Get Mystery Box with random crypto!

Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tadeletibebu — Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tadeletibebu — Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ
የሰርጥ አድራሻ: @tadeletibebu
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 58.57K
የሰርጥ መግለጫ

ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 45

2022-09-01 13:16:01
15.9K viewsTadele Tibebu, 10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:14:10 #ሼር_ፖስት! -የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ዛሬም ወደግምባር መትመሙን አላቆመም።

-"ጃናሞራ ለጠገበው ጥይት ለራበው እንጀራ" የተባለለት ከጃሞራም ክተት ብሏል፤ በተመሳሳይ ከጭልጋ የተነሳው ኃይል ወደግንባር ጉዞ ጀምሯል

-የሸዋ ፋኖ ተወርውሮ ወልዲያ ገብቷል።

-የጎጃም ሚኒሻ ወደ ግምባር ከዘመተ ቆይቷል፣ ህዝቡም ደጀንነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።

-ትናንት የነገርኳችሁ የሽሬ ጉዳይ ህወሓት መግለጫ ሰጥቶበታል፤ አንድ ጠንካራ ምሽግ ተሰብሯል፤ የልምምጥ መግለጫ እየሰጡ ያሉት እንደ ካቻምናው ያሰቡት ባለመሆኑና ምቱ ስለከበዳቸው ነው።

-ታጋይ ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ)." የትግራይ እና ዐማራ ህዝብ ተጎራብቶ መኖሩ ስለማይቀር የተፈጠረው ቀውስ ለማከም ሁሉም ሊሰራ ይገባል፤ ከዚህ በኋላ ግን ሌላ ቁስል መፍጠር ሊያበቃ ይገባል። በመሰረቱ የትግራይ ህዝብ ጠላት የአማራ ህዝብም ጠላት ነው" የሚል መግለጫ ሰጥተዋል።

እውነት ነው. በዐማራና.. በትግራይ ሕዝብ መካከል ልዩነት አለ ከተባለ በቋንቋቻቸው ላይ ያለው ልዩነት ነው። ቋንቋቸውም ቢሆን በሴሜቲክ ቋንቋዎች የሚመደቡ የአንድ ቤተሰብ ልጆች ናቸው። ሁለቱም ሃገራችን በስልጣኔ ማማ በነበረችበት ዘመን በስነ-ህንፃ፣ ስነ-ቅርፅ፣ ስነ-ጥበብ፣ ስነ-ፅሑፍ እና ስነ-መለከት የጋራ ዓሻራ ያረፋባቸው የዓለም ቅርስ ሆነው የተመዘገቡ ቅርሶች ያሏቸው፤ የአኩስም ሥልጣኔ አሻራ ወራሾች፣ የግዕዝ ፊደል ባለቤቶች፣ የግእዝ ስነ-ጽሁፍ ባለሀብቶች፣ የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ የተመሳሳይ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተቋማት ባለቤቶች ብሎም ተመሳሳይ የኑሮ ስልትን የሚከተሉ ሕዝቦች ናቸው።

የዐማራና ትግራይ ህዝብ በባህል፣ በሃይማኖት እና ቋንቋ መተሳሰር ብቻ ሳይሆን ለሀገር የተዋደቁና በአንድ ጉድጓድ የተቀበሩ ናቸው። ብዙሃነታችን በአግባቡ ማስተናገድ ተስኗቸው ከነበሩት የስልጣኔ ከፍታ ቁልቁል ተንደርድረው ሲወርዱ ሆነ በፊዳላዊ የባላባቶች ስርዓተ-ማህበር ሲሰቃዩም ሆነ ሲሸማቀቁ የችግሩ ግፈት ቀማሽ ሁለቱም ህዝቦች ናቸው። በዛን ዘመን በተደራጀና ባልተደራጀ አኳሃን ለውስጥ ገዥዎችና የውጭ ወራሪዎች ሲታገሉ፣ ሲሰውም ይሁን ድል ሲያደርጉ አብረው ታሪክ ሰርተዋል። ባጠቃላይ ተክለጻድቅ መኩሪያ እንዳሉት፣ "ዐማራና ትግሬ በነገድ አንድነት፣ በልማድ፣ በሃይማኖት ከመዋሐዳቸው የተነሳ የመንግሥቱ ዓምድ ሆነው ኖረዋል" (የግራኝ አህመድ ወረራ፣ 15)

ይህን ታሪክ ፈጽሞ መካድና መፋቅ አይቻልም። ነገርግን ይህን የመሰለ የሁለቱን ህዝቦች ለዘመናት የተገነባ አብሮ የመኖር ወርቃማ እሴቶችና ታሪካዊ ዳራ፣ የደም፣ የባህል፣ የታሪክ፣ የቋንቋና ሃይማኖት ትስስር ወደጎን በመተው የዐማራን ህዝብ ነጥሎ በደመኛ፣ በጭቆና፣ በታሪካዊና በስትራቴጂካዊ ጠላትነት ፈርጆ ወደ ትግል የገባው ህወሓት ነው። በደም፣ በአጥንት፣ በጋብቻ የተደባለቀውን፣ ኢትዮጵያዊነትን ከደመ ሥጋው ቀላቅሎና ኮርቶ የሚኖረውን የዐማራና የትግራይ ህዝብ "እኛ" እና "እነሱ"
(Categorization) የሚል ክፍፍል የፈጠረው ህወሓት ነው። ዐማራ በጠላትነት ፈርጆ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ሰለባ ከመሆን አልፎ፣በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና መሰል እንቅስቃሴዎች ውስጥ የወሣኝነት ቦታ ቀርቶ፣ የተሳትፎ መብት እንዳይኖረው ያደረገው ህወሓት ነው።

ከዚህ በኋላ ህወሓትን ከምድረገፅ እንደ ዳይኖሰር ካልጠፋ በስተቀር የይቅርታ፣የሠላምና የአንድነት ልብ ይኖረዋል ብሎ ማሰብ እባብ ለመድ ብሎ በኪስ እንደመያዝ ይቆጠራል። መግለጫዎችም ሠላም ከመናፈቅ የመነጨ ሳይሆን ከጀርባው ተንኮልና ሴራ ያዘለ ነው።

ዝምብለህ ወጥር ዐማራ!
16.0K viewsTadele Tibebu, edited  10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:50:28
13.3K viewsTadele Tibebu, 17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:48:09
13.6K viewsTadele Tibebu, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:42:44 #ሼር_ፖስት! የወገን ጥምር እስትራቴጂካዊ ቦታ ያዘ እንጂ 'አበርገሌ' ገና አልተያዘም፤ ነገርግን የወገን ጦር በከፍተኛ ማጥቃት ወደፊት እየገሠገሠ ይገኛል። በግዳን በኩል በህወሓት የተያዙ አካባቢዎች በወገን እጅ የገቡ አሉ።
በወርቄ በኩልም በተመሳሳይ የወርቄ ጀግኖች ምላሹን እየሰጡት ይገኛሉ።

-በሁመራና ወልቃይት በኩል በ2 ቦታ ነው ጦርነቱ የተጀመረው በበረከትና በሽሬ። በሽሬ ህወሃት ሲገነባው የኖረው አንድ ምሽግ ተሰብሯል። ዝርዝር መረጃው ይቆይ!

-የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በነቂስ ግልብጥ ብሎ በመውጣቱ "መከላከያ ስላለ በቂ ነው" እየተባለ "ከምድራዊ" ከምትባል ቦታ ላይ ተመለሱ ተብሎ ሲከለከል ነው የዋለው። ይህ ህዝብ ያለ ቅስቀሳ ቁጭት፣ እልህና ወኔ ይዞት ነው መሳሪያውን እየያዘ ለመፋለም የወጣው። ይህ ለሌላው አካባቢ ብዙ ትምህርት የሚሰጥ ነው እንደ ሕዝቡ የመጣውን እንደ ሕዝብ ለመመከት "ሆ!" ብሎ መግጠም ከወልቃይት ትምህርት ሊወሰድ ይገባል። እንደሚታወቀው የወልቃይት ሰው ተኩሶ ኢላማ የሚስት አይደለም፣ እንዲያውም እዛ አካባቢ መሳት ትልቅ የጥይት ብክነትና እንደ ብቃት ማነስ ይቆጠራል። አነጣጥሮ የዥግራ አንገት በጥሶ መጣል እንደ ባህላዊ ጨዋታ ነው፤ ወይንም ተከዜ ወንዝ ዳር ሆነው፤ ተከዜ ወንዝ ውስጥ ያለው አዞ አፉን ሲከፍት በጉሮሮው ውስጥ መክተት የተለመደ ነገር ነው። ወንዱ ብቻ ሳይሆን በሴቱም ይብሳል!

-በነገራችን ላይ ዘገባ የምትሰሩ ሰዎች የአካባቢውን ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ በሚገባ ጠይቃችሁ ቢሆን ይመረጣል። በደፈናው ወልቃይት ወይንም ሰቆጣ የሚል መረጃ ስትሰጡ ያደናግራል። ለምሣሌ በሰሜን ወሎ በኩል ህወሓት ጦርነት የከፈተው በዋግኽምራ ዞን፣ በአበርገሌና ዝቋላ ወረዳ ነው። የዋግኽምራ ዞን ዋና ከተማ ደግሞ "ሰቆጣ" ናት። ይህ ዞን በርካታ ወረዳዎች አሉት ነገር ግን ጦርነቱ እየተደረገባቸው የሚገኙት  አበርገሌና ዝቋላ በዚህ ዞን ስር ናቸው።  በሌላ በኩል በሰሜን ወሎ ራያ ግንባር ወርቄ እና ግዳን እና ሌሎችም ቦታ ጦርነቱ እየተካሔደባቸው ያሉ ናቸው።


-በተመሳሳይ ወልቃይት እጅግ በጣም ሰፊና በርካታ ወረዳዎች ያሉት ነው። ህወሃት ጦርነት የከፈተበት ቦታ "በረከት"፣ ልዩ ቦታው "ሸረሪና" ይባላል፣ ከሁመራ የ20 ኪሜ ርቀት አለው።
ስለዚህ የአካባቢውን ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ሳያውቁ መረጃ የሚያዛቡ ሰዎች እርምት እንዲያደርጉ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

-በዋግ ግንባር የሕወሓትን ወራራ በሚገባ እየመከተ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ጥምር ጦር የዋግ ሕዝብ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ቀጥሏል። በየአካባቢው ያለ ማህበረሰብ ለሰራዊቱ ስንቅ እያዘጋጀ በማቀበል ደጀንነቱን በተግባር እያሳዬ ይገኛል። የወልድያ ህዝብም በተመሳሳይ! እንበረታ፤ እንናበብ!
13.9K viewsTadele Tibebu, edited  17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 13:09:41
10.9K viewsTadele Tibebu, 10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 13:09:00 #ሼር_ፖስት ጥዋት እንደነገኳቸው የሁመራ ወጣት፣ ሚኒሻና ፋኖ በቁጣ ነው ወደግምባር እየሄደ ያለው። ጥዋት በስልክ ሳነጋግራቸው "በሬሳችን ተረማምደው ካልሆነ ወልቃይት ከዚህ በኋላ ረመጥ ነው፥ ይፋጃል" ነበር ያሉኝ። በወልቃይት ጉዳይ መንግሥትም መግለጫ ሰጥቷል።

-አሁን ከዳንሻ፣ ከሳንጃ እየተመመ ያለው ኃይል ከምታስቡት በላይ ነው። ስትፈልጉ ብትውሉ አንድ መሳሪያ ያልያዘ ጀሌ አታገኙም። ሁሉም ገዝቶ ያስቀመጠውን መሳሪያ ይዞ ለማይቀረው የአርማጌዶን ጦርነት ወደግምባር እየተመመ ነው።

-ሴቶችና ወጣቶች ስንቅ ይዘው ከኋላ እየተከተሉ ናቸው። የዛ አካባቢ መኪናዎች ሰውን በማጓጓዝ ተጠምደዋል። በየሱቁ ውሃ እየተፈለገ በገፍ እየተጫነ ይገኛል።

-በጣም ያስገረመኝን ልንገራችሁ በቦታው የሚገኘው የመከላከያ ኃይል የህዝቡን ወኔና ደም ፍላት አይቶ በመገረም ነው። በህዝብ ብዛት አካባቢው በመጥለቅለቁ የመከላከያ አመራሮች "ይህ ሁሉ ህዝብ ለዚህ ትንሽ ቡድን ምንም ስለማይሰራ እባካችሁ ተመለሱ" እያሉ ልመና ላይ ናቸው። ህዝቡ ግን ወይ ፍንች..."ላለፉት 50 ዓመታት ወያኔን ከኛ በላይ የሚያውቀው የለም፤ ይህን ወሰን አልፎ ቢመጣ አይምረንም። ማይካድራ ላይም አልማረንም። እንዲያውም ከትህነግ የምናወራርደው ሂሳብ አለን። እናተንም ሆነ አካባቢውን ለቀን የትም አንሄድም" ብሎ ንቅንቅ አላለም። አሁንም ወደ ወልቃይት ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ኃይል እየገባ ነው።
11.1K viewsTadele Tibebu, edited  10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:38:56
17.1K viewsTadele Tibebu, 05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:38:35 #ሼር_ፖስት ህወሓት በሁመራ በኩል ጦርነት ከፍቷል። ከሁመራ....20 ኪሎ ሜትር "ዝጓላ" ከሚባለው አካባቢ ነው ጦርነት ከፍቶ ያደረው፤ አሁንም ውጊያ እንደቀጠለ ነው። የሁመራ ህዝብም ወደ ቦታው እየተመመ ይገኛል።

-ወልዲያ ከተማ ሠላም ናት። ትናንት እንደነገርኳችሁ ጦርነቱ ከወልዲያ በስተሰሜን አቅጣጫ ጎብዬ፤ ሮቢት እና ተኩለሽ አካባቢ ነበር። መከላከያ፣ ልዩ ኃይል፣ ፋኖና ሚኒሻ በጥምረት ባደረጉት መልሶ ማጥቃት ወደኋላ ተመልሶ አላውሃን በመልቀቅ ወደ ሮቢትና አካባቢው ሸሽቶ ነው የዋለው። ጦርነት እንደመሆኑ መረጃዎች እንደሚለዋወጡ ልብ ይለዋል! አሁን ከባለፉት ቀናት በተሻለ በወልዲያ መረጋጋት አለ። ሸሽተው የነበሩ ነዋሪዎች ወደቀያቸው እየተመለሱ ይገኛሉ።

-ትናትም እንዳልኩት ዛሬም የምደግመው ህዝቤ ሆይ አንድ ሁን፤ እንደ ዘመነ መሳፍንት ተከፋፍለን ታሪካዊ ስህተት እንዳንፈፅም፤ የልጆቻችን ህልም እንዳናጨልም። ዐማራ ካለፈው የታሪክ ስህተቱ መማር አለበት። በ17ኛው መክዘ መጀመሪያ ርስቱን የተነጠቀው፣ ለም መሬቱን ትቶ እንደ ዝንጀሮ የተራራና የቆለኛ ነዋሪ ሆኖ የቀረው ምድሪቱን እያድለቀለቀ የመጣውን ጥፋት በአንድነት ቆሞ መመከት ባለመቻሉ እንደሆነ አባ ባህሪ ነግረውናል።

-ዐፄ ቴዎድሮስ የተሸነፈው በናፒይር በሚመራው የእንግሊዝ ጦር ሳይሆን በራሱ በዐማራው መሳፍንት ክህደትና አለመተባበር ነው። ቴዎድሮስ ሚያዚያ 3፣ 1860 'በአሮጌ" ጦርነት ማግስት ለባድሉ ጀኔራል ናፒየር በጻፈው ደብዳቤ ለሕዝቡም ሆነ ለዓለም የመጨረሻ ቃሉን አሰምቶ አልፏል። ይህ ደብዳቤ አልገዘ ላለው ሕዝቡ የሟች ወቀሳ ነው። ያ እንዲያ የደከመበት የስነሥርዓት ጉዳይ እስመከጨረሻው አልሠምርለት በማለቱ የተሰማውን ቁጭት እንዲል ይገልጻል።

".... ያገሬ ሰው ገብር ሥራት ግባ ብየ ብለው እምቢ ብሎ ተጣለኝ። እናንተ [እንግሊዞችን] ግን በስራት በተገዛ ሰው አቸነፋችሁኝ። እኔን ወደውኝ የተከተሉኝ ሰዎች አንድ እርሳስ ፈርተው ጥለውኝ ሸሹ ብትቃጧቸው ከሮጡ ሰዎች ጋራ አልነበርሁም ጌታነኝ መስሎኝ ባልሰላ መድፍ ሥታገል ዋልኩኝ።..."


ለቴዎድሮስ መሸነፍ ምክንያት የእንግሊዞቹ የጦር መሳሪያ ጥራት አይደለም፤ ህዝቡን ሥርዓት ግባ ብሉት እምቢ አለ፤ የዐማራው መሳፍንት ከመተባበር ይልቅ በቴዎድሮስ ላይ ሸፈተ፤ ከቴዎድሮስ ጎን የነበሩትም ፈርተው ጥለውት ጠፉ። ቴዎድሮስ ወዲህ ዞር ቢል ሰው የለም፤ ያምኗቸው የነበሩት ሁሉ ከድተውታል፤ እንደ ጀብራ መቅደላ አፋፉ ላይ ብቻውን ቆሞ ቀረ፤ በመጨረሻም "ከተወለድሁኝ እስታሁን ወንድ እጄን ጨብጦት አያውቅም" ብሎ ሽጉጡን ጠጣው።

ይህ ያለፈ የታሪካችን አንዱ አካል ነው። ዛሬ ልንማርበት ይገባል፤ በአንድነት እንቁም፤ በሥርዓት እንመራ፤ የሆነ ከተማ ተያዘ፤ አልተያዘ የሚለው ክርክር የዐማራ ከተሞችን ከመወረር አያድናቸውም። ከተሞቻችን የማይያዙት በአንድነት ስንመክት፣ ለመከላከያ፣ ልዩ ኃይሉና ፋኖ ደጀን ስንሆን ብቻ ነው።
17.0K viewsTadele Tibebu, edited  05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:40:18
21.6K viewsTadele Tibebu, 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ