Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.54K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-01-02 21:28:03
የኤምፔሪያል ተሻጋሪ ድልድይ የቀኝ ክፍል ለትራፊክ ክፍት ሆነ

ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው መስመር ላይ የሚገኘው የኢምፔሪያል ተሸጋጋሪ ድልድይ የቀኝ ክፍል ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል። የተሸጋጋሪ ድልድዩን የግራ ክፍል እና ሌሎች የመንገድ ግንባታውን ቀሪ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ይገኛል።

በቦሌ ሚካኤል፣ በኢምፔሪያል እና በለቡ መጋጠሚያ መንገዶች (inter change) ላይ የትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድይ (overpass) እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፣ ግንባታዎቹን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው።

ቀደም ሲልም ቦሌ ሚካኤል አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው የቀለበት መንገድ ተሸጋጋሪ የትራፊክ ማሳለጫ ድልድይ የግራ ክፍል ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት መደረጉ ይታወሳል።
1.6K views@A, 18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-02 10:32:10 ከላይ የሚታየውን ቲክቶክ ፎሎ እንድታደርጉ እጋብዛለሁ።
1.5K viewsAnt B, 07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-02 10:31:30 https://www.tiktok.com/t/ZTRbaLTs9/
1.5K viewsAnt B, 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-02 10:13:49
ህጋዊ እቃዎችን ሽፋን በማድረግ በኮምፒውተር ሞኒተር ውስጥ ተደብቀው የገቡ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች የኤሌክትሮኒከስ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋለ

በሞጆ ጉምሩክ ህጋዊ እቃዎችን ሽፋን በማድረግ በኮምፒውተር ሞኒተር ውስጥ ተደብቀው የገቡ 100 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ሀርዲስኮች እና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጉሙሩክ ኮሚሽን አስታወቀ

የዴስክ ቶፕ ኮምፒውተሮችን ሞኒተር ውስጡን ባዶ በማድረግ እና በምትኩ አዳዲስ ላፕቶፖችን እና ሌሎች የኤሌክትሮኒከስ እቃዎችን በማስገባት እና መልሶ በማሸግ በህገወጥ መንገድ ሊገቡ የነበሩ 100 ላፕቶፖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል

በተገኘው የፍተሻ ውጤት መሰረትም በሰነድ ላይ ያልተገለፀው ዕቃ የቀረጥና ታክስ መጠን ከ3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑን አቶ ፈረጃ ጠቁመዋል

የተፈፀመዉ የንግድ ማጭበርበር ተግባር በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ሲሆን በተያዘው እቃ ላይም የውርስ ውሳኔ የተሰጠበት መሆኑንም ም/ስራ አስሊያጁ አስረድተዋል

አቶ ፈረጃ አክለውም የስሪት ሀገርን ማሳሳት፣ ህጋዊ እቃዎች ሽፋንን በማድረግ ህገወጥ እቃዎችን ማስገባት እና ሌሎች የማጭበርበሪያ ስልቶችን በመጠቀም ከህጋዊ መንገድ ያፈነገጠ ስራ የሚሰሩ አንዳንድ አስመጭና ላኪዎች እንዳሉ ታውቋል

በዚህ መሰረት ባለፉት አምስት ወራት እቃዎች የጉምሩክ ስነ ስርዓት አጠናቀው ለነፃ ዝውውር ከተለቀቁ በኃላ የአስመጭዎችን የህግ ተገዥነት ለማረጋገጥ በድንገተኛ ፍተሻ እና የመረጃ ክፍሎች በተደረጉት የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች በየተለያዩ የማጭበርበሪያ ስልቶችን በመጠቀም መንግስት ሊያጣው የነበረ የቀረጥና ታክስ መጠኑ ከ320 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ማዳን መቻሉን ተናግረዋል፡
1.7K views@A, 07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 23:06:33
የኳስ ንጉሱ ፔሌ በ82 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

‘’የእግር ኳሱ ንጉስ’’ ተብሎ የሚጠራው ብራዚላዊው ኳስ ተጫዋች ፔሌ በ82 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ፔሌ በአለም ዋንጫ ታሪክ ሶስት የዓለም ዋንጫዎችን፣ በ1958፣ 1962 እና በ1970 ከሀገሩ ጋር የውድድሩ አሸናፊ በመሆን ብቸኛ ባለታሪክ ነው፡፡

ባለፈው አንድ ወር በአንጀት ካንሰር ሳቢያ ህክምና ሲደረግለት የቆየው ፔሌ ባለፈው ሣምንት አስጊ ሁኔታ ላይ እንደሆነ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሲዘግቡት እንደነበር ይታወሳል፡፡

በዚህም ኳስ ትታዘዝለታለች የሚባልለት የኳስ ጥበበኛው ፔሌ መትረፍ አልቻለም።
621 viewsAnt B, 20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 02:15:02
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ ለመሄድ በሁለት ቀን ውስጥ የተመዘገበ የሰው ብዛት 9ሺህ ሲሆን ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት የተመዘገበው የሰው ብዛት ደግሞ 27ሺህ ደርሷል።
2.8K viewsAnt B, 23:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 09:08:39
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ ነገ ታሕሳስ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ መቀሌ መደበኛ በረራ ማድረግ የሚጀምር መሆኑን አስታወቀ ።
5.5K views@A, 06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 09:17:18
ሰበር ዜና

በአፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ የሚመራ የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ወደ መቀሌ አቀና
***********************

በአፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ የሚመራ የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ወደ መቀሌ አቀና።

የልኡካን ቡድኑ ወደ መቀሌ ያቀናው የሰላም ስምምነቱን የትግበራ ሂደት ለመቃኘትና በስምምነቱ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች በታቀደው መሠረት እንዲፈጸሙ ለማድረግ ነው።

የልኡካን ቡድኑ ከሁለት ዓመት በኋላ ወደ መቀሌ የተጓዘ የመጀመሪያው የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ ልኡክ ሲሆን ስምምነቱ በመልካም ሁኔታ ላይ  እንደሚገኝ ማሳያ መሆኑ ታምኖበታል።

በልዑካን ቡድኑ የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን አባላትም ተካትተዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
400 viewsAnt B, 06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-25 21:14:38
1.3K viewsAnt B, 18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-25 11:44:05
ፖሊስ ተከሳሹን ፈልጎ እንዳጣ ቢናገርም ተከሳሹ ግን በድብቅ ችሎት እየገባ ክሱን አዳምጦ ይወጣ ነበር። 

አቢሲኒያ ባንክን የ6.1ሚሊዮን ብር አሳጥተዋል ተብለው በከባድ ሙስና ወንጀል ከተከሰሱ ከ 5 ተከሳሾች መካከል አንደኛ ተከሳሽ አይተንፍሱ እንዳሻው ይባላል።

ይህ ተከሳሽ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ በተደጋጋሚ ፖሊስ አፈላልጎ እንዲያቀርበው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ትዕዛዝ ተሰጥቶ ነበር።

በመጨረሻም ፖሊስ ተከሳሹን በመኖሪያ አድራሻው አፈላልጎ ማግኘት እንዳልቻለ ገልጾ መልስ መስጠቱን ተከትሎ ተከሳሹ በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግለት ተደርጓል። ከጋዜጣ ጥሪው በኋላ ተከሳሹ በችሎት አለመቅረቡን ተከትሎ በሌለበት መዝገቡ እንዲቀጥል ብይን ተሰጥቶ ነበር።

ይሁንና ግን ተከሳሹ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ የችሎቱ ዳኞች በአካል ስለማይለዩት ተደብቆ ችሎት እየገባ ምን እንደተባለ አዳምጦ ሾልኮ ይወጣ ነበር። በዚህ መልኩ ተከሳሹ ተደብቆ ሲገባ አንደኛዋ ተከሳሽ ለፍርድ ቤት ለሚገኙ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር እንዲያውሉት ብትጠቁማቸውም በቁጥጥር ስር ሳያውሉት ቀርተዋል። ተከሳሹም ሳይያዝ ከችሎት ወጥቶ ይሄዳል። ይህንን ሁኔታ ተከሳሿ ለችሎቱ ዳኞች ጥቆማ ሰጥታለች።

የችሎቱ ዳኞች አርብ ዕለት በነበረ ቀጠሮ ጉዳዩን ለማጣራት የተከሳሹ የአክስት ልጅ የሆነ በዚሁ መዝገብ ለቀረበ ግለሰብ ተከሳሹን በሚመለከት ጥያቄ አቅርበዋል።

''በቁጥጥር ስር ያልዋለውን አይተንፍሱ የሚባለው ተከሳሽ እዚህ ሲመጣ አይተኸዋል ወይ?'' ተብሎ የቀረበለት ግለሰብም በበኩሉ ''አዎ አይቼዋለሁ፣ እኔ እንደሚፈለግ አላቅም እንጂ ፍርድ ቤት እየመጣ ተከታትሎ ሲሄድ አይቻለው'' ሲል መልስ ሰጥቷል።
2.8K viewsAnt B, 08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ