Get Mystery Box with random crypto!

ኑ እናንብብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የሰርጥ አድራሻ: @nuenanbib
ምድቦች: ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.11K
የሰርጥ መግለጫ

ማንበብ የስብዕና ልህቀትን ያጎናፅፋል!!
ማንበብ ምክንያታዊ እና የሰላ አእምሮን ያንፃል!!
በዚህ ቻናል
👉የስነ ልቦና ምክሮች
👉ግጥሞችና ወጎች
👉ሳይንስና ፍልስፍና
በብዛት ይቀርባሉ።
ወዳጆዎን የዚህ የንባብ ማዕድ ተካፋይ እንዲሆኑ በመጋበዝ ቻናሉን ይደግፋ።
ማንኛውም አስተያየት @NuEnanbib_bot ላይ ይላኩልን

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-10-06 21:00:49 የደስተኝነት ምንጭ

ምንጭ ፦ ደስታን የማግኘት ጥበብ
ትርጉም ፦ ዳኜ መላኩ

ህይወት ባልተጠበቁ ድንገተኛ አጋጣሚዎች የተሞላች ሂደት ነች፡፡ ደስታም ሆነ ሀዘን ባልተጠበቀ መልኩ ወደ ህይወታችን ሰተት ይላል፡፡ ድንገተኛ እድልና ብልጽግና ሲመጣ ልቦናችን በጊዜያዊ ሀሴትና ፌሽታ ይወጠራል፡፡ በተቃራኒው ድንገተኛ አደጋ በህይወታችን ላይ ሲያንዣብብ አንዳች ረብሻና ስሜታዊ ድንዛዜ በውስጣችን ይነግሳል። ይሁን እንጂ ጊዜያዊው ፌሽታም ሆነ ስቃይ በውስጣችን እንደተቀመጠ የሚጸና አይደለም፡፡ ሰው በተፈጥሮው ነገራትን በፍጥነት የሚዛመድ ፍጡር በመሆኑ ከስኬቱም ሆነ ከውድቀቱ በቀላሉ ይላመዳል። ፈጠነም ዘገየ ድንገት የተከሰተው ሀሴትም ሆነ ሀዘን ተንኖ ወደተለመደው የስሜት ይዞታ መመለሳችን አይቀሬ ይሆናል፡፡

ይህ ነገራትን የመላመድ ተፈጥሯችን በእለት ተእለት ህይወታችን ውስጥ ሳያቋርጥ የሚስተዋል ክስተት ነው፡፡ የደሞዝ ጭማሪ ሊደረግልን፣ አዲስ መኪና ወይ ቤት ስንገዛ ወይም አዲስ ፍቅረኛ ስንተዋወቅ ለተወሰኑ ሳምንታት
ስሜታችን በሀሴት ይሞላል። ህይወታችን በአዲስ መልኩ የታደሰ ይመስለናል፡፡ ሆኖም ብዙም ሳይቆይ ይህ የህይወት ወረት ቀስ በቀስ እየተቀዛቀዘ ሄዶ ወደተለመደው የስሜት ይዞታ እንመለሳለን፡፡

አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ህይወት የተገላቢጦሽ ትሆናለች፡፡ ምናልባት የእለት ተእለት ገቢያችን ይመናመናል፣ ከወዳጅ ባልደረቦች እንጋጫለን ወይም በሆነ አይነት ችጋርና መከራ እንከበባላን። እናም በሀዘንና ትካዜ መንፈሳችን ይታወካል። ሆኖም ከተወሰነ ቆይታ በኃላ ነገራት ቀስ በቀስ እየቀለሉ ወይም ከእውነታው እየተላመድን ስንሄድ መንፈሳችን ታድሶ ውስጣችን ይደረጃል፡፡

ከጊዜያዊ ስሜቶቻችን ባሻገር ሁሌም ወደተለመደው የህይወት መስመር የምንመለስ ከሆነ « በርግጥ መሰረታዊውን የደስተኝነት ባህሪ የሚወሰነው ምንድን ነው?” የሚል መሰረታዊ ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም።

በመስኩ ላይ ጥናት ያደረጉ የስነ ልቦና ተመራማሪዎች እንደሚገልጹት የሰዎች ባህሪ በብዙ መልኩ ከወላጆቻቸው በሚወርሱት ጂን ወይም ስነ ህይወታዊ ዘረ-መል የሚወሰን እንደሆነ አንዳንድ ሰዎች በቀላሉ የመደሰት ተፈጥሮ ሲኖራቸው፣ አንዳንዶች በተቃራኒው
ጭንቀትና ድብርትን የሚገፋፋ ባህሪ ይዘው ይፈጠራሉ፡፡ የተለያየ ቦታ ተራርቀው በሚኖሩ መንትዮች ላይ የተደረገ የባህሪ ጥናቶች እንዳመለከቱት ከአስተዳደግና ከባቢያዊ ሁናቴዎች በተለየ መልኩ የሰዎች ስነ-ህይወታዊ ዘረ-መል የደስታና የጭንቀት ባህሪያቸውን እንደሚወስን ጠቁመዋል፡፡

ከወላጆች የምንወርሰው ተፈጥሯዊ ባህሪ በስብዕናችን ላይ መልከ- ብዙ ተጽእኖ እንደሚኖረው እሙን ቢሆንም፣ አእምሯችንንና አመለካከታችንን በመለወጥ የደስተኝነት ስሜትና ባህሪያችንን ማሻሻል እንደምንችል የስነ ልቦና ባለሞያዎቹ ይገልጻሉ፡፡

በርግጥ ለደስተኝነትም ሆነ ለደስታ ማጣት መሰረታዊው መንስኤ ሁኔታዎችን የምንመለከትበት መንገድ ነው፡፡ በህይወታችን ውስጥ ከሚከሰቱ አጋጣሚዎች በላቀ አጋጣሚዎቹን የምንመለከትበት መንገድ ውስጣዊ ስሜታችንን ይወስነዋል።

ደስታን የመሻት መሰረቱ ውስጣዊ አመለካከትና ባለን ነገር የመርካት ልምድ ነው።

እራስን ማነጻጸር

በውድድር በተሞላ ማህበራዊ ስርአት ውስጥ እንደማደጋችን ከህይወት የምናገኘው እርካታ እራሳችንን አነጻጽረን በምናገኘው ውጤት ላይ የተመሰረተ ነው። ያለንበት ደረጃ በፊት ከነበርንበት የተሻለ ሆኖ ሲገኝ ደስታ ይሰማናል። ካለፈው በባሰ ሁኔታ ላይ የምንገኝ መስሎ በታየን ቁጥር ደግሞ በራሳችን እንከፋለን፡፡ አመታዊ ገቢያችን ከሀያ ወደ ሰላሳ ሺህ ሊያድግ ደስተኛ እንሆናለን፡፡ ሆኖም ከጥቂት ወራት በኋላ ስሳሳው አንሶን አርባ ሺህ መመኘት ስንጀምር በርግጥ የህይወት እርካታ በአመታዊ ገቢያችን ላይ የተመሰረተ እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡

የውድድር አባዜው የራሳችንን ህይወት በማነጻጸር ብቻ የሚያበቃ አይደለም፡፡ ከራሳችን ባለፈ በዙሪያችን ያሉ ወዳጅ ባልደረባዎቻችንን እንፈካከራለን። ያገኘነውን ያህል ብናገኝ ጎረቤታችን የተሻለ ካገኘ በገቢያችን ደስተኛ አንሆንም፡፡ በአመት ሁለት ሶስት ሚሊዮን የሚያገኙ ፕሮፌሽናል አትሌቶች ሳይቀሩ ሌሎች ከፍተኛ ተከፋዮችን እየጠቀሱ ገቢያቸውን ያማራሉ። በርግጥ ኤች.ኤል. ማንኬን በአንድ ወቅት ‹‹ሀብታም ማን ነው›› ተብሎ ሲጠየቅ ‹‹የሚስቱን እህት ባል በመቶ ዶላር የሚበልጥ ሰው ሁሉ ሀብታም ነው›› ብሎ ነበር፡፡

እራሳችንን ከቢጤዎቻችን የምናወዳድረው በገቢ ወይም በሀብት ብቻ አይደለም፡፡ በመልክ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በትዳር፣ በቤታችን ስፋት... በማንኛውም ረገድ እራሳችንን ከሌሎች እናነጻጽራለን፡፡ እናም ደስታና እርካታችን በዚህ የንጽጽር ውጤት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡ ከህይወት የምናገኘው እርካታ በራሳችን ማንነት ሳይሆን በምንፎካከራቸው ሰዎች ማንነትና የኑሮ ደረጃ የሚወሰን ነው። በመልክ ወይም በአስተሳሰብ ከራሳችን የተሻሉ ሰዎች ስንመለከት ወይም ከእኛ በተሻለ ስኬታማ የሆነ ሰዎች ስናይ የቅናትና ደስታ የማጣት ስሜት ይወረናል፡፡

ደግሞም እራሳችንን የምናነጻጽረው ከሚበልጡን፣ ቢያንስ ከሚመጣጠኑን ሰዎች እንጂ ከሚያንሱን ጋር አይደለም፡፡ ምናልባት ከእኛ ከፍ ያሉትን ትተን ዝቅ ብለው የሚገኙትን ብንመለከት ህይወት የሰጠችንን ገጸ በረከት አመስግነን እንቀበል ነበር፡፡ ከእኛ የከፋ የህይወት እጣ ፈንታ የወደቀባቸውን ሰዎች ብንመለከት በርግጥ ባለን ነገር መርካት፣ በህይወታችን መደሰት እንጀምር ነበር፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
313 views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 13:13:57 የነዳጅ ኮንትሮባንድ ለመከላከል "ነዳጅ ላይ ጭማሪ ማድረግን" እንደመፍትሔ መጠቀም፥
በሞተር ሳይክል የሚፈፀምን ወንጀል ለመግታት "ሞተር ሳይክል" ላይ እቀባ መጣልን እንደመፍትሄ መቁጠር፥
ወንጀለኞችን ለማቆም "ከአማራ ክልል ወደ አዲሳባ የሚገባ መኪናን" አቁሞ ህዝብ ማጉላላት እንደመፍትሄ ማሰብ፥
መታወቂያ ማደስና ማውጣትን በመከልከል ሕገወጥነትን ለመግታት መሞከር፥
የገንዘብ እጠረትን ለመቅረፍ ገንዘብ አትሞ በመርጨት ኢንፍሊሽን ማምጣትን እንደመላ መውስድ.....

ብቻ መንግስታችን እግዚአብሔር የባረከው እና በአስተዋይነቱ ወደር የማይገኝለት ነው።

@Tfanos
587 views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 00:46:27 # የሟቹ_ኑዛዜ

የምንዱቡን ትንፋሽ ፥ ሞት በግፍ ቢነጥቅም
ሟች ቀኑን ያጣ ቀን ፥ ገዳዩ አይታወቅም ፤

አፋኙ ጣረ ሞት
አንደበቱን ይዞ ፥ ነፍሱን የነጠቀው
በምን ይናገራል ፥ ገዳዩንስ ቢያውቀው ፤

ብቻ ጀምበር ዕድሜው
በመአልቱ ጽልመት ፥ ማልዶ የታገተ
እስከ ሽበት ደርሶም ፥ አፍ ሳይፈታ ሞተ ፤

ምናልባት ምናልባት ፥ እንደ መልካም ዕጣ
ድንገት በለስ ቀንቶት ፥ የኔም ቀን ከመጣ
ሚጠይቁም ካሉ
ያሟሟቱ ነገር ፥ እንዲህ ነበር በሉ
.
''ሲለው መሶብ መስሎ ፥ ጎድሎ እንዳጎደለው
ሲሻውም ቀን ሆኖ ፥ ከፍቶ እንደበደለው
እድሜውን በልቶ ነው ፥ ዘመን የገደለው"
------------------------//-----------------------

( ኢዛና መስፍን Ezana Mesfin )
("የዜማ ናፍቆት" የግጥም ስብስብ፣2010 ዓም)

@NuEnanbib
1.0K views21:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 08:38:25 «ምኞት በጥም የተቃጠለ
ሰው የሚጠጣው ጨዋማ ውሃ ማለት ነው>>

ምንጭ ፦ጥበብ ፭
ፀሀፊ ፦ ጲላጦስ (ሀይለጊዮርጊስ ማሞ)

የሰው ልጅ ንፁህ የሆነውን የቡድሀ ተፈጥሮውን የሚያረክስበት ሁለት መንገድ እንዳለው የቡድሀ ትምህርት ያሳየናል። እነዚህ ሁለት መንገዶች በዓለማዊ ፍላጐት ከመያዝ እንደሚመነጩ የሚነግረን ቡድሀ እነሱም፡- «የመጀመሪያው፡- ሰው ስለእያንዳንዱ የሕይወት ጉዳይ የሚሰጠው ትርጓሜና ከዚያም በሚመነጨው ክርክር የሚደርስበት ውሳኔ ግራ መጋባትን ስለሚፈጥርበት የሕይወት መርከስ ውስጥ መግባቱ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ በሕይወቱ ታላቅ ዋጋ ያለውን ጉዳይ በመጣል ስሜቱ እንደመራው ሲጓዝ እንዲሁ በግራ መጋባት ተጠምዶ እርኩሰትን መሞላቱ ነው» ይላል።

«እንግዲህ አስቀድሞ በፍላጐት በመወሰድ ቀጥሎም ያሰቡትን በመኖር የሚገባበት ግራ መጋባት የሰው ልጅ የመከራው ምክንያት መሆኑን ታውቁ ዘንድ ይገባል። ነገር ግን አሁንም የዚህ ሁሉ ርኩሰት ምንጩ «አላዋቂነት (ስንፍና) እና ከንቱ ምኞት ነው» የሚለን ቡድሀ፦ የሰው ልጅ በፍላጎቱ ተወስዶ የሚገባበት ግራ መጋባት መሠረቱ አላዋቂነት ሲሆን፣ በኑሮው የሚገባበት ግራ መጋባት ደግሞ መሠረቱ ከንቱ ምኞቱ ነው» ይላል፡፡ ...

የሁለቱ ተጣምሮ በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ መገኘት ብዙዎች ለሚገኙበት መከራ ምክንያቱ እንደሆነ የሚያስተምረን ቡድሀ የሰው ልጅ ከእውቀት በራቀ መጠን በትክክልና እንደሚገባው ማሰብ እንደማይችልና ከምኞቱ ተጣብቆም እሱን ሲከተል ግራ መጋባትን ዕጣ ፈንታው አድርጐት እንደሚቀር ይነግረናል። ብዙዎች በልማድ ግራ መጋባት እየተነዱ ለጊዜያዊ ደስታ ሲራቡ የመስተዋሉ ምስጢርም ይኸው ነው፡፡ እንደቡድሀ ትምህርት አንዳንዶች የሥጋቸውን ሞት እስከመሻት የሚያደርሳቸው ይኸው የሕይወት ግራ መጋባት እንደሆነም ያሳየናል፡፡

«እንግዲህ» ይለናል ቡድሀ «የሰው ልጅ በፍላጐቱ በመወሰዱና በተወሰደውም በመኖሩ ስግብግብነት፣ ቁጣ፣ ስንፍና፤ አለመግባባት፣ ሐዘን፣ ቅናት፣ ሽርደዳ፣ ማታለል፣ ኩራት፣ ትዕቢት፣ ራስን መውደድ በየትውልዱ እየተገለጡ የሚታዩ የማንነቱ ተናጋሪ ሆነዋል» ይላል።

«የስግብግብነት ምንጩ ለራስ እርካታን ከማግኘት የሚመነጭ የተሳሳተ ሐሣብ ነው፤ ቁጣም እንዲሁ ከተሳሳተ ሐሣብና የሚገኙበትን ደረጃ ካለመረዳት የሚመነጭ የአስተሳሰብ ውጤት ነው፤ ስንፍናም ቢሆን ትክክለኛው ባህርይን ለይቶ ከአለማወቅ የሚወጣ ስሜት ነው» የሚለን ቡድሀ «ስግብግብነት፣ ቁጣና ስንፍና ሦስቱ የዓለም እሳቶች መሆናቸውን ተረዱ» ይለናል።

«የስግብግብነት እሳት ሁሉን ነገር ለራስ በመመኘት አእምሮአቸው የተዋጠ ሰዎችን የሚበላ ሲሆን፤ የቁጣ እሳት ደግሞ በሕይወት ጉዳይ በመብሰልሰልና በመናደድ ሕሊናቸው የተሸነፈ ሰዎችን ሲውጣቸው ይስተዋላል፡፡ የስንፍና እሳትም እንዲሁ የቡድሀን የሕይወት መንገድና ሐሣብ ባለመረዳት በራሳቸው መንገድ ሲሄዱ የሚሸነፉትን ሰዎች የሚያነድ ነው» ይላል ቡድሀ፡፡

እርግጥ ነው ይኸን ዓለም የሚያነዱ ለቁጥር የበዙና ዓይነታቸው የትየለሌ የሆነ የእሳት ዓይነቶች መኖራቸውን ቡድሀ ሲነግረን ከእነዚህም ውስጥ ከስግብግብነት፣ ከቁጣ፣ ከስንፍና ባሻገር ራስን የመውደድ፣ የሽምግልና፣ የበሽታና የሞት፣ የሐዘን፣ የሰቆቃ፣ የመከራና ስቃይ እሳቶች ዋነኞች ናቸው፡፡ በምድራችን አራቱም አቅጣጫ ይኸ እሳት እየነደደ ነው፡፡ እሳቱ ራስን ከማቃጠል አልፎም ለሌሎች ሐዘንና መከራን እንዲሁም ሰቆቃን ማትረፉን ስናስተውል በእሳቱም የተቃጠሉት ቁስል እያመረቀዘ የሚወጣው መርዝ በክፋት መንገድ አያሌዎችን ዘወትር ሲመራቸው ይኖራል፡፡

«የስግብግነት መዘዝ እርካታን ከመሻት፣ ቁጣ ደግሞ እርካታን ከማጣት የሚመነጩ የሰው ስሜቶች ሲሆኑ ስንፍና ደግሞ ከአደፈ አስተሳሰብ መመንጨቱን ልብ በሉ» የሚለን ቡድሀ «የስግብግብነት መንፈስ ጉድፉ ጥቂት ቢሆንም በቀላሉ የማይላቀቁት ችግር ነው፤ የቁጣ መንፈስ ደግሞ ጉድፉ እጅግ የበዛ ቢሆንም ለመላቀቅ ግን አስቸጋሪ አይሆንም፤ የስንፍና መንፈስ ጉድፉ የበዛ እንዲሁም ለመላቀቅ አስቸጋሪ መሆኑን ተረዱ» ይለናል፡፡

ስለዚህም የሰው ልጅ እውነተኛ እርካታን ለማግኘት የቡድሀን ትምህርትና ዕውቀት በማግኘት ቅንነትን፣ ባለው ረክቶ መኖርን እንዲሁም ታጋሽነትን እንዲለማመድና የራሱን የሰላም ዓለም መመስረት እንዲችል የሚነግረን ቡድሀ ለሰው ልጅ መከራ ውስጥ መዘፈቅ ስግብግብነት፣ ቁጣ እና ስንፍና ዋነኛ መሠረቶቹ እንደሆኑ በሚገባ እንድናውቃቸው በማስተማር ወደሌላ ርዕሰ ጉዳይ ይዞን ይሻገራል፡፡

«የሰው ልጅ ምኞት ገደብ የለሽ ነው፡፡ ምኞት በጥም የተቃጠለ ሰው የሚጠጣው ጨዋማ ውሃ ነው፤ ጨዋማ ውሃ የውሃ ጥምን አለማርካት ብቻ ሳይሆን ጥሙ እየጨመረ እንዲሄድ ማድረጉ የማይቀር ነውና። ስለዚህም የሰው ልጅ የእርካታ ምንጩ ከውስጡ ነው፤ በምኞቱ ግን አለመርካት ብቻ ሳይሆን ስቃዩም እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለምኞትህ ልጓም አብጅለት:: ምኞትህ ከጨመረ ቁጣህ ደስታና እርካታ እየቀነሰና እየከፋ ከመሄዱም ባሻገር መጨረሻህ ወደ እብደት መድረስ ብቻ ይሆናል» የሚለን ቡድሀ «ምኞታቸውን ለማርካት ሰዎች ዘወትር ሲሮጡ ስንመለከት ውጤታቸው አንዱ በሌላው ላይ ማሴር፣ መንግሥት በሌላው ላይ ሠራዊት ማዝመት፣ ወላጆች በልጆቻቸው ላይ መነሣት፣ ወንድም በወንድሙ ላይ ለጥፋት ማድባትና ወዳጅ የወዳጁን መቃብር መቆፈር ናቸው፡፡ በአጭሩ እርስ በርስ መጋደልና መጠፋፋት የዘወትር
ተግባራቸው ይሆናል» ይላል፡፡

«ልብ በሉ! ሰዎች ሕይወታቸውን የሚያለሙበትም ሆነ የሚያጠፉበት ዋነኛ ምክንያት ምኞታቸው ነው:: ማታለል፣ መስረቅ፣ ዝሙት፣ ከዚያም ተይዞ በውርደትና በሐፍረት መሰቃየት የምኞታቸው ዘር የሚያሳጭዳቸው አዝመራ ነው:: በራሳቸው ገላና ቃል ኃጢአትን ይፈፅማሉ:: በአእምሮአቸው የሚፈፅሙት ኃጢአት መጨረሻው በሥጋና ነፍሳቸው ሐዘንና መከራ እንደሚያተርፍላቸው ሲያውቁት እንኳን ይኸንኑ ከመፈፀም ወደኋላ አይሉም። መጨረሻቸውም በመከራ ዓለም ገብቶ በዚያ መካከም ይሆናል» ይላል ቡድሀ።

ቡድሀ ወደሌላው የከፋ ዓለማዊ ምኞት ሲወስደን የምናገኘው ጉጉትን ነው:: ለቡድሀ ሌሎች ዓለማዊ ምኞቶች ሁሉ የሚፈሱት በጉጉት ቦይ ውስጥ ነው:: ከፍ ያለ ጉጉት በሥጋህ ነፍስን ሲዘራ ሌሎች ምኞቶች የሚበቅሉበት ለም አፈር ይሆናል፡፡ ጉጉት የሰው ልጅ መልካም ተግባራትን ሁሉ በልቶ የሚጨርስ አንበጣ ነው፡፡ መልካሙ የአትክልት ሥፍራ የተንቀሳቀሰው የእባቡ መርዝ ይኸው ጉጉት ነው፤ ውበትን ብቻ በመሻት ወደዚያ የሚመጡትን ሁሉ ጉጉት ሲመርዛቸው ዘመናት ተቆጥረዋል። ጉጉት የሚያንቀው ነገር ከፊቱ እስኪቆም ድረስ እንደወይን ዛፍ ቅጠሉንና ቅርንጫፉን እያሰፋ የሚሄድ ተክል ነው። ጉጉት በሰው ልጅ ስሜትና ሐሣብ ውስጥ የሚሰነቀር ሰንኮፍ ሲሆን ልብንና አእምሮን በዝግታ የሚገድል መርዝም ነው፤ ጉጉት በክፉው ሰው መንፈስና በሰነፍ ሕይወት ውስጥ ተዘርቶ የሚበቅል ዘር ነው፡፡

«ይኸንን ተረዱ! ደረቅ አጥንትን በደም ለውሳችሁ ለውሻ ብትጥሉ ውሻው እስኪደክመው ድረስ ከአጥንቱ ጋር ታግሎ ጥሎት ይሄዳል፤ እንዲሁም ጉጉት ለሰው ልጅ ለውሻው እንደተሰጠው አጥንት ነው፤ ሕይወቱን በመከራ እንዲገፋ አድርጎት እንዲሁ ጥሎት እንዲሄድ ያደርጋል» ይላል ቡድሀ፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.1K views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 07:05:33 ከአሰልቺው ሰማይ ስር
( Abi.G )
ሰባኪው እንዳለው ፣ የሰው ትርፉ ድካም
የእድሜያችን ርዝመት ፣ በእርምጃ አይለካም
ቢለካስ ምን ሊኮን?
ምኞቱ ሳይሞላ ፣ የሞላ ወንዝ ወስዶት
ባጭሩ የቀረ ፣ ህልሙን ውሀ በልቶት
ወይ ከናቱ ማህፀን ፣ ማለም ሳይችል ገና
በውርጃ መኪና
መገጨት የሆነ ፣ የህይወት ፍፃሜው
ሳይራመድ ሟቹ ፣ ስንት ይሆናል እድሜው?
እግዞ!
የተራመደውም ፣ ተጉዞ ተጉዞ
መንገድ መርጦ ኑሮ ፣ ፍጥረት ሁሉ እንዳሻው
አለመጓዝ ሲሆን ፣ ጉዞው መጨረሻው
ስለምን ይጓዛል ?
ብልህ ለምን ለፍቶ ፣ ከንቱነት ይገዛል ?
እንጃ!
ግን በህይወት ፍርጃ
ጠንቋይ ቢጠነቁል ፣ የህይወትን ፍጥም
መሞቻውን አውቆ ፣ ከሞቱ አያመልጥም
ህይወት ርእስ ናት ፣ ሞት ለሚለው ግጥም!
ይሁና!
ይሄን ያሳብ መና
ተፈጥሮም አታጣም ፣ የሚችል ሊያፅናና
እድል እጣ ፈንታ
ጎኔን እየመታ
ወደ ምንምነት ፣ ቢችልም ሊያደርሰኝ
ምንምነት ራሱ
ምንም ነው 'ሚሆነው ፣ ከንፈርሽ ሲደርሰኝ!!
..
405 views04:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 18:16:59 እንኳን አደረሰሽ (ለኢትዮጵያ )

ከፀሀይ በታች፥  አዲስ ነገር ባይኖርም
መልካም አዲስ አመት፥ ማለት  አናቆምም።
ዘመን ባይለወጥ፥ አዲስ ቀን ባይወጣ
ከድጥ ወደ ማጡ፥  ቢሆንም የኛ እጣ ።
እንኳን አደረሰሽ ማለት አላቆምም
በሚመሩሽ እንጂ፥ እኔ ባንቺ አላዝንም ።

እንኳን አደረሰሽ እንደ አምና ፥ ካች አምና
ፀሀይም ባትኖር፥ ሌሊትሽ ባይነጋ
መላው መሬትሽም፥ ቢርስ በሰው እንባ
ዘመን ቢተካካም፥   አዲስ ቀን ባይወጣ ።

በእንጥፍጣፊ ተስፋ፥  ከልቤ በቀረው
እንኳን አደረሰሽ ፥ ዛሬም እልሻለው።

ኬቲኤል
1.7K views15:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 10:21:25 አንዳንድ ነገሮች ብዙ ያስገርማሉ።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ ትግራዊያን የሃይል ሚዛኑ ወደ መንግስት ሲያጋድል ሰላም ይሰብካሉ። ወደ ህወሃት ሲሆን ደግሞ ጦርነት ጎሳሚ ይሆናሉ። ከዛ ደግሞ አልተረዳችሁንም ይላሉ።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ የአማራ ሰዎች 'ትግሬዎች ህወሃትን ማስወገድ አለባቸው። አይጠቅማቸውም ገለመሌ' ይላሉ። እውነታው ግን ለአማራ ያልጠቀመውን ብአዴንን ማስወገድ ያልቻሉ መሆናቸው ነው።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ የጉራጌ ሰዎች 'የጉራጌ እጣ ፈንታ በጉራጌ ብቻ ይወሰን። እናውቅላችኋለን አትበሉን' ይላሉ። የወለኔን እና መሰል የማንነት ጥያቄዎችን ግን ይደፈጥጣሉ። 'በኛ ጉዳይ አትወስኑ' ባሉበት አንደበት በወለኔ ጉዳይ ፍርድ ይሰጣሉ።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ የኦሮሞ ተወላጆች የ19ኛውን ክፍለ ዘመን የሚኒሊክ ዘመቻ ያነሱና 'ኦሮሞ ተጨቁኗል፥ ኢትዮጵያ በድላናለች' ወዘተ ይላሉ። ነገር ግን በ16ኛው ክፍለ ዘመን በኦሮሞ መስፋፋት ዘመን የተፈጠረውን ነገር ማውራት አይፈልጉም።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ ጴንጤዎች 'ፀበል አያድንም' ይላሉ ነገር ግን ከበሽታቸው ለመፈወስ ከእዩ ጩፋ ዘይት በ1ሺ ብር ይገዛሉ።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ ሙስሊሞች 'ሰሜኖቹ ክርስቲያናዊ መንግስት ለማቋቋም ስለሞከሩ ሊወገዙ ይገባል' ይላሉ። በተቃራኒው በጅማ እና በሃረር ተቋቁሞ የነበረውን እስላማዊ መንግስት ያሞግሳሉ። (ለኔ ሲሆን መብት ላንተ ሲሆን ጥፋት የሚል ሎጂክ

ለምሳሌ፥ አንዳንድ ኦርቶዶክሶች 'ጴንጤዎች በመዝሙር ይጨፍራሉ' ይላሉ። ነገር ግን በንግስ ቀን ይሰክራሉ፥ ይጨፍራሉ፥ ይዘሙታሉ።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ ኤቲስቶች 'አለምን እግዚአብሔር ፈጠረ' የሚለው ተረት ነው ይላሉ። በተቃራኒው 'አለም ከአንዲት ቅንጣት ተፈጠረች' የሚለውን ተረት ያምናሉ።

ለምሳሌ፥ አንዳንድ አማኞች 'ኹለት የፍልስፍና መፅሐፍ አንብባችሁ አምላክ የለም አትበሉ' ይላሉ። በተቃራኒው አንዱን የሃይማኖታቸውን መፅሐፍ በቅጡ ሳያነቡ አምላክ አለ ማለታቸውን ይረሳሉ


@Tfanos
1.8K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 10:17:50 ግራ ዘመን
(ተስፋኣብ ተሾመ)

ላይ ላዩን ሲታይ የኛ ዘመን ጥሩ ይመስላል። በትክክል ግን ግራ አጋቢ  ዘመን ነው። የማይጨበጥ ዘመን!

ዛሬ ላይ አላስፈላጊ መተራመስ ውስጥ ነን፥ እርጋታ የለም፥ የጋራ እሴት የለም።  ግለሰባዊነት ማበቡ ያልበቁ ግለሰቦች እንዳሻቸው እንዲፈነጩ አድርጓል። ያልተማሩቱ መምህራን የሚሆኑበትን እድል አግኝተዋል። ራሱን ለመግዛት ያልታደለ የመንጋው አውራ ለመሆን በሚያደርገው ትግል የተነሳ መንጋው ታምሳል። እውነተኛ ተመሪ ልከኛ መሪ የለም። ልክ ያልሆነ ቦታ መቀያየር ተፈጥሯል

በመረጃ ጎርፍ ብንጥለቀለቅም እውቀት አልሆነንም። ጥራዝ ነጠቅ አደረገን እንጂ!
በየሴኮንዱ ከሚለቀቀው መረጃ መኻከል እውነት የሆነውን የመለያ ጥበብ አላዳበርንም። ትርምስ ብቻ።

ዘመናችን ግራ አጋቢ ነው። በግራ አጋቢ ዘመን በግራ መጋባት እየተራመስን ነው። ትርምስ ብቻ!

ዘመን መዋጀት ይኹንልን!


https://t.me/Tfanos
1.5K views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 07:07:07 አገር እንቁጣጣሽ

አገር እንቁጣጣሽ
የ'ዳ ክንድሽ አቅፎኝ
ያሳር ክንፍሽ አቅፎኝ
ዕንቁሽን ስመኘው፥ ጣጣሽ ብቻ ተርፎኝ
መኖርን ስፈራ፥ መሞትም ስፈራ
ካየር ንብረት በቀር፥ ንብረት ሳላፈራ
ወሩ ተጠራቅሞ፥ አንድ ደርዘን ሞልቶ
እንደባለጌ ልጅ፥ በሩን በግሩ ከፍቶ
አዲስ ዘመን ገባ፤


አዲስ አመት ገባ
ያለ መስቀል ወፎች፥ ያለ ዓደይ አበባ
በግዜርሠራሽ ማማ
ቁራ ብቻ ሰፍሯል
የመስቀል ወፍማ
ወይ አገር ለውጧል
ወይ ልብሱን ቀይሯል፤


አዲስ አመት ገባ
በቄጤማ ምትክ፥ ብሎኬት ጎዝጉዞ
በቅፍ ዓደይ ምትክ፥ ጉንጉን ሽቦ ይዞ
በሉባንጃ ምትክ፥ አቧራ እያጤሰ
በፈንድሻ ምትክ፥ ጠጠር እያፈሰ፤


አዲስ አመት ገባ
እንዲህ እንደዋዛ
ተፈጥሮ በውበት፥ መንፈሴን ሳይገዛ
በመአዛው ሳይዋጅ
መስከረም መግባቱን በሬድዮ ልስማው?
እንደ መንግሥት አዋጅ።
............
እንቁጣጣሽ
............
581 views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 20:33:46 አንዳንድ ገፅ
"""""""'''''''''''''''""

የኔነቴ ምዕራፍ
ልክ እንደ መፅሀፍ
ጠፍተው የተረፉ ሰባት ገፆች አሉት፤
የኔና አንቺን ህይወት በግልፁ የሚያትት።

ማውጫ የለው መግቢያ
ጥራዝ የለው ሽፋን
ወና ....ቤት አልባ ገፅ፤
እንዲህ ይነበባል
በባለ ታሪኩ ታሪኩ ሲገለ'ፅ።

(ገፅ አንድ)

በሰፈሬ መንገድ ቁልቁለቱን ስወርድ፤
አንቺ ደሞ ወደላይ ስትወጪ አቀበት፤
እንቅፋት ሳይነካኝ ልቤ አለ ሸርተት፤
አልገባኝም ነበር?
ከየት አመጣጡ? ደርሶ ይሄ ስሜት።

አቀበት ሆኖብሽ
ደካክሞሻል አንቺ ያለሽበት መንገድ፤
ድካም ነው ቁንጅናሽ?
አልገባኝም ከቶ ደርሶ የልቤ መራድ።

መንገዱ ሲወስደኝ የልቤ መረበሽ፤
መንገዱ ሲይለፋሽ እንዲያ ተደካክመሽ፤
ድጋሚ አልገባኝም?
ጎን ለጎን ስንደርስ
ለምን ተሽኮረመምሽ? ለምን ስቀሽ አለፍሽ?

(ገፅ ሁለት)

እኔ እንቅልፋሙ
የሞትኩ የምመስለው ጎኔ ሲነካ አልጋ፤
አልገባኝም ዛሬም?
አልጋው ኮሰኮሰኝ ስገላበጥ ነጋ።

ውሎዬ አላማረ
እንዲሁ ስነጫነጭ ባህሪዬ ከፍቶ፤
"ምን ሆነሀል?" ሲለኝ
መጤ ባህሪዬን ሰዉ ተመልክቶ።
አላውቅም ምንድነው?
ልገልፀው አልቻልኩም ያናደደኝ ነገር፤
ቆይቼ ሲገባኝ
ገፅ አንድ ላይ ያለው አሳሳቅሽ ነበር!

(ገፅ ሶስት)

ድንገት ያየሁሽ ቀን
በደስታ ባህር ውስጥ ልቤ ሲረግጥ ጮቤ፤
ያላየሁሽ ለታ
ተከፍቼ ስገኝ ሀዘኔን ደርቤ፤
ለተመልካች ሁሉ
እኔ አንቺን መውደዴ አሳበቀ ቀልቤ፤
ልቀርብሽ ፈለኩኝ
የወንድነት ወኔ ድፍረቴን ሰብስቤ።

(ገፅ አራት)

ሰላም ተባባልን
ትንሽ ተንተባተብኩ አንቺም ተዋወቅሽኝ፤
ፍርሃቴም ቀነሰ
ተለማመድንና ቀርቤሽ ቀርበሽኝ፤
ግን ሌላ ምጥ ያዘኝ
እንደ ጓደኛ እንጂ በፍቅር አላየሽኝ፤
ድጋሚ አማጥኩኝ
ትንሽ ጉድጓድ ስዘል ትልቅ ገደል ሆንሽኝ።

(ገፅ አምስት)

ምንም አይገባሽም
ላሳይሽ ብሞክር ፍቅሬን በተግባር፤
የፍቅር አኩኩሉ
እየተጫወትኩኝ  ተደብቄ ነበር፤
ደንታም አልነበረሽ
በስስት ማየቴ ለማሳይሽ ነገር፤
ግን ስፈራ ስቸር
ልነግርሽ ወሰንኩኝ በቃል የኔን ፍቅር።

(ገፅ ስድስት)

የነገርኩሽ ለታ
እንደ መሳቅ እያልሽ
"እንዴት ነው ያየከኝ?" የሚል ወጣ ካፍሽ
"ስሜት የለኝ ላንተ"
በምትለዋ ቃል በሰቀቀን ጥለሽ መንፈሴን አደማሽ
ታዲያ ገፅ አንድ ላይ
ምን አሽኮረመመሽ?...ለምን ስቀሽ አለፍሽ?

(ገፅ ሰባት)

ገብቶሻል ስሜቴ
አትምሰይ እባክሽ ይሄ የማይገባሽ፤
ጨንቆኝ የቀረብኩሽ
እህት ፈልጌ አይደል
ያልገባው አትምሰይ ገብቶሻል እባክሽ።

አሁን በይምሰልሽ አውቀሽ ልትመልሽኝ፤
ሳቅሽ ቀመር ነበር
ዳገቱም ነው ቀመር
አካሄድሽ ቀመር አውቀሽ ነው የታየሽኝ።

(ገፅ ስምንት)

ገፅ ስምንት ላይ
"አውቀሽ ነው የታየሽኝ..." በከፊሉ ይላል.....

የወረቀቱ ገፅ በግማሽ ተቀዷል
               .
               .
               .
               .
ውድቆ ቀርቷል እንጂ ታሪኩ ይቀጥላል

አብራሀም

https://t.me/nuenanbib
930 views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ