አይደለም " ብለዋል።

" ይህን ያህል ከባድ የውንብድና ወንጀል ተፈፅሞ ፓሊስ እንዴት ችላ ይለዋል ? " ሲሉ የጠየቁት ዋና አዛዡ ተስፋይ አማረ ፥ ከከተማው እስከ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን በመቀናጀት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች ለመያዝ ሌት ተቀን እየተሰራ ነው ብለዋል።

" ታዳጊዋን ያገቱ ሰዎች ከእገታው በፊት ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉዋት የቆዩ መሆናቸው ከቤተሰቦችዋ የተገኘ መረጃ ይጠቁማል " ያሉት ዋና አዛዡ ፥ " የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውለናል። ለሚድያ መግለጫ ስላልሰጠን ብቻ ስራችን እየሰራን እንዳልሆነ ተደርጎ መውሰድ አግባብነት የለውም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ በተደጋጋሚ መረጃ ያደረሰ ሲሆን ከቀናት በፊት ቤተሰቦቿ በሰጡት ቃል ፥ አጋቾች ለማስለቀቅያ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፈላቸው በጠየቁበት ዕለት ድምጿን ከሰሙ በኃላ ዳግም እንዳላገኟት እነሱም እንዳልደወሉ ፣በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች እንኳን እንደማያውቁ ፤ በዚህም መላው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቅና ሃዘን ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረው ነበር።

#TikvahEthiopiaMekelleFamily

@tikvahethiopia
260.8K views19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 22:00:42
#AddisAbaba

" ... የተኩስ ልውውጡ የነበረው ከሚሊኒየም አዳራች በሰንሻይን በኩል ወደ ቦሌ መድኃኒዓለም በሚያስወጣው መንገድ ነበር " - የአካባቢው ነዋሪዎች

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቦሌ በፖሊስ እና ፋኖ አባላት መካከል የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች አድርጎ ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ወደ ሚያስወጣው መንገድ ላይ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ገልጸዋል።

በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት እና አንድ መንገደኛ ህይወታቸው ጠፍቷል። ሁለት የፖሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፥ " ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ ወቅት እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው " ብለዋል።

" ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።

ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃላቸው ፥ ቦሌ በነበረው የፋኖ አባላቱና እና የፖሊስ ተኩስ ልውውጥ ፦
" - ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ #ሞቷል፤
- ሀብታሙ አንዳርጌ በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፤
- አቤኔዘር ጋሻው የተባለ የፋኖ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር ውሏል።

ከዚህ ባለፈ ፦
° አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ባለመኪና ‘#አልተባበርም’ ስላሉ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ገድለውታል።
° የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታወት በጥይት መተውታል " ሲሉ ተናግረዋል።

በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ በኩል ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

@tikvahethiopia
251.2K views19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 21:20:27
የኤርትራ መንግሥት 46 እስረኞችን ለቀቀ።

በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።

የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።

በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።

እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።

በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።

የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
231.8K views18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 21:20:22
ባህር ማዶ ከሚኖር ወዳጅ ዘመድ በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎትን ገንዘብ በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሃዋላ በኩል እስከ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ሲቀበሉ 20% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፤ የዕድል ጨዋታ በመጫወት የአየር ሰዓት ይሸለማሉ!

ለተጨማሪ መረጃ ማስፈንጠሪያውን bit.ly/3ArwoEO ይጫኑ

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
235.3K views18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 21:20:16
#አቢሲንያ_ባንክ

በቅርቡ!

#bankofabyssinia  #Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
225.7K views18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 17:26:35
“ በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም ” - አዲስ አበባ ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ በፋኖና በፓሊስ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሲቪልና ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ፣ በሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

የ“ፋኖ” አመራርና አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ ከፀጥታ አካላት ተኩስ እንደከፈቱ፣ በ “ፋኖ” በኩል ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ አንድ በቁጥጥር ስር እንደዋለ፣ በመንግሥት በኩል ሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ በንጹሐን በኩል ደግሞ አንድ አሽከርካራ እንደተገደለ፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል፣ “ የተገደሉት የ “ፋኖ” ቡድን አመራርና አባላት ናቸው። አመራሩ ናሁሰናይ አንዳርጌ ነው። ሌላው አቤኔዘር ጋሻው የተባለው ነው፣ እዛው ቦታው ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሂወቱ አልፏል። ሀብታሙ አንዳርጌ ግን ምንም አልሆነም በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።

የ “ፋኖ” አመራርና አባላት የነበራቸውን እንቅስቃሴ ሲያስረዱም ኮማንደሩ፣ “ በከተማው ውስጥ ነው የሚንቀሳቀሱት የነበረው። በከተማው ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ጥፋቶች ለማጥፋት ነው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበረው ” ነው ያሉት።

አክለውም፣ “ እነርሱን ለመያዝ በተደረገው ሂደት ቦሌ ወረዳ 3 ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የሚባሉ ሁለት የፓሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ከእነርሱ (“ፋኖ”) በተተኮሰ ጥይት ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ እሱም ብቻ አይደለም አንድ አሽከርካሪ እንዲጭናቸው ሲያስገድዱት ‘አልተባበርም’ ስላለ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ሞቷል። የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታውት በጥይት መትተውታል። ሙሉ ለሙሉ ጉዳት ደርሶበታል። ሰውየው ግን ምንም የሆነው ነገር የለም ” ነው ያሉት።

“ ማኀበረሰቡ ከፓሊስና ከፀጥታ አካላት የሚተላለፉ መረጃዎችን በቁም ነገር ማዳመጥ፣ አካባቢውን ማዬት መቻል አለበት። በሰላምና በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም። እነዚህ ሰዎች መካከላችን አሉ። ይሄ አንዱ ማሳያ ነው። ቦሌ መሀል ከተማው ላይ እንግዲህ እየኖሩ ነው የነበረው ” ብለዋል ኮማንደር ማርቆስ።

“ እነዚህ ሰዎች መንፈስ አይደሉም። በተሽከርካሪያቸው ሲወጡ ሲገቡ ይታያሉ። ግን ፓሊስ በራሱ ነው ሲከታተተል የነበረው ” ያሉት ኮማንደር ማርቆስ፤ አሁንም ማህበረሰቡ አካባቢውን መጠበቅ አለበት ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
284.8K viewsedited  14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ