ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል በስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ባካሄደው የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ የጸደቁ ውጤቶችን ይፋ በማድረግ ላይ ነው። ቦርዱ ትናንት የአማሮ ልዩ ወረዳ ውጤትን የጸደቀ ያሳወቀ ሲሆን፣ የልዩ ወረዳው ድምጽ ሰጪዎች በከፍተኛ ድምጽ "የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል" የሚሰኘውን አዲስ ክልል ለማቋቋም እንደወሰኑ ገልጧል። ቅዳሜለት ይፋ በተደረገው የጸደቀ ውጤት፣ የደራሼ፣ አሌ፣ ባስኬቶና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች እና የኮንሶ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች በከፍተኛ ድምጽ አዲሱን ክልል ለማዋቀር መወሰናቸውን ቦርዱ አስታውቋል። 1.9K viewsAnt B, 05:45