የኤምፔሪያል ተሻጋሪ ድልድይ የቀኝ ክፍል ለትራፊክ ክፍት ሆነ ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው መስመር ላይ የሚገኘው የኢምፔሪያል ተሸጋጋሪ ድልድይ የቀኝ ክፍል ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል። የተሸጋጋሪ ድልድዩን የግራ ክፍል እና ሌሎች የመንገድ ግንባታውን ቀሪ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ይገኛል። በቦሌ ሚካኤል፣ በኢምፔሪያል እና በለቡ መጋጠሚያ መንገዶች (inter change) ላይ የትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድይ (overpass) እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፣ ግንባታዎቹን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። ቀደም ሲልም ቦሌ ሚካኤል አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው የቀለበት መንገድ ተሸጋጋሪ የትራፊክ ማሳለጫ ድልድይ የግራ ክፍል ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት መደረጉ ይታወሳል። 1.6K views@A, 18:28