Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.26K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-12-12 04:56:15
https://www.tiktok.com/@antenehabraham850/now/invite?_t=8Y6UxPCsNCt&_r=1
1.8K viewsAnt B, 01:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 11:22:13
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ/ባባ/ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነው አርቲስት ታሪኩ በህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉን ኢፕድ ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ለማረጋገጥ ችሏል።

አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት ነበረ።

አርቲስቱ ወጣት በ97፣ ወንድሜ ያዕቆብ፣ ላውንድሪ ቦይ፣ ማርትሬዛ፣ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣ አንድ ሁለት ፣ብር ርርር፣ ወደው አይሰርቁ፣ ወፌ ቆመች፣ እንደ ቀልድ ፣ወቶ አደር ፣አባት ሀገር እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል።

ለቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች መፅናናትን ይመኛል።
2.4K views@A, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 06:04:38
ማራቶን በዚህ ሁኔታ ተጠናቋል
2.2K views@A, 03:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 18:51:47
በጥሎ ማለፉ የሚደረጉ ጨዋታዎች ይሄንን ይመስላሉ።
3.3K viewsAnt B, 15:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 00:17:04 የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ተቋም የሎጀስቲክ ዋና መምሪያ ም/ዳይሬክተር እነ ተስፋዬ ዳባ በተጠረጠሩበት ከ20 ሚሊዮን ብር  በላይ የሙስና ወንጀል ክስ የመመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ።

በተጠርጣሪዎች ላይ ዓቃቢህግ ክስ እንዲመሰርት የ10 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ተፈቅዷል።

የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ተቋም የሎጀስቲክ ዋና መምሪያ ም/ዳሪክተር አቶ ተስፋዬ ዳባ ጨምሮ ሌሎችም ተጠርጣሪዎች በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር።

ተጠርጣሪዎቹ  ከብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ተቋም  ትዕዛዝ ባልሰጠበት ሁኔታ ሲሚንቶ ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል በማስመሰል የሲሚንቶ ወጪ በማድረግ  ለተቋሙ ሳይቀርብ  ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ለግል ጥቅም በማዋል ወንጀል መተጠረጠራቸውን ተከትሎ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እና በፍትህ ሚኒስቴር በሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳሪክቶሬት ጀነራል ሲያከናውን የነበረው ምርመራ መጠናቀቁን ተከትሎ ዓቃቢህግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ የመመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ለዓቃቢህግ ክስ መመስረት የሚያስችለውን የ10 ቀን ክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።
1.6K viewsAnt B, 21:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 13:59:18
ፀረ ሙስና ዘመቻ

<<በመዲናዋ የአርሶ አደር ልጆች ወይም የልማት ተነሽ ሳይሆኑ የሆኑ በማስመሰል በሐሰት ሙስና የሰሩ ግለሰቦች ተለይተዋል>> የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ

የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ በቀለን ጨምሮ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለስልጣናት በቁጥጥር ሥር ውለዋል

በቅርቡ የተቋቋመው የፀረ ሙስና ብሔራዊ ኮሚቴ ሥራውን በይፋ መጀመሩን አስመልክቶ የኮሚቴው አባላት በዛሬ ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫውም የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ በቀለን ጨምሮ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለስልጣናት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተነግሯል።

በአዲስ አበባም የአርሶ አደር ልጆች ወይም የልማት ተነሽ ሳይሆኑ የሆኑ በማስመሰል በሐሰት ሙስና የሰሩ ግለሰቦችም ተለይተዋል ብለዋል የብሔራዊ ኮሚቴው አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ።

175 ሺሕ ካሬ ሜትር ቦታና የኮንዶሚኒየም ቤት ምዝበራ የፈፀሙ እንዲሁም በፍትህ ዘርፉ ስልጣናቸውን በመጠቀም ከግለሰቦችና ከንግድ ተቋማት ጋር ለግል ጥቅማቸው ሲሰሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችም ተለይተዋል ተብሏል።

ኮሚቴው ሦስት ንዑስ ኮሚቴዎችን ማለትም የህግ፣ የመረጃ እና የፋይናንስ ንዑስ ኮሚቴዎችን በማቋቋም እቅድ አውጥቶ ሥራ መጀመሩንም የብሔራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጥሩነህ ተናግረዋል።

በመንግሥት አግልሎት አሰጣጥ፣ በፋይናንስና ግዥ፣ በፍትህ ስርዓቱ እና በመሬት አስተዳደር እንዲሁም በመሰረታዊ ፍጆታ አቅርቦት ዘርፎች ላይ ሙስና በከፍተኛ ኹኔታ እንደሚስተዋልም ገልጸዋል።

"የሌባ ትንሽ የለውም" ያሉት ተመስገን ጥሩነህ፤ ከመታወቂያ አሰጣጥ ጀምሮ ህብረተሰቡን የሚያማርሩት ላይ ጠንካራ እርምጃዎች እንደሚወሰዱም ተናግረዋል።
(ኢፕድ)
3.1K viewsAnt B, 10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 13:27:33
" ሌብነት የኢኮኖሚ ነቀዝ ነው፤ የዕድገት ነቀርሳ ነው" -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
2.7K viewsAnt B, 10:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 19:42:19
#ህውሃት ታጣቂዎች ለቀው የወጡት ግንባር
ከማይቅነጣል
ዛላምበሳ
ነበለት
ኩኩፍቶና
ሕጉምብርዳ ከተባሉ አካባቢዎች ታጣቂውን በከፊል ወደ ማዕከል መቀሌ አቅራቢያ እያሰባሰበ መሆኑን ድምፀ ወያኔ ዘግቧል።
5.2K viewsAnteneh Babanto, 16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 13:06:38 በመቀሌና ዙሪያዋ ብቻ ተወስኖ የቀረው የቡድኑ ታጣቂ እስካሁን አንድም ከባድ መሳሪያ አላስረከበም። በወሬና የማታለያ ምክንያቶች በመደርደር ቀጥሎበታል። ከባድ መሳሪያውን በአንድ ቀን ላለማስረከብ ምንም በቂ ምክንያት የሌለው ቢሆም። ለዳግም ልክስክስ ባህሪው አሳቻ ሁኔታን ለመፍጠርና ሌላ የደም ጎርፍ በምድሪቷ ለማስፈሰስ እየዶለተና ይገኛል።

እነሱ ብልጥ ሌላው ሞኝ ይመስላቸዋል። ከሚልዮኖች ደሆችንና የደሃ ልጆችን በከንቱ ማስጨረሳቸው ሳያንስ ሌላ በሰው ነፍስ የመቀለድ እድል ሊሰጣቸው አይገባም። ደጋግመው እንደሚሉት ትግራይ የመቃብር ቦታ የማድረግና ህዝቡንም የማስፈጀት ሰይጣናዊ ተልዕኮ ሊያቆሙ አይፈልጉም። ያገኙትን በሰላም የመኖር እድል ያባክኑታል። አሁንም ያላቸውን ኮልኮሌ ታንክና መድፍ በአንድ ቦታ ሰብስበው በማስረከብ ፋንታ ሰራዊታችንን በያለበት በመሰለል ስራ ተጠምደዋል። በውሉ መሰረት ትጥቅ ያልፈቱት  በምላሳቸው እየሸነገሉ አሞኘናቸው እያሉ ነው። ለአራተኛ ጊዜ ጦርነት ቢከፍቱ ዓለም እነሱን ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርጋቸው ይመስላቸዋል።

ትጥቅ ሳይፈቱ እርዳታውና የመሰረተልማት ዝርጋታው በፌዴራል መካሄዱ ፌዴራልን እንደጂል እንዲቆጥሩ አድርጓቸዋል። አረሳስተን ከነትጥቃችን እንቀራለን ብለውም ይመኛሉ። የጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫ መታጠቅ ከመገደልና ከማለቅ እንዳልታደጋቸው ይልቁንም ለሚዘምትባቸው ወገን አሳማኝ ምክንያት እንዲኖረው የሚያደርግ አደገኛ ነገር መሆኑን አልቱረዱትም። ታጠቁ አልታጠቁ ከምንም አያስጥላቸውም። ሰራዊቱ ቢሰማራ በ24ሰዓት ከነትጥቃቸው አመድ እንደሚሆኑ ቢያውቁትም የትጥቅ አፍቅሮቱ ሊቆርጥላቸው አልቻለም። ሌላ ህልም ላይ መቀላወጥ ላይ ናቸው። ስብሰባ እቅድ የጋራ እቅድ ውይይት ምክክር ኦሬንቴሽ እያሉ ከመዘላበድ ውጭ አንዲት መድፍ ለማስረከብ ፈቃደኛ አይደሉም። ሰራዊታችን በያለበት ቦታ ሁሉ በተቀናጀ ሁኔታ እየሰለሉት እንዴት በድጋሚ እንደሚያጠቁት እቅድ እያወጡና እየገመገሙ መሆኑን በውጭ በሚገኙ አባሎቻቸው መረጃ አሾልከዋል። የኤርትራ ጦርና የአማራ ልዩ ኃይል ይውጣልን መከላከያውን በህዝባዊ ማዕበል ከበን ትጥቁን እንቀበለዋለን እንጂ ከእነዚህ ጋር ማን ይኖራል ብለው እየተናገሩ ነው። የፌዴራሉ መንግሥት ቸልተኝነት በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ዋጋ አስከፍሏል። ጥንቃቄ ያሻል
4.9K viewsAnteneh Babanto, 10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 13:06:22
የህወሓት ታጣቂ ትጥቅ ያለቅድመ ሁኔታ እፈታለሁ ቢልም ለትጥቅ ያለው ፍቅሩ ቶሎ ሊቆርጥለት አልቻለም። ምክንያቶች በመደርደር ከትጥቁ ጋር ይንፏቀቃል። እቅድ፣ ዝርዝር እቅድ፣ የጊዜ ሰሌዳ ዝባዝንኬ እያለ በከንቱ ጊዜውን ያባክናል። ይሄም መዘግየቱ በመቀሌና በትግራይ ስልክና የባንክ እንዲሁም የአየር ትራንስፖርት እንዳይጀመር እንቅፋት ሆኗል።

4.5K viewsAnteneh Babanto, 10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ