Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-29 23:08:32
ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረቧ ተገለጸ!

ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረቧን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ የሰጡ ሲሆን፤ በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ ጥቅሞቿን ሊያስጠብቁ ከሚችሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር መስራቷን ትቀጥላለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ በብራዚል፣ ሩሲያ፣ ሕንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረቧ ተገልጿል።

"ብሪክስ ከኢትዮጵያ ለቀረበለት ጥያቄ አወንታዊ ምላሽ እንደሚሰጠን እንጠብቃለን።" ያሉት አምባሳደር መለስ፤ ከሌሎች ብሔራዊ ጥቅሞችን ሊያስጠብቁ ከሚችሉ ተቋማት ጋር መስራታችንን እንቀጥላለንም ብለዋል።

አባል አገራት ያቀረቡትን የእንቀላቀል ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጥ ተገልጿል።ሳውዲ አረቢያ፣ አረብ ኢምሬትስ፣ ኢራን፣ ቱርክ፣ ግብጽ እና አልጀሪያ ብሪክስን ለመቀላቀል ጥያቄ ካቀረቡ አገራት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
5.4K viewsAnt B, 20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 23:04:16
ሰበር ዜና

#EthioAmerican : የአሜሪካን መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ክሶች ማምሻውን ሙሉ በሙሉ አንስቷል:: ይህንን ተከትሎም ለኢትዮጵያ የተያዘው የልማት ፈንድ እንደሚለቀቅላት ታውቋል።
3.3K viewsAnt B, 20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 19:23:04
4.1K viewsAnt B, 16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 19:03:38
የኢትዮጵያ የባህር ሃይል ያሰለጠናቸውን ባህረኞች እያስመረቀ ነው

የኢትዮጵያ የባህር ሃይል በተለያዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን ባህረኞች እያስመረቀ ነው።

በመርሃግብሩ የጦር ሃይሎች ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ፣ የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ዋና አዛዥ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ፣ ጀነራል መኮንኖች፣ የነባር ባህር ሃይል አባላት፣ የተመራቂ ቤተሰቦችና የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የኢፌዴሪ አየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ከ30 አመት በላይ ተገለው እና አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ጀልባዎችን ዘመኑ የሚጠይቀውን የፈጣን ተዋጊ ጀልባ ቴክኖሎጂ እና መሳሪያዎች በመግጠም ለግዳጅ ዝግጁ ማድረግ መቻሉን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።

   
3.9K viewsAnt B, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 20:50:27
ከኢትዮጵያ እስከ ቻይና የተዘረጋው የወንጀል ሰንሰለት. ከኦሮሚያ እስከ ፌደራል ባለስልጣናት የሚሳተፉበት የቻይኖች የወርቅ መአድን ዘረፋ
1.4K viewsAnt B, 17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 03:29:54
2.4K viewsAnt B, 00:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 10:43:47
ኤርትራ ከኢትዮጵያ እና ከጅቡቲ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ዘጋች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ጋር የሚያገናኟትን አካባቢዎች ዘግታለች ሲል የብሪታንያ መንግስት ማስታወቁን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል። በኤርትራ የሚገኙ የታላቋ ብሪታንያ አካል የሆኑ ሀገራት ዜጎችም ሀገሪቱን ለቅቀዉ እንዲወጡ አሳስቧል።

ኤርትራ ድንበሯን የዘጋችበትን ምክኒያት ያላሳወቀዉ የብሪታንያ መንግስት ፤ ከሱዳን ጋር የሚያዋስናት ድንበር ክፍት መሆኑን እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚደረግበት እንደሆነ ገልጿል።

ኦም ሀጀር የተሰኘዉ እና ኢትዮጵያን ከኤርትራ ጋር የሚያዋስነዉ ቦታ ከተዘጉት አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በሰሜኑ ጦርነት ወቅትም ሆነ ከጦርነቱ በኋላ ክፍት የነበረ መሆኑ ይታወቃል። የብሪታንያ መንግስት እንዳስታወቀዉ ከሆነ ግን ኤርትራ በዚሁ በኩል ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ጨምሮ በባድመ እና አዲ ክዋህላ የተሰኙ አዋሳኝ ቦታዎችም ዘግታለች ብሏል።

የብሪታንያ መንግስት ዜጎቹ ከኤርትራ ድንበር 25 ኪሎሜትር ርቀት ባላቸዉ ማንኛቸዉም አካባቢዎች እንዳይንቀሳቀሱ መክሯል። በኤርትራ የሚገኙ ዜጎቹም ሀገሪቱን በአፋጣኝ ለቅቀዉ እንዲወጡ ፤ ወደ ሀገሪቱ ለመጓዝ ያሰቡም ጉዟቸዉን እንዳያደርጉ መምከሩን ዳጉ ጆርናል ከመግለጫው ተመልክቷል።

የብሪታንያ መንግስት ክልከላዉን ለማድረጉ ያስቀመጠው ምክኒያት ባይኖርም በኤርትራ ግን የሽብር ጥቃት ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት እንደሌለዉ ባወጣዉ መግለጫ ተናግሯል።
3.7K viewsAnt B, 07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 23:27:18
1.6K viewsAnt B, 20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 05:20:51 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02FKV59bjgrK4CDygh938m2r8xwqTscEHyrbUQBK8Z1fPD1qWgwrcPADxDRz1MG8Tdl&id=100084991505029&mibextid=NzXCef
3.6K viewsAnt B, 02:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-30 06:14:55
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወሰኑ ተቋማት አገልግሎቶችን ለግል ተቋማት በውክልና አስተላልፎ ሊያሰራ ነው  

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ መስሪያ ቤቶች፤ የተወሰኑ ስራዎቻቸውን በውክልና ለግል ተቋማት አስተላልፈው (outsource) ሊያሰሩ ነው። በዚህ አሰራር ምክንያት ከስራቸው የሚነሱ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞችን ወደ ሌሎች መስሪያ ቤቶች ለማዘዋወር እና “በሚፈልጉበት የስራ መስክ” እንዲሰማሩ ለመደገፍ መታሰቡም ተገልጿል።

አዲሱን አሰራር ተግባራዊ የማድረግ ሂደትን እየመራ ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ነው። በከተማ አስተዳደሩ ስር ያሉ መስሪያ ቤቶችን የአገልግሎት አሰጣጥ የመከታተል ኃላፊነት ያለበት ይህ ቢሮ፤ አዳዲስ አሰራሮችን የመዘርጋት ስልጣንም በአዋጅ ተሰጥቶታል። ቢሮው የተወሰኑ የመንግስት ስራዎችን ወደ ግል ተቋማት የማስተላለፍ እቅዱን በተመለከተ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ካሉ መስሪያ ቤቶች ጋር ዛሬ ሰኞ ግንቦት 21፤ 2015 ዓ.ም ውይይት አድርጓል።

ይህንን አሰራር በቅድሚያ እንዲጀምሩ በጥናቱ የተለዩ የከተማ አስተዳደሩ አምስት መስሪያ ቤቶች እና ስድስት ሆስፒታሎች መሆናቸው  በዛሬው ውይይት ላይ ተጠቅሷል። በቅድሚያ ወደ ተግባር ይገባሉ የተባሉት የንግድ፣ ትራንስፖርት፣ ገቢዎች እንዲሁም የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮዎች እና የአሽከርካሪ፣ ተሽከርካሪ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ውስጥ ያሉት የካቲት 12፣ ጥሩነሽ ቤጂንግ፣ ዳግማዊ ሚኒሊክ፣ ዘውዲቱ፣ ጋንዲ መታሰቢያ እና ራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታሎች የተወሰኑ አገልግሎታቸውን ለግል አካላት ከሚያስተላልፉት ውስጥ ተመድበዋል።
ዝርዝር https://ethiopiainsider.com/2023/11062/
5.3K viewsAnt B, 03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ