Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-30 06:14:54
በዋሽንግተንና አካባቢው ከሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ከንቲባ አዳነች ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋሽንግተን እና አካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ።

ከንቲባዋ በዩናይትድ ስቴትስ የተለያዩ አካባቢዎች ያደረጉትን ጉብኝት አጠናቀዋል።

በዋሽንግተንና አካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ባደረጉት ውይይ በአዲስ አበባ ስላለው የኢንቨስትመንት አማራጮች ጠቅለል ያለ መረጃም መሠጠቱን ገልፀዋል።

"በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች ከሚሰሙት የተዛቡ መርጃዎች በላይ በከተማችን አዲስ አበባ ትላልቅ ሰው ተኮር ስራዎች እና ሜጋ ፕሮጀክቶች መሰራታቸውን ጠቅሰናል" ያሉት ከንቲባዋ፥ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑም ለመሳተፍ ያላቸውን ፍላጎት መግለፃቸውን ነው ያስታወቁት።

በውይይቶቹ ላይ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የ200 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ለማድረግና ፕሮጀክቶቹም ተገንብተው እስኪጠናቀቁ በቀጣይነት ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባታቸውን አመልክተዋል።

በአሜሪካ ለነበራቸው ቆይታ ስኬታማነት አስተዋፅኦ ለነበራቸው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የዲያስፖራ አባላት ምስጋና አቅርበዋል።
3.7K viewsAnt B, 03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-26 19:54:43
5.1K viewsAnt B, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-26 19:54:41 General Migbie good job brother.
4.3K viewsAnt B, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-25 14:03:20
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት- አፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት ክብረ በዓል በአዲስ አበባ መከበር ጀመረ
************************

60ኛው የአፍሪካ አንድነት  ድርጅት - የአፍሪካ ህብረት የተመሰረተበት 60ኛ ዓመት ክብረ በዓል በአዲስ አበባ በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት በመከበር ላይ ነው፡፡

“የእኛ አፍሪካ የወደፊት ዕጣችን” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 60ኛው የአፍሪካ ቀን፣ የበለጸገች እና ሰላም የሰፈነባት፣ በራሷ ዜጎች የምትመራ እና በዓለም አቀፍ መድረክ የምትወከል አፍሪካን መፍጠርን ዓለማ አድርጎ ነው።

ይህም ህልማቸው አንድነቷ የተጠበቀ አፍሪካን ለመፍጠር፣ ሰላማዊት እና ተለዋዋጭ ኃይልን በዓለም መድረክ እና በተለይም ደግሞ ከቅኝ አገዛዝ ጋር የሚደረገውን ትግል የሚወክል መስራች አባሎቿን በማስታወስ ነው።

የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እ.ኤ.አ. በ1963 በኢትዮጵያ መመስረቱ ይታወሳል፡፡
7.0K viewsAnt B, 11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-23 21:26:03
ሰበር የአፈና መረጃ

አርቲስት ቤዛዊት መስፍን በጸጥታ ኃይሎች ተይዛ መወሰዷን ቤተሰቦቿ ለENN Media ገልጸዋል።
5.4K viewsAnt B, 18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-23 21:26:03 ቤዛዊት ታስራ ከሆነ መፈታት ይኖርባታል።
5.0K viewsAnt B, 18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-22 19:27:21
አዲስ አበባ እና ዴንቨር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14፣ 2015 (ኤፍ ቢሲ) የአዲስ አበባ እና ዴንቨር ከተሞች በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ስምምነቱ የሁለቱን ከተሞች ግንኙነት ይበልጥ በማጠናከር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ ለመስራት የሚስችል ነው ብለዋል፡፡

ከተማ አስተዳደሩ በዓለም የንግድ ቀን ፕሮግራም ላይም ኢትዮጵያን የሚያስተዋውቁ ምርቶችን ማስተዋወቁን ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች እና ልዑካቸው በዴንቨር ከተማ ለተደረገላቸው አቀባበል እና መስተንግዶ ለከተማዋ ከንቲባ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
5.9K viewsAnt B, 16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 11:38:54
የዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ሁሉን አቀፍ ትብብር እና አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ባንኩ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ወቅታዊ ግንኙነት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።
በመግለጫውም በኢትዮጵያ በተከሰቱ ግጭቶች እና በድርቅ ምክንያት በሚሊየን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክፉኛ መጎዳታቸውን እና የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ተፅዕኖ ውስጥ መውደቁን አንስቷል፡፡
በመሆኑም በኢትዮጵያ የተከሰቱ ችግሮችን ለመቋቋም የዓለም ባንክ ቡድን ከኢትዮጵያ ያለውን ሁሉን አቀፍ ትብብር እና አጋርነት እንደሚያስቀጥል ነው ያስታወቀው፡፡
ባንኩ ባለፉት አስርት አመታት በተደረጉ ሰው ተኮር ድጋፎች በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን እና አሁን ላይም ባንኩ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች መሰረታዊ የሰብአዊ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቅሷል፡፡
በመላ አገሪቱ ያለውን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተልኩ ነው ያለው የባንኩ መግለጫ ÷በሀገሪቱ የሰላም ግንባታን፣ እርቅን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያበረታቱ ጅምሮችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጿል።
2.1K viewsAnt B, 08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 13:06:41 በበጀት አመቱ 9 ወራት ምንም አይነት ቀጥተኛ የበጀት ድጋፍ ከውጭ የልማት አጋሮች እንዳልፈሰሰ የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በበጀት አመቱ 7.7 ቢሊየን ብር ቀጥተኛ የበጀት ድጋፍ እንደሚኖር ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም እስካሁን ምንም አለመገኘቱን ነው የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ያስታወቁት፡፡

ከሰሜኑ ግጭት ጋር ተያይዞ አጋር አገራት እና ተቋማት በተለይ ምእራባውያን መንግስት ላይ ጫና ለማሳረፍ በማሰብ ለኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ድጋፍ በአብዛኛው ማቀዛቀዛቸው ይታወሳል፡፡
በመሆኑም መንግስት ከአጋሮች ለወትሮው ሲያገኘው የነበረው ድጋፍ ባለፉት አመታት በከፍተኛ ሁኔታ ቅናሽ ታይቶበታል፡፡
3.0K viewsAnt B, 10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 03:46:14

3.2K viewsAnt B, 00:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ