Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethiopia — TIKVAH-ETHIOPIA
ርዕሶች ከሰርጥ:
Gbe
Questionandanswer
Globalbankethiopia
Bankinethiopia
Oursharedsuccess
Furtheraheadtogether
Mpesasafaricom
Addisababa
Update
Genocide
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethiopia
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.34M
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2024-04-24 17:06:00
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የግንባታ ድንጋይ እና አፈር ተደርምሶ የ7 ሰዎች ሕይወት አፏል።

አደጋው የደረሰው በአዲስ ከተማ ክ/ ከተማ ወረዳ 12 " ጠሮ መስጂድ " አካባቢ ነው።

ለሊት 11 ሰዓት ገደማ ለቤት ግንባታ የተከመረ ድንጋይ እና አፈር ከላይ ወደ ታች (ወደ ቤቱ) ተንዶ 3 ክፍል ያለው ቤት ላይ አደጋ ደርሷል።

በዚህም ቤት ውስጥ ተኝተው የነበሩ 7 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

ሟቾቹ ፦
የ4 ዓመት ህጻን ፣
ሶስት የ11 እና የ12 ዓመት ታዳጊዎች 
ከ25 እስከ 30 ዓመት ያሉ 3 ወጣቶች ናቸው።

ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች የሁለት ቤተሰብ አባላት እንደሆኑ ታውቋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ አደጋው የደረሰበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለማወቅ ምርመራ ላይ ነው።

መረጃው የአዲስ አበባ እሳት እና ድንገተኛ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ነው።

@tikvahethiopia
183.9K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 17:05:35
#ቀብሪደሃር

ከፊታችን ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ጀምሮ ወደ ሶማሌ ክልል #ቀብሪደሃር ከተማ በሳምንት ሁለት ቀን የበረራ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።

አየር መንገዱ በሶማሌ ክልል ከጅግጅጋና ጎዴ ቀጥሎ #ቀብሪደሃር ሶስተኛው መዳረሻው ይሆናል።

@tikvahethiopia
156.0K viewsedited  14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 17:05:25
“ ገዳሙ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል ” - አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም

አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም በዙራያው በሰፈሩ ሰዎች የታዘ መሬቱን ለማስመለስ የካሳ ክፍያ መጠየቁን አስታወቀ።

በአማራ ክልል የሚገኘው ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም ከ30,000 እስከ 50,000 የሚሆኑ ፀበልተኞች እንደሚጸበሉበት ይሁን እንጂ የገዳሙ መሬት ሰዎች ስለሰፈሩበት እንኳን ለጸበልተኞች ለመነኮሳቱም እጅግ በመጣበቡ፣ “ ገዳሙ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል ” ተብሏል።

የገዳሙ ይዞታ የጠበበው ከበርካታ ዓመታት ጀምሮ ለመፈወስ ወደ ስፍራው የሚሄዱ ፈውስ ያገኙ ጸበልተኞችና አርሶአደሮች ከሕመማቸው ከተፈወሱ በኋላ በገዳሙ መሬት ቤት እየሰሩ እዚያው በመኖራቸው መሆኑን የገዳሙ መነኮሳት አስረድተዋል።

ሰዎቹ በአንዴ ሳይሆን ቀስ በቀስ እዛው መኖር እንደጀመሩ ጠቁሟል።
 
በገዳሙ ይዞታ የሰፈሩ ከ250 በላይ አባውራዎች ይነሱ ዘንድ ለጠየቁት ካሳና ለሌሎች አገልግሎቶች ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ አሳውቋል።

ለዚህም ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም በካፒታል ሆቴል የገቢ ማሰባሰብ መርሀ ግብር እንደተዘጋጀ፣ በመሆኑም በውስጥም በውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊያን እርብርብ እንዲያደርጉ ገዳሙ ጥሪ አቅርቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
156.8K viewsedited  14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 17:04:56
#SafaricomEthiopia

መልካሙን ዜና ከሳፋሪኮም ሰምተዋል?!

ዕለታዊ የዳታ ጥቅል ስንገዛ ቀኑን ሙሉ፣ ሳምንታዊ የዳታ ጥቅል ስንገዛ ሳምንቱን በሙሉ እንዲሁም ወርሃዊ የዳታ ጥቅል በምግዛት ወሩን ሙሉ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም መስመር በነጻ እንደዋወል!

ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ  እንጋብዛለን።

Facebook

Telegram

Twitter

Instagram

YouTube
130.0K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 17:04:48
Addis Ababa University- Cisco
Networking Academy @CiscoExams
www.netacad.com www.cisco.com

Online Live class - Cybersecurity Training & Certification Preparation.

Registration Date: April 22 to May 26, 2024
Class start date: May 27, 2024.

Course Recognitions:- Trainees will receive 4 certificates of training completion; 4 digital badges & 32% discount for LPI Linux Essentials and 58% discount for CyberOps Associate Certification exam voucher.

Mobile 0902-340070/ 0935-602563/ 0945-039478
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
141.0K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 14:37:51
#ቱርክ #ሶማሊያ

ሶማሊያ እና ቱርክ የካቲት 1/2016 በተለያዩ ወታደራዊ ዘርፎች ትብብር ለማድረግ ስምምነት መፈራረማቸውን ይታወሳል።

ይህንን ስምምነት ተከትሎ የቱርክ ባሕር ኃይል የጦር መርከብ ሞቃዲሾ ወደብ መድረሷን ቢቢሲ ዘግቧል።

የሁለቱ ሀገራት ስምምነት ዝርዝር ይፋ ባይሆንም ቱርክ የሶማሊያን ባሕር ኃይልን #ለማሠልጣን እና #ለማስታጠቅ እንዲሁም በአካባቢው ያለውን የባሕር ላይ ደኅንነት ለማስጠበቅ ተስማምታለች ተብሏል።

በአንጻሩ ቱርክ ከሶማሊያ የባሕር የተፈጥሮ ሃብት ተጠቃሚ እንደምትሆን ሪፖርቶች ይጠቁማሉ።

@tikvahethiopia
181.9K viewsedited  11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 17:06:46
#ኮሬ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ።

ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል።

የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል።

እንደ አካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ጥቃት ከደረሰባቸው ነዋሪዎች መካከል አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ የሚገኝበት ሲሆን ሁለቱ ደግሞ እድሜያቸው ከ17 እስከ 19 ባለው ውስጥ ይገመታል።

አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ ቀደም ብለው ማታ ላይ ገብተው ቦታ ይዘው እንደነበርና 7 ክላሽ የታጠቁ ሰዎች እንደሆኑ ገልጸዋል።

" ሟቾቹ ከብት ሊያግዱ ይዘው እየሄዱ እያለ፤ ከብት የሚታገድበት ቆላ የሚባል ቦታ ሲደርሱ እዚያ ጋር ነው ተኩስ የጀመሩት " ሲሉ አስረድተዋል።

ታጣቂዎቹ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ አራቱ ታዳጊዎች እያገዱ የነበሯቸውን ከብቶች ለመውሰድ ቢሞክሩም ተኩሱን ሰምተው በመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመለሱ ተደርገዋል።

የዞኑ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ የኮሬ ሕዝብ በሚያዝያ ወር ብቻ ብዙ ሞቶችን ማስተናገዱን ገልጿል።

ምን ያህል የሚለውን በቁጥር አልገለጸም።

ነዋሪዎች ግን ከመጋቢት ወር ጀምሮ ቢያንስ አራት ጊዜ በተፈጸሙ ጥቃቶች ነዋሪዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።

መረጃው የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia
47.6K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 17:06:21
#Mekelle

በመቐለ የሚገኘው " ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል " በእሳት ቃጠሎ አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ወድመት አጋጥሞታል። 

አደጋው ያጋጠመው ሚያዝያ 7/ 2016 ዓ.ም ሲሆን ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ የእርዳታ ጥሪ ተማጽኖ አቅርቧል።

የምግባረ ሰናይ ድርጅቱን የተለያዩ በጎ አድራጊዎች ሲረዱት ቆይተዋል።

የሚያዘያ 7ቱ የእሳት አደጋ ከአጋዦቹ አንዱ የሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሚሊዮን ብሮች በመስጠት ባሰራው አዳራሽ ነው የደረሰው።

በተነሳው ቃጠሎም አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ሲወድም በተረጂዎች ማደሪያ ፣ መመገብያና ፣ መስሪያ ክፍሎች ወድመት ደርሷል።

በከፍተኛ ውጪ የተሰራው አዳራሽ ሚያዝያ 6/2016 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን በነጋታው  ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ነው በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመው።

የአደጋው መንስኤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ በተነሳ ቃጠሎ ነው ተብሏል።

ያጋጠመው ቃጠሎ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም በህዝብና በመቐለ የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ የተቀናጀ ርብርብ በማእከሉ በሚገኙ አቅመ ደካሞች የህይወት ማጣት አደጋ  አልደረሰም።

ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኝታ፣ መመግብያ ክፍሎቻቸው የተቃጠለባቸው የሚንከባከባችው አቅሞ ደካሞች ሜዳ ላይ ተጥለው እንደሚገኙ በመጠቆም በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሰብአውያን ሁሉ እንዲረዱት ጥሪ አቅርበዋል።    

መርዳት የሚፈልጉ ወገኖች ፍሬምናጦስ  የአረጋውያን የእአምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000622132404 ሂሳብ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ።

#TikvahFamilyMekelle

@tikvahethiopia
45.3K viewsedited  14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 17:06:08
አስደሳች ዜና ከሳፋሪኮም !

ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA ሳፋሪኮም APP ላይ በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል! ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ  እንጋብዛለን።

Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
YouTube: https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm
36.3K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 17:06:00
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
36.3K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ