Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
Fastmereja
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 48.04K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-06-16 13:12:34
3.7K viewsDan B, 10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-15 20:30:24 አሜሪካ በጥንቆላ ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች

ጥንቆላ በአሜሪካ ለ100 ሺህ ገደማ ዜጎች ስራ እድል ሲፈጥር 2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢም አስገኝቷል።

አሜሪካ በጥንቆላ ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች
ዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ከዚህ በፊት ጥንቆላ እና ከዚሁ ጋር የተያያዙ ሁነቶችን በይፋ አግዳ ነበር፡፡

በተለይም በቨርጂኒያ ግዛት ጥንቆላ በተለያዩ መንገዶች በስፋት ከሚፈጸሙባት ግዛቶች መካከል ዋነኛዋ ስትሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የተጠቃሚዎች መብዛት ህጉ እንዲሻር ምክንያት ሆኗል፡፡

የ45 ዓመቷ አሽሊ ብራንተን በዚሁ ግዛት ላለፉት ዓመታ በጥንቆላ ሙያ ተሰማርታ ማሳለፏን እና የደንበኞቿ ቁጥርም በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ለቪኦኤ ተናግራለች፡፡

ወደ ጥንቆላ ሙያ ከመግባቷ በፊት የስነ ውበት ባለሙያ እንደ ነበረች የምትናገረው ብራንተን ሰዎች ስለ ጥንቆላ ያላቸው አመለካከት ያለ ማስታወቂያ በየጊዜው እየጨመረ መጥቷል ብላለች፡፡

እንደ ዘገባው ከሆነ በተለይም ከባድ ውሳኔ ያለባቸው ሰዎች፣ የተበላሸ የፍቅር ግንኙነት ያላቸው እና ከሀገር ሀገር የሚያጓጉዝ ስራ ያለባቸው ሰዎች ዘብዝተው ወደ እሷ ይመጣሉ፡፡

አብዛኞቹ ደንበኞቿ ለዚሁ ስራ ተብለው የተዘጋጁ ካርዶች ወይም የእጣ ፈንታ ማንበቢያ ካርድን የሚጠቀሙ እንደሆኑ የምታነገረው ይህች አሜሪካዊት ጠንቋይ ደንበኞቿ ትንበያዎቿን እንደሚወዱት እና እንደሚሳካላቸውም አክላላች፡፡

አሜሪካ ጥንቆላን በይፋ ህገ ወጥ ነው ብላ አውጃ ቢሆንም በርካታ የሀገሬው ዜጎች ግን በድብቅ ሲጠቀሙ መቆየታቸውን በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

የተጠቃሚዎችን መብዛት ተከትሎ ጥንቆላ ህገ ወጥ መሆኑ የቀረ ሲሆን ባሳለፍነው ዓመት ብቻ ይህ ዘርፍ ለ100 ሺህ አሜሪካዊያን የስራ እድል እንደፈጠረ እና 2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማስገኘቱ ተገልጿል፡፡

የቨርጂኒያ ከተማ ህግ አውጪ ምክር ቤት በጥንቆላ ላይ ተጥሎ የነበረውን እግድ በይፋ ማንሳቱ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

በአሜሪካ ከዚህ በፊት በተደረገ ጥናት ከ10 አሜሪካዊያን አራቱ በጥንቆላ የሚያምኑ ሲሆን ከ10ሩ ዜጎች ውስጥም ቢንስ አንዱ ጠንቋዮችን አማክሮ ያውቃል ተብሏል ሲል አልአይን ዘግቧል። ጫደታ
3.8K viewsDan B, 17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-11 19:02:27 ግንቦት 20 ከካላንደር ላይ ተሰረዘ
#FastMereja
ዛሬ በፓርላማ የፀደቀው የህዝብ በዓላት እና የበዓላት አከባበርን ለመወሰን የወጣው አዋጅ በልማድ ሲከበር የቆየውን ግንቦት 20 ብሔራዊ በአልነቱ አስቀርቷል፡፡ 

የሰማዕታትን ቀን (የካቲት 12) እና የብሔር ብሔረሰቦች ቀን (ህዳር 29 ) መስሪያ ቤቶች ክፍት ሆነው፤ ታስበው ይውላሉ ተብሏል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሰንደቀ ዓላማ ቀን፣ የመከላከያ ቀን፣ የሴቶች ቀንና ሌሎችም በዓላት ታስበው የሚውሉ ናቸው ተብሏል፡፡

አዋጁ ተከብረው በሚሉ ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት መደረግ አለባቸው ያላቸውን ተቋማትን ዝርዝር አስቀምጧል፡፡

በዚህም የእለት ከእለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑ የውሃ፣ የመብራት፣ የስልክ እና መሰረታዊ አገልግሎቶች የጤና ተቋማትና መድሃኒት ቤቶች ለሕዝብ ደህንነት አስፈላጊ የሆኑ የደህንነት ተቋማት የእሳት አደጋ፣ መከላከል አገልግሎትና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎቶች እንዲሁም ነዳጅ ማደያዎች ክፍት ሆነው እንዲውሉ በአዋጁ ተቀምጠዋል፡፡

ምክር ቤቱ የህዝብ በዓላትና የበዓላትን አከባበር መወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ በአንድ ድምፅ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ አፅድቆታል ሲል ሸገር ሬዲዮ ዘግበዋል።
3.6K viewsDan B, 16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-09 20:09:15 የሶማሌላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያና የሶማሌላንድን የባህርበር ስምምነት በዛሬው እለት ለፓርላማ አቅርበዋል።

"ሁለታችንም የምንፈልገው ይታወቃል ኢትዮጵያ ባህር በር ትፈልጋለች፣ እኛም እድሜ ዘመናችንን ሀገር ለመሆን ታትረናል ።

" ያሉት ፕሬዝደንት ሙሴ ...ለፓርላማው ባደረጉት ንግግር "ስምምነት ከሰሞኑን ይፈፀማል ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ግልፅ የሆነ ስምምነት ላይ ደርሰናል፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ታገኛለች እኛም የሀገርነት እውቅና ከኢትዮጵያ ይሰጠናል ሁሉም ስምምነቶች አልቀዋል መፈረም ብቻና ለፓርላማዎቻችን ማፅደቅ ነው የቀረን ብለዋል።

በሌላ በኩል ሁለቱ ሀገራት የተግባር እንቅስቃሴዎችን እያደረጉ ሲሆን የሶማሌላንድ ፖሊስ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ሀዋሳ ከተማ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል። በተጨማሪም የሶማሌላንድ አየር መንገድ ለማቋቋም ዝግጅት የተጀመረ ሲሆን ሶማሌላንድ 4 የመለማመጃ አነስተኛ አውሮፕላኖችን መግዛቷን ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ ተናግረዋል።
4.0K viewsDan B, 17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-06 13:25:42
የከባድ መኪና ሹፌሮች ኦሮሚያ ክልል ውስጥ መስራት አስቸጋሪ ኾኖብናል ማለታቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ የከባድ መኪና ሹፌሮች፣ "የኮቴ" በሚል በእያንዳንዱ ኬላ ላይ በሕገወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚከፍሉ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ባንድ ኬላ ላይ የተሰጠ ደረሰኝ ሕጋዊ ይኹን አይኹን እንደማይታወቅና ቀጣዩ ኬላ ላይ ደረሰኙን አሳይቶ ገንዘብ ሳይከፍሉ ማለፍ እንደማይቻልም አሽከርካሪዎች መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አሽከርካሪዎች ለኦሮሚያ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ማጠናከሪያ በሚል ከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍሉ እንደሚገደዱም ተናግረዋል።(ዋዜማ)
4.6K viewsDan B, 10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-02 16:32:52
ጦርነትን ኖረንበታል። የተወሰኑ ችግሮቻችንን ፈትተንበታል።

አብዮትን ደጋግመነዋል። የተወሰኑ ችግሮችን ፈትተንበታል።

በሁለቱም ያልተፈቱትን ችግሮች ለመፍታት የቀረን መንገድ ምክክር ነው።

ምክክርን ግን አልተጠቀምንበትም።

ጦርነትና አብዮት የተሟላ መፍትሔ የማያመጡት አሸናፊ እና ተሸናፊ ስለሚያስከትሉ ነው።

ቢዘገይም የተሸነፈው ለማሸነፍ ይታገላል። ያሸነፈውም ድሉን ለመጠበቅ ይዋጋል።

ምክክር ግን ሁሉንም አሸናፊ ያደርጋል። ከተሸነፍንም ሁላችንም ለሀገራችን ብለን ነው የምንሸነፈው።

ይሄ የምክክር ሂደት ሦስት ነገሮች ያስገኝልናል።

1. ሁሉንም ባይሆን እንኳን ዋና ዋና ችግሮችን ይፈታል
2. ከጦርነት ይልቅ ምክክር ባህል እንዲሆን ያደርጋል
3. በተቃራኒ ኃይሎች መካከል መቀራረብና መግባባት ይፈጥራል። ይሄንን መቀራረብ በመጠቀምም ወደፊት በጉዳዮች እየተነጋገርን ለመቀጠል ያስችለናል። በመሆኑም ይኽንን እድል ሳናበላሽ ወደ ተሟላ ድል እንድናሸጋግረው እጠይቃለው።
4.8K viewsDan B, 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-01 22:58:05

3.8K viewsDan B, 19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-31 00:17:00 #Ethiopia

ማንኛውንም ሰው ከሀገር እንዳይወጣ የማገድ ስልጣንን፤ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤትን በዋና ዳይሬክተርነት ለሚመራ ኃላፊ የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ።

የአዋጅ ማሻሻያው ምን ይዟል ?

ማንኛውንም ሰው ከሀገር እንዳይወጣ የማገድ ስልጣንን፤ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤትን በዋና ዳይሬክተርነት ለሚመራ ኃላፊ ይሰጣል።

ነባሩ ህግ ምን ይላል ? “ ማንኛውም ሰው ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ ሊታገድ የሚችለው በህግ መሰረት በፍርድ ቤት ሲታዘዝ ብቻ ነው ” ይላል። ዛሬ ለፓርላማ የቀረበው የአዋጅ ማሻሻያ በነባሩ ህግ የተቀመጠውን የፍርድ ቤት “ ብቸኛ ስልጣን ” የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤትን በዋና ዳይሬክተርነት ለሚመራ ኃላፊ በተጨማሪነት ያጋራ ነው።

አዲሱ ማሻሻያ ፥ " የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ከሚመለከታቸው የደህንነት አገልግሎት እና ህግ አስከባሪ አካላት ከሚያገኘው መረጃ ወይም አገልግሎቱ በራሱ ከሚያገኘው መረጃ በመነሳት፤ በብሔራዊ ጥቅም እና ደህንነት ላይ ሊቀለበስ የማይችል ግልጽና ድርስ የሆነ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል ሁኔታ መኖሩን ሲያምን፤ ማንኛውም ሰው ከሀገር እንዳይወጣ ማገድ ይችላል " ሲል ደንግጓል። 

  የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት " ከሀገር እንዳይወጣ ያገደውን ሰው ይዞ የሚያቆይ ከሆነ ፍርድ ቤት መቅረቡን ማረጋገጥ አለበት " ሲል የአዋጅ ማሻሻያው ደንግጓል። 

ዜጎች ከሀገር እንዳይወጡ የማገድ ስልጣን ላይ ማሻሻያ የተደረገው፤ በነባሩ ድንጋጌ ምክንያት እየደረሰ ያለውን " ከፍተኛ ጉዳት " ለመቅረፍ ነው ይላል ማሻሻያው። አሁን በስራ ላይ ባለው አዋጅ መሰረት " ከፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ እስኪገኝ ድረስ በብሔራዊ ጥቅም እና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ ወይም ሊያደርሱ የሚችሉ ሰዎች ከሀገር እየወጡ ከተጠያቂነት እያመለጡ በሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም እና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ነው " መሆኑን የረቂቅ አዋጁ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፦

ማሻሻያ አዋጁ " አስተዳደራዊ ቅጣት " አንቀጽ ይዟል።

" ከጊዜ ወደ ጊዜ በህገ ወጥ መንገድ በሀገራችን ውስጥ የሚኖሩ የውጭ ሀገር ዜጎች እየተበራከቱ፤ በህገ ወጥ ድርጊቶች እየተሳተፉ ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩ በመሆኑ በአስተዳደራዊ ቅጣት በመቅጣት ከህገ ወጥ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ሲል ያስረዳል።

በዚህም በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የውጭ ሀገር ዜጎችን " በጥቁር መዝገብ እንዲመዘገቡ እና ከሀገር እንዲወጡ ማድረግ ወደ ህጋዊ ስርዓት እንዲመጡ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና " እንዳለው ተብራርቷል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ አማካኝነት፤ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤት አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጥል በአዋጅ ማሻሻያው ስልጣን ተሰጥቶታል።

" ይህን አዋጅ አሊያም በዚህ አዋጅ መሰረት የወጣ ደንብ ወይም መመሪያን የጣሰ ማንኛውም ሰው፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰድበታል " ይላል ማሻሻያው።
4.3K viewsDan B, 21:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-30 15:25:37
በእስራኤል ቴል አቪቭ በኤርትራውያን ስደተኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ ተገለፀ፡፡
ግጭቱ በኤርትራ መንግስት ተቃዋሚ እና ደጋፊ በሚል በሁለት ጎራ በተከፈሉ ኤርትራውያን ስደተኞች መካከል የተፈጠረ ሲሆን አንድ ሰው በስለት ተወግቶ ህይወቱ ማለፉን ፖሊስ እና የህክምና ባለሙያዎች አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም በግጭቱ አምስት ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው የተገለፀ ሲሆን፤ ከአምስቱ ውስጥ ሶስቱ ለሞት የሚያደርስ ከባድ የአካል ጉዳት አስተናግደዋል ነው የተባለው፡፡
ግጭቱን ተከትሎ የእስራኤል ፖሊስ 20 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን እና ህይወቱ ያለፈውን ሰው በተመለከተ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡
የእስራኤል ፖሊሶች ግጭቱን በማርገብ ሰላም ለማስከበር በቴል አቪቭ አካባቢ ተሰማርተው በግጭቱ ተሳትፎ እንዳላቸው የተጠረጠሩ ሌሎች ሰዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ባለፈው ዓመት መስከረም ወር በተመሳሳይ ጎራ በለዩ የኤርትራ ስደተኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት የፖሊስ ኦፊሰርን ጨምሮ 70 ሰዎች መጎዳታቸውን ያስታወሰው የዘ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ዘገባ ነው።
3.4K viewsDan B, 12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-29 18:47:59 የሰላም ምሽጋችሁን ለብልፅግና አትልቀቁ!

የድርድር ጉዳይ ወጥመድ እየሆነ ነው። ሰሞኑን ደግሞ ለብልፅግና በሚመች መልኩ ወደ ወጥመዱ ዘው ተብሎ እየተገባ ነው። ጥቃት ፈፃሚው ብልፅግና ሆኖ ተጠቂዎቹ "አንደራደርም" የሚል የማይገባ ሽሽት እያደረጉለት ነው። ከዚህ የተሻለ ማድረግ ይቻል ነበር።

1) ብልፅግና እውነተኛ ድርድር አይፈልግም። ከምንም በላይ የሚፈራቸው የአማራ ጥያቄዎች አጀንዳ ሆነው ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ባለበት ወይንም በሚሰማው እንዲቀርቡ አይፈልጉም።

2) የከረመውም ሆነ የሰሞኑ ዘመቻ ብልፅግና ሰላም እንደማይፈልግ ማሳያ ነው። አዳክሜያቸው ከፈለኩት ጋር እደራደራለሁ እያለ ነው። የአማራን ጉዳይ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀርብበት አይፈልግም። ድርድር አንፈልግም ከማለት ይህን የአገዛዙን አካሄድ በተደጋጋሚ ማውሳት፣ ጦረኝነቱን ማሳየት፣ እየፈፀመ ያለውን ሰብአዊ ውድመትን በየአጋጣሚው አጀንዳ ማድረግና የአገዛዙ መልክ ሰላም ሳይሆን ይህኛው መሆኑን ማስመር።

3) እደራደራለሁ አልደራደርም ሳይባልም የሚሰሩ የህዝብ ግንኙነቶች አሉ። አገዛዙን የቋጥኝ ያህል የሚከብዱት ቅድመ ሁኔታዎች አሉ። በዛውም ደጋግመህ የተቆጠሩ የአማራ ጥያቄና በደሎችን ነው የምታስተዋውቀው።

4) አልደራደርም ካልክ ግን ብልፅግና ደስታው ነው። እንደ ሰላም ኃይል ሆኖ የሰላም ምሽግህን ይረከብሃል። "ድርድር ውይይት" ብሎ የለቀቀው የሰላም ምሽግ ገብቶ ፕሮፖጋንዳ ያዘንብብሃል። ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ አድርጎ ጭምር ሰላማዊ ለመምሰል ይጥራል። ህዝብ ጥሪ አቀረበ ወዘተ እያለ ይቀጥላል። በእልህ ከሰላም ምሽግህ ትርቃለህ። ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ያስጠቁርሃል። በዛውም የአማራውን የህልውና ጥያቄ የግብዝነት፣ የእብሪት እያስመሰለ ይቀጥላል።

5) አሁን ባለው ሁኔታ ብልፅግና ለማወናበድ ተጨማሪ እድል እያገኘ ነው። ድርድርና ወዘተ ብሎ ቢመጣ "አንደራደርም" ያሉት ካፈርኩ አይመልሰኝ " ብለው ይሸሹለታል። እየሸሹለትም ነው። የማይገባውን እድል እያገኘ ነው።

6) ብልፅግና እንኳን ወደ አዲስ አበባ ሸሽቶም ቢሆን በድርድር ቁማር ሞክሯልኮ። አልፈልግም አላለም። ወደ ክልል አወረደው። "መሳሪያ አስረክበው ይምጡ" ብሎ መቀረጃ አደረገበት። እጅ ስጡ የሚል ሆኖ "የሰላም ጥሪ" አድርጎ ቀባባው። ብልፅግና እንኳን ድርድር አልፈልግም ከማለት በዚህ ቁማር ተጫወተ። ይህን ያደረገው ጭንቅ ውስጥ ሆኖ፣ እየተሸነፈ ጭምር ነው። የፋኖ አመራሮች ይችን እንኳ እየተጫወቱባት አይደለም። የሰላም ምሽጋቸውን ለብልፅግና እየለቀቁለት ይመስላል።

7) ይህ ሁሉ ሆኖ፣ የሰላም ምሽግህን ለቅቀህ ነገ እደራደራለሁ ብትል በዲፕሎማሲው ገፅህ ይገረጣል። ደጋፊዎችህ እምነት ያጡብሃል። ብልፅግና ከለቀቅክለት ቦታ እየተንጎማለለ አንተ ወዳለበት እየሄድክህ እንደሆነ አድርጎ ያቀርብሃል።

8/ ያለ አለም አቀፍ ማህበረሰቡ አራት ኪሎ የሚታሰብ አይደለም። ባለፈው የአሜሪካ አምባሳደር ወቀሳ አቅርቧል። ብዙ ተቆርቋሪዎች ያን መግለጫ እንዲያርም በሚጥሩበት ወቅት ድካማቸው ላይ ውሃ የሚቸልስ፣ ዲፕሎማቶቹ ለወቀሳ የሚሆን ተጨማሪ ምክንያት እንዲያገኙ፣ ፋኖ ባንክ ዘረፈ ሲባል ባንክ እየጠበቀ ያገኛትን የዓለም አቀፍ እውቅና የሚያበላሽ የውድቀት መንገድ ነው። አራት ኪሎን የሚያስብ አካልም ድርድርን በዚህ መልክ አይገልፀውም። እውነተኛ ጥያቄ ተይዞ የድርድርን ምሽግ በድሮን ንፁሃንን ለሚጨፈጭፍ ኃይል መልቀቅ ሽንፈት ነው።

9) ሰው የጦር ሜዳ ጀግንነትን ብቻ ሳይሆን ብልጠትንም ከፋኖ መሪዎች ይጠብቃል። የወረዳና ቀበሌ ከተማ ተያዘ ተለቀቀ ብሎ ዜና የሚያጮህ ዩቱዩበኛ አልደራደርም ስትል ሊያሞካሽህ ይችላል። ግን አይጠቅምህም። ወደ ወጥመድ ነው የሚያስገባህ። ለአራት ኪሎ የሚበቃ ሀሳብ ሊሰጡ የሚችሉ ትልልቅ ወታደራዊም ፖለቲካ ልምድ ባለቤቶች "የልጆች ጨዋታ ሆነ" ብለው ይሸሹሃል። ቀሪው ህዝብ ሰላም እፈልጋለሁ ስላልክ በበጎ ያይሃል። አገዛዙ ነው በጥባጩ የሚለውን ትቶ አንተን አይወቅስም። አራት ኪሎ ለመግባት የሌሎች ትብብር ወሳኝ ነው። ዛሬ አልደራደርም ያልከው፣ ነገ ከእሱም ጋር አልደራደርም እንዳትል ይሰጋል።

10) አገዛዙ በአሁኑ ወቅት በጨፍጫፊነት እየተወገዘ ነው። "አልደራደርም" ስትል ከአሁን አጀንዳውን ከሰብአዊ ግፍ ሰላም ፈላጊ መስሎ ብቻ አይመጣም። የፈፀመውን ለማስረሳት፣ ከአሁን በኋላ የሚፈፀመውን በአንተ ምክንያት የመጣ ጭምር አድርጎ ያቀርባል። ቅሬታ ብታቀርብ "ለምን አትደራደርም" የሚባል ወቀሳ ይቀርብብሃል። የሰላም ምሽግህን ከለቀቅክ የተፈፀመብህን መከራ እንኳን እንዳትናገር የተጠመደብህ ወጥመድ ጭምር ነው።
3.7K viewsDan B, 15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ