Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-02-27 19:22:49 #Oromia

የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ባካሄደው  መደበኛ  ጉባኤው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ውሳኔዎቹ ምድናቸው ?

ውሳኔዎቹ ከከተሞች አደረጃጀት ጋር የተያያዘ ሲሆን ሁለትና ከዛ በላይ ከተሞችን አንድ ላይ እንዲደራጁ ተወስኗል።

1. ቢሾፍ ከተማ ፦ የቢሾፍቱ ከተማ፣ ዱከም ከተማ እንዲሁም የመዘጋጃ ቤት ከተሞች ሂዲ፣ ኡዴ ደንካካ እና ድሬ በመቀላቀል በ3 ክ/ከተሞች እና በ10 ወረዳዎች እንዲደራጅ ሆኗል፤

2. ሻሸመኔ ከተማ፦ የሻሸመኔ ከተማ እና የብሻን ጉራቻ ከተማ በመቀላቀል በ4 ክ/ከተሞች እና በ12 ወረዳዎች እንዲደራጅ ሆኗል፤

3. አዳማ ከተማ፦ የአዳማ ከተማ እና የወንጂ ከተማን በመቀላቀል በ6 ክ/ከተሞች እና በ19 ወረዳዎች እንዲደራጅ ሆኗል፤

4. ሮቤ ከተማ፦ የሮቤ ከተማ እና የጎባ ከተማን በመቀላቀል በ3 ክ/ከተሞች እና በ12 ቀበሌዎች እንዲደራጅ ሆኗል፤

5. ማያ ከተማ፦ የሀረማያ ከተማ፣ የአወዳይ ከተማ እና የአዴሌ ከተማን በመቀላቀል በ3 ክ/ከተሞች እና በ12 ቀበሌዎች እንዲደራጅ ሆኗል፤

6. ባቱ ከተማ፦ የባቱ ከተማ እና የአዳሚ ቱሉ ከተማን በመቀላቀል በ7 ቀበሌዎች እንዲደራጅ ሆኗል፤

ከዚህ ባለፈ ደግሞ የሚከተሉት ከተሞች ተጠሪነታቸው ለክልሉ መንግስት እንዲሆን ተወስኗል፡፡

1. መቱ ከተማ
2. አጋሮ ከተማ
3. ቡሌ ሆራ ከተማ
4. ነጆ ከተማ
5. ሰንዳፋ በኬ ከተማ
6. ሸኖ ከተማ
7. ሞያሌ ከተማ
8. ዶዶላ ከተማ
9. ሻክሶ ከተማ

ከዚህ ባለፈ የሚከተሉት ከተሞ ደረጃ እንደሚከተለው እንዲሻሻል ተወስኗል።

1. አዳማ፣ ሻሻመኔና ቢሾፍቱ ከተሞች፡- የሬጂዮ-ፖሊስ ከተማ

2. የሮቤ ከተማና የማያ ከተማ፡- ዋና ከተማ

3. የመቱ፣ አጋሮ፣ ቡሌ ሆራ፣ ነጆ፣ ሰንዳፋ በኬ፣ ሞያሌና ሻክሶ ከተማ፣- ወደ ከፍተኛ ከተማነት እንዲያድጉ ተወስኗል።

በሌላ በኩል የምስራቅ ቦረና ዞን አዲስ ዞን ሆኖ እንዲደራጅ ተወስኗል፡፡

በአዲስ መልክ 21ኛ ዞን ሆኖ የተደራጀው የምስራቅ ቦረና ዞን ዋና ከተማው ነጌሌ ቦረና ሆኖ፡-
• ከቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ፣ ሞያሌ ከተማ፣ ጉቺ ወረዳ እና ዋችሌ ወረዳ፣
• ከጉጂ ዞን ሊበን ወረዳ፣ ጉሚ ኤልደሎ ወረዳ፣ ነጌሌ ቦረና ከተማ፣
• እንዲሁም ከባሌ ዞን መደወላቡ ወረዳ፣ ኦቦርሶ ወረዳ እና ሀረና ቡሉቅ ወረዳ በመጨመር እንደ ዞን 10 ወረዳዎችን በመያዝ እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡

በአዲሱ አደረጃጀት የምስራቅ ቦረና ዞን በአዲስ መልክ የተደራጀ ሲሆን የጉጂ ዞን ዋና ከተማ አዶላ ሬዴ ሆኖ የቦረና ዞን ዋና ከተማ ደግሞ ያቤሎ ከተማ እንዲሆን ተወስኗል።

የመደ ወላቡ ወረዳ ደግሞ በሁለት ቦታ ማለትም የመደ ወላቡ ወረዳና ኦቦርሶ ወረዳ ሆኖ እንዲደራጅና የጭናክሰን ወረዳ የነበረው በሁለት ወረዳ የጭናክሰን ወረዳና የመከኒሳ ኦሮሞ ወረዳ ሆኖ እንዲደራጅ ተወስኗል።
2.1K viewsAnt B, 16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 23:59:24
ማኛው ስለጫማ ፖለቲካ አስተያየት ሰጠ
1.8K viewsAnt B, edited  20:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 04:09:23 ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፓሬሽን  የ14ኛውን ዙር የ20/80 እና የ3ኛውን ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት  እድለኞችን ከጥር 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ ውል ማዋዋል  መጀመሩ ይታወቃል።

በመሆኑም እስከአሁን በተቀመጠላቸው  የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቅፅ 09ን የወሰዱ የቤት ባለ እድለኞች ቁጥር 23,373 ሰዎች ሲሆኑ ቅፅ 09 ከወሰዱት መካከል ከሚኖሩበት ቀበሌ የሚጠበቅባቸውን ያሟሉ እና የክፍያ ማዘዣ ቅፅ 03 በመውሰድ ውል የተዋዋሉ 7,855 ያህል ናቸው።

ይሁንና ውል ማዋዋል ከተጀመረ አንድ ወር ያለፈው ቢሆንም ቅፅ 09ን  በመውሰድ ከመኖሪያ ቀበሌያቸው አስፈላጊውን መረጃ በሟሟላት ወደ አንድ ማእከል መመለስ እና የክፍያ ማዘዣ ቅፅ 03 ወስደው መዋዋል ላይ መዘግየት ተስተውላል። 

ስለሆነም ተዋዋዮች የመዋዋያ ጊዜው እየተገባደደ ስለሆነ ከመኖሪያ ወረዳችሁ አስፈላጊውን መረጃ ፈጥናችሁ በማምጣት የክፍያ ማዘዣ ቅፅ 03ን እየወስዳችሁ ውል መዋዋል እንዳለባችሁ እያሳሰብን ወረዳዎችም ለባለጉዳዮቹ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ለስራው መቃናት ተገቢውን ትብብር እንድታደርጉ እናሳውቃለን።

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
2.8K viewsAnt B, 01:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 08:45:58 ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል በስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ባካሄደው የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ የጸደቁ ውጤቶችን ይፋ በማድረግ ላይ ነው። ቦርዱ ትናንት የአማሮ ልዩ ወረዳ ውጤትን የጸደቀ ያሳወቀ ሲሆን፣ የልዩ ወረዳው ድምጽ ሰጪዎች በከፍተኛ ድምጽ "የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል" የሚሰኘውን አዲስ ክልል ለማቋቋም እንደወሰኑ ገልጧል። ቅዳሜ'ለት ይፋ በተደረገው የጸደቀ ውጤት፣ የደራሼ፣ አሌ፣ ባስኬቶና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች እና የኮንሶ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች በከፍተኛ ድምጽ አዲሱን ክልል ለማዋቀር መወሰናቸውን ቦርዱ አስታውቋል።
1.9K viewsAnt B, 05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 16:12:54
በአዲስ አበባ በሚካሄደዉ የአፍሪካ ሕብረት ጉባዔ  ላይ 35 ፕሬዝዳንቶችና 4 ጠቅላይ ሚኒስትሮች  ይሳተፋሉ ተባለ፡፡

በአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ላይ የ51 አገራት ልዑካን ቡድኖች   እንደሚሳተፉ ታዉቋል፡፡ በመድረኩ ላይ  35 ርዕሰ-ብሔሮች፣ አራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች፣ 11 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ 13 ቀዳማዊ እመቤቶችና 10 የዓለም አቀፍ ድርጅት ኃላፊዎች ይታዳማሉ  ተብሏል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ከነገ ጀምሮ 36ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ  መካሄድ ይጀምራል፡፡
ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ጉባኤው የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ጉዳይ ላይ በስፋት እንደሚመክር ተናግረዋል።

በጉባኤው የፀጥታ ምክር ቤት ማሻሻያ እና የተለያዩ የሕግ ሰነዶች ይጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። ቀጣዩ የአፍሪካ ሕብረት ፕሬዝዳንት ኮሞሮስ ከሴኔጋል ትረከባለች ብለዋል።
2.6K viewsAnt B, 13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 13:17:03
2.0K viewsAnt B, 10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 07:10:30 በኢትዮጵያ የሚዲያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ በሚገኙ ሁሉም የቴሌቪዥን እና የሬዲዩ ጣቢያዎች ባለፈው ቅዳሜና እሁድ መዝናኛ ፕሮግራሞቻቸውን ሳያስተላልፉ አሳልፈውታል።

የመዝናኛ ፕሮግራም በማሰራጨት ከሚታወቁት አርትና ኢቢኤስ በተጨማሪ ሌሎችም የተለያዩ ሰበቦችን በመስጠት የመዝናኛ ፕሮግራም ከማሰራጨት ሙዚቃ ከማጫወትና አዝናኝ ጉዳዩችን ለማቋረጥ የተገደዱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች በተላለፈ ጥሪ መሰረት ነው ተብሏል።
የቴሌቪዥን ጣቢያዎቹ ያቋረጡትን የመዝናኛ ፕሮግራም መቼ ማሰራጨት እንደሚጀምሩ የታወቀ ነገር የለም።
2.5K viewsAnt B, 04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 08:23:37
የዱባይ ማራቶን ውጤት።
ከ1 እስከ 10 ኢትዮጵያ
1.1K views@A, 05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 16:22:13
በሁለት ቀናት 50 ጋብቻ ፈረሰ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነቶች መረጃና ምዝገባ ኤጀንሲ ሁለት ቀናት ብቻ 50 ህጋዊ ጋብቻ በፍቺ ተጠናቀቀ።
በከተማ ደረጃ ከሰጣቸው አገልግሎቶች በዝርዝር የተቀመጠው አሃዝ በሁለት ቀናት የተከናወነ ፍቺ ሲሆን ምክንያቶች አልተገለጹም።
1.3K viewsAnt B, 13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 08:22:25
ኖቪ ኮምፕሌክስ ድንቅ ህንጻ መሃል አብነት ላይ አስገንብቶ አጠናቀቀ ። ለሽያጭም አቀረበ። የአፓርትመንትና የንግድ ቤት ግዥዎች እንኳን ደስ አላችሁ። እውነተኛና ከፍለው ቁልፉን የሚቀበሉበት ቀጠሮ የሌለው መልካም አጋጣሚ ተፈጥሯል። ይፍጠኑ!!

የቤቶን ቁልፍ ዛሬውኑ ይረከቡ
የመኖርያ ቤት ሽያጭ በመሀል ከተማ

አድራሻ ፦ አብነት ጆስ ሃንሰን / ዋና መንገድ ዳር
ሙሉ ለሙሉ ጥንቅቅ ብሎ የተገነባ G+9
99% የደረሠ
ከወዲያው የሚረከቡት
ከ178 ካሬ እስከ 252ካሬ ሜትር ስፋት እንደፍላጎትዎ አለልዎ።

ህንፃው የሚኖሩት አገልግሎቶች

ቴራስ፣ኢንተርኮም፣ ጋርቤጅ ሹተር፣ ሊፍት (2)፣ለሁሉም የህንፃው ክፍል ጀኔሬተር ፣ የውሀ ታንከር እንዲሁም
ፋርማሲ፣ባንኮች፣ ለንግድ ቦታም አመቺ ነው።

ሳይት ለመጎብኘት እና ቢሮ ለመምጣት
0978 -78-80-00
0911-43-50-58
5.1K viewsAnt B, 05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ