Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.54K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-01-12 05:02:10
የ4ኛዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የንግድ ቤት ጨረታ ነገ ጥር 3/2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በሰንጠረዡ ውስጥ በተጠቀሱት የመሸጫ ፕሮጀክቶች / ቦታዎች የሚጀመር መሆኑን የአ/አ ቤቶች ልማት ኮርፓሬሽን አስታወቀ።


በ40/60 ፕሮግራም በተለያዩ ክ/ከተሞች ያስገነባቸውን 5,397 በጋራ መኖሪያ ቤቶች ሕንፃ ላይ የሚገኙ ንግድ ቤቶችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ እንደሚፈልግ ዛሬ አሳውቋል።

ኮርፖሬሽኑ ለሽያጭ ያቀረባቸውን የንግድ ቤቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ተወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ድርጅት በኮርፖሬሽኑ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከጥር 3/2015 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ የካቲት 6/2015 ዓ.ም. ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ ባሉት 28 የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 10፡30 ድረስ ቅዳሜ ግማሽ ቀን ጨምሮ በአካል በመቅረብና የማይመለስ ብር 400 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ ተብሏል።

የት ነው የጨረታው ሰንድ የሚገዛው ?

- አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ቤቶች ጽ/ቤት 1ኛ ፎቅ
- ሰንጋ ተራ 40/60 ቤቶች ብሎክ 4
- የካ ክ/ከተማ ቤቶች ጽ/ቤት 4ኛ ፎቅ
- የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን 4ኛ ፎቅ
- 40/60 ቦሌ ቡልቡላ ቅርንጫፍ 1 ጽ/ቤት
- 40/60 አያት 49 ማዞርያ ብሎክ 21 ቅርንጫፍ 2 ጽ/ቤት

የጨረታ ሳጥን የካቲት 6/2015 ከቀኑ 11 ሰዓት ተዘግቶ በማግስቱ የካቲት7/2015 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ተጫራጮች በተገኙበት ይከፈታል ተብሏል።
2.7K viewsAnt B, 02:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 09:40:18
የ14ኛው ዙር 20/80 እና የ3ኛው ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት እጣ የወጣላቸዉ የቤት እድለኞች ከጥር 1 ጀምሮ ቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የአንድ ማእከል አገልግሎት ውስጥ በመገኘት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ኮርፖሬሽኑ ጥሪ አቀረበ ፡፡ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጥር 1/2015 ዓ.ም
521 viewsAnt B, 06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 19:41:04
1.9K viewsAnt B, 16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 20:02:31
አምባሳደር ተሾመ ቶጋ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ከዛሬ ታሕሳስ 28 ቀን 2015 ጀምሮ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል፡፡

አምባሳደር ተሾመ ከዚህ ቀደም በቻይና የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር በመሆን ማገልገላቸው ይታወቃል።
4.8K viewsAnteneh Babanto, 17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 19:51:02 የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ታህሳስ 29 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ዘጠኝ ጊዜ መድፍ የሚተኮስ መሆኑን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ የሀገር መከላከያ የኪነ ጥበባት ስራዎች ዳይሬክቶሬት  አስታውቋል፡፡

ፖሊስ በተለያዩ ጊዚያት ባደረገው ቁጥጥር የጦር መሰሪያ የሚያዘዋውሩ ህገወጦች   በዓላትን ጠብቀው ርችትን ሽፋን አድርገው ልዩ ልዩ የጦር መሳሪዎችን እንደሚተኩሱ አረጋግጧል፡፡ 

ከዚህ ቀደም በአንድንድ ቦታዎች በርችት ምክንያት ጥፋትን ያስከተሉ አደጋዎች ማጋጣማቸውን ፖሊስ አስታውሶ ለህብረተሰቡ ሰላምና እና ደህንነት ሲባል እንዲሁም ርችት መተኮስ ለጦር መሳሪያ ለሚያዘዋውሩ ህገወጦች ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ ለህብረተሰቡ ሰላምና ደህነንት ሲባል ርችት መተኮስ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ህብረተሰቡ ርችት ባለመተኮስ አስፈላጊውን ትብብር እንዲሁም  ርችት በመተኮስ የህብረተሰቡን ፀጥታ የሚያውኩ  ሲያጋጥመው ለፖሊስ ሪፖርት እንዲያደርግ  የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላፏል፡፡
3.5K viewsAnteneh Babanto, 16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 17:33:22 20/80 እና 40/60 ውል ፦

የቤት እድለኞች #ውል_ለመዋዋል_ሲመጡ ማሟላት የሚጠበቅባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ምንድናቸው ?

- እጣው የደረሰው ግለሰብ ውል ለመፈፀም በአካል መቅረብ፤

- በውጭ የሚኖሩ ጉዳያቸውን በውክልና ለማስጨረስ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ (አውታንቲኬት) ሆኖ የመጣ ውክልና ማቅረብ፤

- የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤

- የጋብቻ የምስክር ወረቀት ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤

- ያላገባ/ች ከሆነ/ች 6 ወር ያላለፈው የምስክር ወረቀት፤

- ያገባ/ች ከሆነ/ች የትዳር አጋር የታደሰ መታወቂያ ዋና እና ፎቶ 2 ኮፒ፤

- የምዝገባ ማረጋገጫ (print out) ዋና እና 1 ፎቶ ኮፒ፤

- የምዝገባ የምስክር ወረቀት ዋና እና 1 ፎቶ ኮፒ፤

- የባንክ ምዝገባ ማረጋገጫ ከተመዘገቡበት ባንክ የሚቀርብ ዋና እና 1 ፎቶ ኮፒ፤

- የባንክ የቁጠባ ደብተር ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ (ፎቶ ባለው በኩል)፤

- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤

- ቅጽ -09 (ከወረዳ ተሞልቶ ታሽጎ የሚላክ) ዋና እና 1 ፎቶ ኮፒ፤

- የጠፋ ሰነድ ካለ የፖሊስ ማስረጃ ዋና እና 1 ፎቶ ኮፒ፤

- 4×4 የሆነ ጉርድ ፎቶ ግራፍ 4፤

- ፍቺ ካለ በፍ/ቤት የፀደቀ ፍቺ ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤

- የንብረት ክፍፍል ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤

- ባለ ዕድለኛው በሞት ከተለየ የውርስ አጣሪ ሪፖርት ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ፤

- የወራሽነት ማስረጃ ዋና እና 2 ፎቶ ኮፒ ባለ እድለኛው ወይም ወኪሉ ይዞ መቅረብ አለባቸው።

የተዘረዘሩትን ቅድመ ሁኔታዎችን ሳያሟላ የሚመጣ ማንኛውም ባለጉዳይ #እንደማይስተናገድ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በጥብቅ አሳስቧል።

#በውጭ_ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያዊ ከላይ የተጠቀሱትን ማሟላት #የግድ_ሆኖ ፦

• የታደሰ ፓስፖርት ወይም ቢጫ ካርድ (yellow card) የታደሰ፤

• በውክልና ከሆነ የውክልና ወረቀቱ በጀርባው በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማህተም የተረጋገጠ እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ ይዞ መቅረብ ይጠበቅበታል ተብሏል።

ባለዕድለኞች / ወኪላቸው በ60 የስራ ቀናት ውስጥ ካልተዋዋሉ ምን ይፈጠራል ?

ባለእድለኞች ወይም ወኪላቸው ምዝገባ ከተጀመረበት ቀን አንስቶ ባሉት 60 የሥራ ቀናት ውስጥ ቀርበው ካልተዋዋሉ #ቤቱን_እንዳልፈለጉት_ተቆጥሮ ተመላሽ እንደሚደረግ የከተማው ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በአጽንኦት አሳስቧል።

Credit : አዲስ ዘመን ጋዜጣ
3.5K views@A, 14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 17:31:20
የ20/80 እና 40/60 ባለዕድለኞች ውል እንዲፈፅሙ ጥሪ ቀረበ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ፤ የ14ኛ ዙር 20/80 እና 3ኛ ዙር 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም የጋራ መኖሪያ ቤቶች የቤት እድለኞች ማሟላት የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት ከጥር 1ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ባሉት 60 የሥራ ቀናት ውስጥ ባለእድለኛው ወይም ወኪሉ ቀርበው ውል መዋዋል እንደሚጠበቅባቸው አሳስቧል።

ከተማ አስተዳደሩ በ14 ኛ ዙር የ2080 የቤት ልማት ፕሮግራም 18 ሺ 930 ቤቶች፣ በ40/60 ደግሞ 6 ሺ 843 ቤቶች እንዲሁም ተጨማሪ 18 ስቱዲዮ ቤቶች በድምሩ 25 ሺ 791 ቤቶችን እጣ የማውጣት መርሃ ግብር በማካሄዱ የሚዘነጋ አይደለም።

ውል የመዋዋያ ቦታው #መገናኛ በሚገኝው የቦሌ ክፍለ ከተማ ቅጥር ግቢ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫ ውስጥ መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን ጋዜጣ
3.2K views@A, 14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 12:05:59
በኢትዮጵያ ታሪክ ስነዳ ሂደት ሞጋቹ ፕሮፌሰር - ዶ/ር  ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ
**********************

ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ በቀድሞው በከንባታ እና ሐዲያ አውራጃ በኩፋላ ሐበሌ ግንቦት 12 ቀን 1930 ዓ.ም ተወልደው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቢቾ ሆሣዕና ሚሽን ት/ቤት እና በመንግሥት ትምህርት ቤት ሲከታተሉ ቆይተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አዳማ በሚገኘው በአጼ ገላውዴዎስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ባይብል አካዳሚ  ተምረዋል።

ከዚያም ወደ አሜሪካ በማቅናት በኮሙኒቲ ኮሌጅ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው በኀብረተሰብ ታሪክ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል። ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲም በአፍሪካ ታሪክ ጥናት የማስትሬት ዲግሪያቸውን፣ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ እና በአውሮፖ ታሪክና በፍልስፍና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ ወስደዋል።

ዶክትሬታቸውን ካጠናቀቁ  በኋላ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸው ለሁለት ዓመታት በቨርጂኒያ ዩንየን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲያስተምሩ ቆይተው አብዮቱ ሲፈነዳ ‘የታሪክ አካል መሆን አለብኝ’ በማለት ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ያኔ የነበራቸውን ስሜት ሲገልፁ “የኢትዮጵያ አንድነትን እንደ ጣኦት እያመለኩት መጣሁ” ይላሉ።

በአሜሪካን ሀገር በፍልስፍና እና በታሪክ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ሲማሩ ከአምስት መቶ ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት ከፍተኛ አድናቆት ማትረፍ ችለዋል። በዚህም ምክንያት  በርካታ የአሜሪካን ሀገር ዩንቨርስቲዎች የነፃ የትምህርት ዕድል በአማራጭነት አቅርበውላቸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0QqMHTvURLqukvcR74zi4ZorPLC42NQjBFu2oY7drke8vKetEVU2n8bBKc3tnW1Htl
1.6K viewsAnt B, 09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 22:37:00 https://www.tiktok.com/t/ZTRbgSQTH/
482 viewsAnteneh Babanto, 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 00:18:29 https://www.tiktok.com/t/ZTRbXNaJ1/
462 viewsAnt B, 21:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ