Get Mystery Box with random crypto!

የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ታህሳስ 29 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ዘጠኝ ጊዜ | Skyline media

የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ታህሳስ 29 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ዘጠኝ ጊዜ መድፍ የሚተኮስ መሆኑን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ የሀገር መከላከያ የኪነ ጥበባት ስራዎች ዳይሬክቶሬት  አስታውቋል፡፡

ፖሊስ በተለያዩ ጊዚያት ባደረገው ቁጥጥር የጦር መሰሪያ የሚያዘዋውሩ ህገወጦች   በዓላትን ጠብቀው ርችትን ሽፋን አድርገው ልዩ ልዩ የጦር መሳሪዎችን እንደሚተኩሱ አረጋግጧል፡፡ 

ከዚህ ቀደም በአንድንድ ቦታዎች በርችት ምክንያት ጥፋትን ያስከተሉ አደጋዎች ማጋጣማቸውን ፖሊስ አስታውሶ ለህብረተሰቡ ሰላምና እና ደህንነት ሲባል እንዲሁም ርችት መተኮስ ለጦር መሳሪያ ለሚያዘዋውሩ ህገወጦች ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ ለህብረተሰቡ ሰላምና ደህነንት ሲባል ርችት መተኮስ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ህብረተሰቡ ርችት ባለመተኮስ አስፈላጊውን ትብብር እንዲሁም  ርችት በመተኮስ የህብረተሰቡን ፀጥታ የሚያውኩ  ሲያጋጥመው ለፖሊስ ሪፖርት እንዲያደርግ  የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላፏል፡፡