Get Mystery Box with random crypto!

ኑ እናንብብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የሰርጥ አድራሻ: @nuenanbib
ምድቦች: ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.11K
የሰርጥ መግለጫ

ማንበብ የስብዕና ልህቀትን ያጎናፅፋል!!
ማንበብ ምክንያታዊ እና የሰላ አእምሮን ያንፃል!!
በዚህ ቻናል
👉የስነ ልቦና ምክሮች
👉ግጥሞችና ወጎች
👉ሳይንስና ፍልስፍና
በብዛት ይቀርባሉ።
ወዳጆዎን የዚህ የንባብ ማዕድ ተካፋይ እንዲሆኑ በመጋበዝ ቻናሉን ይደግፋ።
ማንኛውም አስተያየት @NuEnanbib_bot ላይ ይላኩልን

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-21 06:53:40 የትንፋሽ ሜዲቴሽን

ሁለት አይነት የሙሉ እዕምሮ አተነፋፈስ ሜዲቴሽን አለ።አንዱ በቀን ውስጥ የተወሰነ ጊዜ መድበን ሲሆን ፤ሌላ ስራችንን ሁሉ አቁመን የምናደርገው ሲሆን ፤ተቀምጠን ወይም አልጋ ላይ ጋለል ብለን ወይም ራስችንን እንደተመቸን አስቀምጠን ሙሉ በሙሉ ትኩረታችን ትንፋሻችን መግባትና መውጣት ላይ ይሆናል ማለት ነው ።

ይሄን በየጊዜው አዘውትርን ያለማቁዋረጥ የምናድረግ ከሆነ በዚህ በራስችን ላይ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንችላለን ማለት ነው።ይህ እንግዲህ አዕምሮችን ከውስጥ ራሱ ከሚፈጥረው ችግርም ሆን ከውጭው አለም ከሚደርስብን ግፊት ራሳችንን መከላከል እንችላለን ማለት ነው ።

አዕምሮአችን ራሱ ከሚፍጥረው መጥፎ ሃስብም ሆነ በኑሮ ከሚመጣብን እንቅፋት ይልቅ ትኩረታችን ወደ ትንፋሽችን ሲሆን አዕምሮአችን የበለጠ ጤናምና ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ ችግሮችን የመቋቋም ችሎታው ይዳብራል።

ሁለተኛው ደግሞ በቀን ውስጥ በየትኛውም ጊዜ ወይም ቀኑን ሙሉ በምናደርገው እንቅስቃሴ ትኩረታችንን ወደ ትንፋሻችንም ሆነ ወደ ሰውነታችን እንቅስቃሴ በማድረግ ነው ።

ለምሳሌ ስንራመድ ስንቀመጥም ሆነ በተገኘው ሁሉ አጋጣሚ ትኩረታችንን ትንፋሻችን ላይ ማድረግ ስንጀምር እርጋታን፤ነገሮችን በጥንቃቄና በሰከነ መንፈስ ማየት እንጀምራለን።

የትንፋሽ ሜዲቴሽን መለማመጃ

1.ተመቻችተህ በጀርባህ መንጋለል ወይም በደንብ ተስተካከለህ
ትቀመጣለህ ትከሻህን ዘና ታደርገዋለህ

2 .አይንህን ትጨፍናለህ ይህም ተስማሚ ሆኖ ካገኘህው ነው።

3 ትኩረትህን ሁሉ ወደ ሆድህ አምጣው፤ወደ ውስጥ ስትተነፍስ የሆድህን ወደ ላይ መውጣት ወይም ወደ ጎን ሰፋ ማለት እንዲሁም
ወደ ውጭ ስትተነፍስ የሆድህን ወደ ታች ማለት አስተውለው።

4 .ትኩረትህን ወደ ትንፋሽህ ጨምር፤ ወደ ውስጥም ሆነ ወደ ውጭ የምትተንፍስበትን ጊዚያት ሁሉ ከሱ ጋር አብረህ ሁን።በሃሳብ አንተ የትንፋሽህን ሞገድ የምትነዳው አድርገህ ገምትና አብረህ ወደታች ወደላይ በል።

5. አዕምሮህ ትንፋሽህን ዘንግቶ ወደ ለመደው ስራው መሄዱን ስትገነዘብ በእርጋታ መልስህ ወደ ትንፋሽህ አምጣው።እንደገና ወደ ውስጥና ውጭ ትንፋሽህ ትኩረትህ ይሁን።


6 .አንድ ሺህ ጊዜ አዕምሮህ ትንፋሽህን እየዘነጋ ወደ ሌላ ሃሳብ ሲዘል ያንተ ስራ በእርጋታ ወደ ትንፋሽህ እንዲመለስ ማድረግ ነው።

7. ይህን ሜዲቴሽን በቀን ለ 15 ደቂቃ ምንም ሳትደርግ ትንፋሽህ ላይ ብቻ በማተኮር ብተለማመድ ለውጡን በሳምንታት ጊዜ ታየዋለህ።

ይቀጥላል ..
@Zephilosophy
@Zephilosophy
3.4K views03:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 13:28:24 ለዚህች ሀገር እዘኑላት
የንባብ ቅምሻ

ደራሲ -ካህሊል ጂብራ
መፅሀፍ -የጠቢባን መንገድ

በአንዱ ቀን ጠዋት ደቀ - መዛሙርቱ ነብዩን ከበው ተቀመጡ፡፡ በአይኖቹ ላይ ርቀቶችና ትዝታዎች ነበሩበት። ሀፊዝ የሚባለው ደቀ - መዝሙሩም እንዲህ አለው፦ «መምህር ሆይ! ስለ ኦርፋሴስ ከተማ ንገረን፡፡ በእነዚያ አስራ ሁለት አመታት ስላረፍክበት ሀገርም ንገረን፡፡»

አልሙስጠፋ ዝም አለ። ወደ ጋራዎቹና ወደ አድማሱም ፊቱን አዙሮ ተመለከተ። በፀጥታው ውስጥ ጦርነት ነበር!!
ከዚያም አላቸው
"ወዳጆቼ ሆይ በእምነቶችና በባዶ ሀይማኖቶች ለተሞላች ሀገር እዘኑላት...

"በጥባጮችን እንደ ጀግና በእልልታ ለምትቀበል ገዳዮችን እንደ ለጋስ ለምታሞካሽ ሀገር እዘኑላት...

"ያልሸመነውን ጨርቅ ለሚለብስ፤ያልጋገረውን ዳቦ ለሚመገብና ያልጠመቀውን ወይን ለሚጠጣ ሰው እዘኑለት።


"ፍቅርን በህልሟ ለምትንቅ ሰትነቃ ግን ለምንትበረከክለት ሀገር እዘኑላት...

"ወደ መቃብር ሲወርድ ካልሆነ በስተቀር ድምፁ ለማይሰማ፤ እንዲሁም አንገቱ በሰይፍ እና በግንዲላ መካከል ሲጋደም ካልሆነ በስተቀር ለማያምፅ ህዝብ እዘኑለት...

"መሪው ቀበሮ ፣ፈላሰፋው ቀጣፊ ፣ጥበቡም መኮረጅና መለጣጠፍ ለሆነ ህዝብ እዘኑለት...

"አዲስ ገዢዎቹን ጥሩምባ እየነፋ ለሚቀበልና እንደገና ጡሩምባ እየነፋ ሌላውን ለመቀበል ሲል ብቻ በንቀት ጩኸት ለሚያሰናብታቸው ህዝብ እዘኑለት....

"አዋቂዎቹዋ እድሜ በመግፋት ዲዳ ለሆኑባትና ልጆቹዋ ገና ከህፃን አልጋ ላይ ላልተነሱላት ሀገር እዘኑላት...

"ግዛቷ ለተበጣጠሰና እያንዳንዱ ብጥስጣሽ ራሱን እንደ አንድ ሀገር ለሚቆጥርባት ሀገር እዘኑላት...

@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.9K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 22:08:31 ሕይወት ምንድን ነው?

ምንጭ ፦ ዘላለማዊነት (ራምፓ)
ትርጉም ፦ ሱራፌል ግርማ

በእውነቱ፣ ያለው ነገር በሙሉ “ሕይወት” ነው፡፡ “ምውት” ብለን የምንጠራው ፍጡር እንኳ ሕያው ነው፡፡ “ምውት” ብለን እንድንጠራው ያደረገን ተለምዷዊ የሕይወት ቅርፁ ማብቃቱ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ያ “ሕይወት” ሲያበቃ አዲስ ዓይነት ሕይወት ይፈጠራል፡፡ የመፍረስ ኺደት በራሱ ሕይወት ይፈጥራል!

ያለ ነገር በሙሉ ይነዝራል፡፡ ሞለኪውሎችን የያዘ ነገር በሙሉ በማያቋርጥ እንቅስቃሴ ላይ ነው። በአቶም፣ በኒዩትሮን፣ በፕሮቶን ፋንታ “ሞለኪውል” የምንጠቀመው ይሄ ትምህርት የኬሚስትሪ አሊያም የፊዚክስ ሳይሆን የዲበ-አካል በመሆኑ ነው፡፡ በማይጠቅሙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ፋንታ አጠቃላይ ምስሉን ለመፍጠር ነው የምንሞክረው፡፡

ምናልባት በመጀመሪያ ስለ ሞለኪውሎችና አተሞች ጥቂት ማለት ሳይኖርብን አይቀርም፡፡ ሞለኪውሎች በኤሌክትሮን ማይክሮስኮፕ ብቻ ሊታዩ የሚችሉ ቅንጣቶች ናቸው። በመዝገበ ቃላት ፍቺው መሠረት ሞለኪውል፣ የአንድ ነገርን ባሕሪያት ይዞ ለብቻው ሕላዌ ሊኖረው የሚችል ቅንጣት ነው። ሞለኪውሎች በጣም ደቃቅ ቢሆኑም ከእነርሱ ባነሱ “አቶም” በሚባሉ ቅንጣቶት የተዋቀሩ ናቸው፡፡

አቶም በሥርዓተ ፀሐይ ሊመሰል ይችላል፡፡ የአቶሙ አስኳል ፀሐይን ይወክላል። በዚህ “ዐሐይ” ዙሪያ ፕላኔቶች ፀሐይን እንደሚዞሯት ኤሌክትሮኖች ይዞራሉ፡፡ እንደ ሥርዓተ-ፀሐይ ሁሉ የአቶም አብዛኛው ክፍል ባዶ ሥፍራ ነው፡፡

እያንዳንዱ ነገር በኒውክለሱ ውስጥ የሚኖረው የኤሌክትሮኖች ቁጥር የተለያየ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ ዩራኒያም ዘጠና ሁለት ኤሌክትሮኖች አሉት። ካርቦን ደግሞ ስድስት ብቻ ነው ያለው፡፡ ለኒውክለሱ የሚቀርቡት የካርበን ኤሌክትሮኖች ሁለት ሲሆኑ አራቱ ደግሞ በርቀት የሚዞሩ ናቸው። ነገር ግን ዋና ጉዳያችን ሞለኪውሎች በመሆናቸው ስለአቶሞች በሰፊው አንነጋገርም።

ሰው በፍጥነት የሚሽከረከሩ ሞለኪውሎች ስብስብ ነው፡፡ ሰው ጠጣር ይመስላል፤ ሥጋችንንና አጥንታችንን በጣታችን መሠርሠር አንችልም፡፡ ሆኖም ግን ይሄ ጠጣርነት የሰው ፍጡር በመሆናችን ለማመን የተገደድንበት ምትሀት ነው፡፡ በጣም ደቃቅ የሆነ ፍጡርን፣ ከሰው አካል በርቀት ሆኖ ሊመለከተው የሚችልን አስቡ ያ ፍጡር የሚያጥበረብሩ ፀሐያትን፣ በጣም ርቀው ያሉ ከዋክብትን ይመለከታል፡፡ በጣም ለስላሳ በሆኑ የሰውነት አካላት ላይ የሚገኙ ሞለኪውሎች የተበታተኑ ናቸው። እንደ አጥንት ባሉ ጠንካራ የሰውነት አካላት ላይ የሚገኙ ሞለኪውሎች ደግሞ በጣም ጥቅጥቅ ያሉ፤ እርስ በርሳቸው በጥብቅ የተሳሰሩ በመሆናቸው የከዋክብት ስብስብን ይመስላሉ፡፡

ጨረቃና ከዋክብት ብሩህ ባደረጉት ምሽት ከተራራ ጫፍ ላይ ቆማችሁ በምናባችሁ ይታያችሁ፡፡ ብቻህን አይደለህም ፤ ወደ ሰማይ ከሚፈነጠቁት የከተማ የኤሌክትሪክ ብርሃናት ባሻገር ካረበበው እርጥበት የተነሣ ሰማየ - ሰማያት ደብዝዘው ይታያሉ፡፡ (ለዚህ ነው የሕዋ ምርምር ጣቢያዎች ከከተማ ርቀው በሚገኙ ሥፍራዎች የሚገነቡት) አንተ በራስህ ተራራ ጫፍ ላይ ነህ። ከአንተ በላይ ክዋክብቱ ብሩህ ብርሃን ይፈነጥቃሉ፡፡ ማለቂያ በሌለው ሰልፍ ከፊትህ ሲሽከረከሩ እነርሱን አተኩረህ ትመለከታለህ፡፡ ታላላቅ የከዋክብት ስብስቦች ከፊትህ ተዘርግተዋል። ከዋክብቱ የምሽቱን ጨለማ አስጊጠውታል፡፡ ከሰማየ ሰማያት ባሻገር “ሚልኪ ዌይ” የተባለው የከዋክብት ስብስብ ሰፊና በጭጋግ የተሸፈነ ዱካ መስሎ ይታያል፡፡ ከዋክብት፣ ዓለማት፣ ፕላኔቶች፣ ሞለኪውሎች:: ልክ እንደዚሁ ነው “ማይክሮስኮፒክ” የሆነው ደቃቅ ፍጡር አንተንም የሚመለከትህ!

በሰማየ - ሰማያት የሚገኙት ከዋክብት በመካከላቸው የማይታመን ክፍተት ያለ የብርሃን ነጥቦች ሆነው ነው የሚታዩት፡፡ በቢሊየን፣ በትሪሊየን የሚቆጠሩ ከዋክብት ቢኖሩም በመካከላቸው ካለው ክፍተት የተነሣ ጥቂት መስለው ነው የሚታዩት፡፡ የጠፈር መረብ ቢኖር በከዋክብቱ መካከል አንዱንም ባለመንካት ለማለፍ ይችላል፡፡ በከዋክብቱ፤ በሞለኪውሎች መካከል ያለውን ክፍተት ለማጥበብ እንደምትችል በምናብህ ስታስብ ምን ልታይ ትችላለህ? ከርቀት አንተን እየተመለከተህ ያለው ደቃቅ ፍጡርም ይሄን እያሰበ ይሆን ያ ፍጡር የሚያየው ሞለኪውሎች በሙሉ “እኛ” መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን፡፡

እንግዲያውስ በሰማየ-ሰማያት የሚገኙ ከዋክብት የመጨረሻ ቅርፅ ምን ዓይነት ነው? እያንዳንዱ ሰው በራሱ ፍጥረተ ዓለም ነው፡፡ በዚህ ፍጥረተ-ዓለም ውስጥ ሞለኪውሎች በማዕላዊ ፀሐይ ዙሪያ ይሽከረከራሉ፡፡ እያንዳንዱ ዐለት፣ ቀምበጥ ወይም የውኃ ጠብታ ማለቂያ በሌለው ሞለኪውሎች የተዋቀረ ነው፡፡

ሰው፣ በእንቅስቃሴ ላይ ከሚገኙ ሞለኪውሎች የተሠራ ነው፡፡ እንቅስቃሴው የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን፣ በላየ ራስ ከሚያመነጨው “ኤሌክትሪክ” ጋር ሲዋኃድ ስሜት ያለው ሕይወት ይሰጣል። በምድር ዋልታዎች ዙሪያ ያለው መግነጢሳዊ ሞገድ ለባለ ሕብረ-ቀለማቱ አውሮራ ቦሪያሊስ መንስኤ ነው፡፡ በሁሉም ፕላኔቶችና ሞለኪውሎች ዙሪያ መግነጢሳዊ ሞገዶች በቅርብ ከሚገኙ ዓለማትና ሞለኪውሎች ከሚመነጩ መግነጢሳዊ ሞገዶች ጋር መስተጋብር ይፈጥራሉ፡፡ “አንድም ሰው ለራሱ፧ ለብቻው ዓለም አይደለም!” ያለ ሌሎች ዓለማት ወይም ሞለኪውሎች አንድም ዓለም ወይም ሞለኪውል ሕላዌ ሊኖረው አይችልም፡፡ እያንዳንዱ ፍጡር፣ ዓለም ወይም ሞለኪውል በሌሎች ፍጡራን ዓለማት ወይም ሞለኪውሎች መኖር ነው
ሕላዌው የሚወሰነው።

የሞለኪውል ስብስቦች እንደ ከዋክብት ስብስቦች በሕዋ ላይ የሚዋልሉ የተለያየ የጥግግት ደረጃ ያላቸው መሆኑ ሊታወቅ፤ ሊደነቅ ይገባል፡፡ በፍጥረተ ዓለም የተወሰነው ክፍል በጣም ጥቂት ከዋክብት ወይም ፕላኔቶች ሲኖሩ እንደ ሚልኪዌይ ባለው ጋላክሲ ውስጥ ደግሞ ፕላኔቶች ተጠጋግተው ይገኛሉ፡፡

በተመሳሳይ መልከ ዐለት በጣም ጥብቅ የሆነ የሞለኪውሎች ስብስብን ወይም ጋላክሲን ሊወክል ይችላል፡፡ የአየር የሞለኪውሎች ይዘት የሳሳ ነው፡፡ በርግጥም አየር በውስጣችን፣ በሳንባችን በማለፍ ወደ ደም ሥሮቻችን ያመራል። ከአየር ባሻገር፣ የሐይድሮጅን ሞለኪውሎች ተበታትነው የሚገኙበት ሥራ አለ፡፡ ወና፣ ሰዎች እንደሚያስቡት ባዶ፥ ምንም የሌለበት ሳይሆን የሐይድሮጅን ሞለኪውሎች . . . ከሐይድሮጅን ሞለኪውሎች የተፈጠሩ ዓለማት፣ ከዋክብትና ፕላኔቶች የተሰባሰቡበት ነው፡፡

አንድ ነገር ጥብቅ ከሆኑ የሞለኪውል ስብስቦች የተዋቀረ ከሆነ ሌላ አካል በእርሱ ውስጥ ለማለፍ እንደማይችል ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን ከተበታተኑ
ሞለኪውሎች የተዋቀረውና “መንፈስ” ተብሎ የሚጠራው በግድግዳ ውስጥ እንኳ ሲሆን አልፎ ለመሄድ ይችላል፡፡ የደንጊያ ግድግዳን አስበው፧ በአየር ላይ እንደተንጠለጠለ የአቧራ ደመና ያሉ ሞለኪውሎች ጥብቅ ስብስብ ነው፡፡ የቱንም ያህል የማይቻል ቢመስልም በእያንዳንዱ ሞለኪውል መካከል ክፍተት አለ (ልክ በከዋክብት መካከል እንዳለው) ስለሆነም፣ ከዚያ አካል ሞለኪውሎች ይበልጥ በተበታተነ ሞለኪውሎች የተዋቀረ ደቃቅ ፍጥረት በጥብቅ ሞለኪውሎች በተዋቀረው የደንጊያ ግድግዳ ውስጥ እንኳ ምንም ሳይነካካ ለማለፍ ይችላል፡፡

ይህም፣ “መንፈስ” በተዘጋ ክፍል ውስጥ እንዴት ሊከሰት እንደሚችል እና በግድግዳ ውስጥ ሊያልፍ እንደሚችል እንድናውቅ ይረዳናል፡፡ እያንዳንዱ ነገር አንፃራዊ ነው ፤ ለአንተ ጥብቅና ጠጣር መስሎ የሚታይህ ግድግዳ ለመንፈስ ወይም ለከዋክብቱ ፍጥረት ክፍል ሊሆን ይችላል፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
4.0K views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 21:51:49 ሰው
( አጭር ልቦለድ)
(በእውቀቱ ስዩም)
ጢም ማቀምቀም በጀመርኩበት ዘመን በከተማችን አንድ ተአምረኛ ባህታዊ ብቅ አለ፤ 'ጥቁር ኢየሱስ ብለው ሊጠሩት የደፈሩ ሰዎች ሁሉ ነበሩ ፤ ባህታዊው እውር ያበራል፤ ጎባጣ ያቀናል፤ ባንድ ጊዜ የከተማው ሆስፒታሎች ሁሉ ባዶ ሆኑ፤ የሆነ ጊዜ ላይ እንዲያውም ሙት ማስነሳት ሁሉ ጀምሮ ነበር፤ የከተማችን አስተዳዳሪ ግን “ ለተነሺዎች ማቋቋሚያ የሚሆን በጀት የለንም ብሎ ከለከለው፤

ባህታዊው ባንድ ወቅት ከተማውን አቋርጦ ሲያልፍ ወልደ ሰንበት ከተባለ የከተማው ነዋሪ ጋራ ተገናኘ፤ ወልደ ሰንበት በራዛ ዘመቻ ጊዜ ፈንጅ ብልቱን ቆርጦበታል፤ በጥሮታ ከተገለለ በሁዋላ ‘መራባት የተሳናቸው ወንዶች ማህበር’ ፕሬዚዳንት ሆኖ ያገልግላል፤

ወልደሰንበት ባህታዊውን ሲያየው “ አባት ሆይ፥ አገሬን አገሬን ብየ ስዋትት ዘሬን ሳልተካ ላልፍ ነው፤ ፈውሰኝ “ ሲል እግሩ ላይ ወድቆ ተማጠነው።

ባህታዊው ወደ ሰማይ አንጋጦ ትንሽ ከጸልዩ ሲያበቃ ወልሰንበትን አስወልቆ ጉያውን ዳበስ አደረገው ፥ መቸም አታምኑኝም ፤ ግን ሀቅ ከከመመስከር አልታገድም፤ የሰውየው ጉምድ ብልት ወዲያውኑ አቆጠቆጠ። ተአምረኛውን ሰውየ ያጀቡ ወንዶች አፋቸውን በጋቢያቸውና በኮሌታቸው ጫኑ !የሴቶች እልልታማ ፤እስከመተማ ፤ ተሰማ፥

ባህታዊው ይህንን ተአምራዊ የብልት- ተከላ ፈጽሞ ትንሽ አለፍ እንዳለ ወልደ ሰንበት እያለከለከ ደረሰበትና እግሩ ስር ተደፋ፤

“ አሁን ደግሞ ምን ፈለግህ?” አለው ባህታዊ፥ በታከተ ሰው ድምጽ ፥
ወልዴ እንዲህ ሲል መለሰ፥

“አባት ሆይ ! በነካ እጅህ ትንሽ ተለቅ ልታረግልኝ ትችላለህ?”
5.2K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 23:39:03
ለፍልስፍና አፍቃሪዎች በሙሉ እነሆ ምርጥ ቻናል ተከፍቶላችዋል

@Zephilosophy
ፍልስፍና ለነፃ አስተሳሰብ
https://t.me/joinchat/RVzIu0-BTYG_XaN8

በዚህ ቻናል ከተለያዪ የአለም ዳርቻዎች የተነሱ የታላላቅ ፈላስፋዎች አስተሳሰቦች እና ፍልስፍናዎች ይቀርባሉ።ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ፤ ከሰሜን እሰከ ደቡብ የአለምን የአስተሳሰብ ኮምፓስ የቀየሩ ፈላስፋዎች እና ሃሳቦቻቸው ከየመፅሀፉ እየተጨለፉ ለናንተ ይቀርባሉ። ከሶቅራጥስ እስከ ኒቼ ፤ ከቡድሃ እስከ ኦሾ ፤ ከማርክስ እስከ ሌኒን አለም ላይ የማይፋቅ አሻራዎቻቸውን ያሳረፋ ሰዎች ፤ ከክርስትና እስከ ቡዲሂዝም ፣ከእስልምና እስከ ሂንዲይዝም ፣ከሶሻሊስት እስከ ካፒታሊስት በዘመናት ውስጥ የተፈጠሩ ሀይማኖቶች ፣ስርዓቶች ርዕዮተ ዓለሞች ሁሉ ይዳሰሳሉ። ለዓለም ያስገኙት ሞራላዊና መንፈሳዊ ትሩፋቶች ይወዳሳሉ። ታሪካዊ ህፀፆቻው ደግሞ ያለምህረት ይተቻሉ ፣ይወቀሳሉ።

ፍልስፍናን ከተደበቀችበት ጓዳ አውጥተን በአደባባይ እናሰጣታለን። ማህበረሰቡ የሚሳሳላቸው ባህሎቹ እና እምነቶቹ በነፃነት ይጠየቃሉ ፣ይመረመራሉ ይፈተናሉ። እንደ ጣት ቁስል የተፈሩ እውነቶች መሀረባቸው ይገለጣል። እንደ ማህበረሰብ በጉያችን የጋረድናቸው እባጮች የግንባር ስጋ ይሆናሉ።ከግለሰብ እስከ ቡድን ፤ከሀይማኖት እስከ ርዕዮተ -ዓለም
፤ ከኋለቀር ባህሎች እስከ ዘመናዊ ስልጣኔዎች ያለምንም ፍርሃት በግላጭ ይሞገታሉ፣ ይመረመራሉ፣ይጠየቃሉ ውስጣቸው የተደበቀው እውነት እስኪገለጥ ድረስ በአውድማው ላይ መንሽ እየተፈለገ ፍሬው ከገለባ ይለያል።
መንሻችን የሰላ አምክንዮዊ አእምሮ፣ የሰከነ የሞራል ልዕልና እና ንፁህ ሰዋዊ ህሊና ናቸው።

Join

@Zephilosophy
@Zephilosophy
4.4K views20:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 21:05:53 ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ሜሪ ፈለቀ)
«ሞቼ ቢሆን ኖሮ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?» አለኝ በወጉ ማሽከርከር ያልለመደውን ዊልቸር እየገፋ ወደሳሎን ብቅ እንዳለ። ፊቱ ምሬት ወይ ጥላቻ በቅጡ ያልለየሁት ስሜት ይተራመስበታል። ዝም ያልኩት መመላለሱ ልቤን ስለሚያደክመኝ ነበር። በጎማው እየተንቀራፈፈ አጠገቤ ደርሶ « ንገሪኛ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?»
«አይከፋኝም ነበር።» መለስኩለት። እግዚአብሔር ይሁን ሰይጣን አደጋውን ያደረሱበት አንዳቸው ምርጫ ሰጥተውኝ ቢሆን ኖሮ እንኳን የቱን እንደምመርጥ እንጃ! (ሰዎች በህይወታቸው የሆነ የከፋ ነገር ሲገጥማቸው <እግዜር ሊያስተምረው ነው!> ይሉን የለ? ያው ራሳቸው ሰዎች ደግሞ የክፉ ነገር ምንጭ ሰይጣን ነውም ይሉናል። ነገሩ ለእኔ ጭንቅላት የተሳከረ ነገር ስላለው ነው ከሁለቱ አንዳቸው ቢሆኑ ያልኩት!! አስቡት የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ፣ ለሰው ልጅ በምርጫው እንዲኖር ነፃነትን የሰጠው የነፃነት አምላክ ሊያስተምር ሲፈልግ በክፉ ሲቀጣ? አንዳንዴ ፈጣሪ በክፉ አይፈትንም ብዬ ሳስብ ለራሴ የምሰጠው ማመሳከሪያ የመፅሃፍ ቅዱሱ እዮብ ነው። ፈጣሪ ጥበቃውን እንደእዮብ ያነሳብህና ለክፉ አባት አሳልፎ ይሰጥሃል እንጂ ራሱ አምላክ ክፉውን አያዘንብም! ከዛ ግን ሞትና የሲኦል መኖር ይሄን እሳቤዬን ከአፈር ያደባይብኛል። ብቻ ማናቸውም ይሁኑ የዛን ቀን እየነዳ የነበረውን ጣዖቱ የነበረ መኪና ከገደል ፈጥፍጠውልኛል። እግዜር ይስጣቸው!!_)
«እግዜሩ እንድትበቀዪኝ እድሉን እየሰጠሽ ይሆናልኮ! ለምን ደግ እየሆንሽ የተሰጠሽን እድል ታባክኛለሽ?» አለ የሰራሁለትን ምግብ ላጎርሰው እጄን ስዘረጋ! ከፍቅሬ ጥልቀት አይደለም የማጎርሰው። በአደጋው ምክንያት እጁ እንደፈለገው ስለማይታዘዝለት እንጂ።
«ከዛስ? በእኔ ክፉት ክፉትህን ልታቀል? በእኔ ሀጢያት በደልህን ልትሰርዝ? በእኔ በቀል ሀጢያትህን ልታወራርድ? በፍፁም ያን ደስታማ አልሰጥህም!!»
በቀል ዓይን ላጠፋ ዓይን ማጥፋት ፣ የገደለን መግደል …………… ባጠቃላይ በቀል ለክፋት ክፋትን መመለስ ነው ያለ ማን ነው? ለሰራው ስራ የስራውን መኸርማ መሰብሰብ የተፈጥሮ ህግም አይደል? ያጭዳል!! ምኗ እንከፍ ብሆን ነው <ወይ በገደልከኝ ወይ በገደልከው> ብዬ ስማፀን የከረምኩበትን ሰው እንዳይሞት እንዳይድን አድርጎ እጄ ላይ ሲያስቀምጠው በክፋት የምበቀለው?
ገብቶታል። ጤነኛ ሆኖ ሰራተኛ ያበሰለውን ምግብ የምንበላ ሰዎች ራሴ የሚበላውን ጓዳ ገብቼ ሳበስልለት በደሉን እንደማላቀልለት ገብቶታል። እልህ የሚይዘው ከእኔ ይሁን ከራሱ እንጃ ርሃብ አንጀቱን ካልፋቀው በቀር እሺ ብሎ አይበላም። አይጠይቅምም!! ከሆስፒታል እቤት የገባ ሰሞን <ነርስ ይቀጠርልኝ> ሲል <እኔ ሚስትህ እያለሁ እንዴት ገበናህን ባዳ ያያል?> ብዬው አልጋው ላይ ሲፀዳዳ እሱንም አልጋውንም ሳፀዳ በቀላሉ ይቅር እንደማልለው ገብቶታል። ከሀዘኔታ ልብ ወይም ከፍቅር ፅዋ ከፈለቀ ደግነት እንደማልንከባከበው ያውቃል። ግን ደግሞ በደሉን በበደሌ አላለቀልቅለትም። እሱም ያ ገብቶታል።
ሞቶ ቢሆንና እንደወጉ ነጠላዬን አዘቅዝቄ ከሬሳው ጋር ወደ ቀብር እየሄድኩ ምንድን ነበር የምለው? ሰው ምን ይለኛል ብዬ ደረቴን እደቃ ነበር? ወይስ <ተመስገን ገላገልከኝ> እያልኩ በፈገግታ ከአፈሩ ጋር የሰባት ዓመት ትዳራችንን ወደ ጉድጓዱ መልሼ እመለስ ነበር? የቱ የበለጠ ደስ ይላል? ሞቱ? ወይስ ስንክልክሉ የወጣ አካላቱን እና ከተሰበሩት አጥንቶቹ እኩል እንክትክት ያለ ትህምክቱን፣ ትእቢቱን፣ ሞራሉን ፣ አምላክ ነኝ ባይ ልቡን ………. ታቅፎ ……….. እንኳን እኔ ላይ ራሱ ላይ እንኳን የማዘዝ አቅም የሌለው ከንቱ ሆኖ ማየቱ? የቱ የበለጠ ደስ ይላል? ወይስ ከነጭራሹ ደስታ አለው? ካለመዋሸት አለው! የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው። አንዳንዴ በ7 ዓመት የዲያቢሎስ ሚስትነት ዘመኔ በደነደነ ክፉ ልቤ ውስጥ የተረፈው ሚጢጥዬ የርህራሄ ጭላንጭል ተስፋ ብቅ ይልና ደስታዬን ይበርዝብኛል።
ደስታዬን መደበቅ ግን አልችልም። በጠዋት ተነስቼ እንዲፀዳዳ እያገዝኩት ፈገግታዬ ያመልጠኛል። ጥርሱን እየቦረሽኩለት፣ ፀጉሩን እያበጠርኩለት፣ ልብሱን እየቀየርኩለት፣ የሚንቀጠቀጡ እጆቹ አስተካክለው ስልኩን መያዝ ስለማይችሉ ስልኩ ሲጠራ ሲንፈራገጥ ሳየው አንስቼ እያቀበልኩት ሁላ ከንፈሬን እንደተከደነ ማስቀረት ያቅተኛል። የሚወደውን ምግብ በዜማ እያፏጨሁ አበስልለታለሁ፤ሲዝረከረክ በሶፍት እያፀዳሁ አጎርሰዋለሁ፤ በጤነኛ ዘመኑ ሰራተኛዋ የማታጓድለውን የምሳ ሰዓት ቡና ከነጭሱ እሱ እንደሚወደው ራሴ አፈላለታለሁ፤ ፈገግታዬ በየቀኑ ከማፈነዳው ፈንድሻ ጋር ይፈካል። የየቀን ምኞቱ እዛው አልጋው ላይ እንድረሳው ወይ ትቼው እንድሄድ ወይም በእንክብካቤ ፈንታ ባንገላታው እንደሆነ አውቃለሁ።
በጤነኛ ዘመኑ ከሚያገኘው እንክብካቤ አንዳች አላጎልበትም እንደውም እንደ ሰሞንኛ ሙሽራ አቀበጥኩት እንጂ! አሁንም ፈጣሪ ይሁን ሰይጣን ሲቀጡት አጓጉል አድርገውት እንጂ በጤነኛ ዘመኑ በየቀኑ ማታ አጅበውት የሚመጡትን ለዛዛ ሴቶች ሁላ አመጣለት ነበር። የሚታገዝ ቢሆን እኔ መኝታ ቤት የሚሰማኝን ሴቶቹን የሚያስጮሃቸውን ልፋቱን እያገዝኩት አስከውነው ነበር። አለመታደሉ እንኳን ለጉድጉድ ለመሽናቱም በድጋፍ ሆነበት።
«እሺ ምን ብሰጥሽ ትተይኛለሽ? ከውላችን በተጨማሪ ባንክ ያለኝን ገንዘብ ልስጥሽ ተይኝ!» አለኝ ምግቡን አብልቼው እንደጨረስኩ።
ውላችን ያለው ስንጋባ ያስፈረመኝን ነው። ከኔ በፊት እንዳገባቸው ሁለት ሚስቶቹ እኔንም 8 ዓመት አብሬው ከኖርኩ የንብረቱ ተካፋይ እንደምሆን ፣ ከዛ ቀድሜ መለያየት ካማረኝ ቤሳቤስቲን እንደማላገኝ አስፈርሞኛል። እንደቀደሙት ሚስቶቹ ጨርቄን ማቄን ሳልል በአንዱ ቀን ብን እንደምል እርግጠኛ ነበር።
«ወይ አለመታደልህ! እንዲህ ተይዘህም ገንዘብህ ሁሉን ነገር የመግዛት አቅም እንዳለው ነው የምታስበው?»
«እሺ ምንድነው የምትፈልጊው?»
«ለጊዜው ምንም! ፍቅሬን መንከባከብ!» አልኩት ፈገግ ብዬ ጉንጩን እየዳበስኩት። ጥሎኝ ሊሄድ ተውተረተረ። የሚንቀጠቀጡ እጆቹ አስተካክለው የዊልቸሩን መንቀሳቀሻ ስላልተጫኑለት ስልኩ ሲጮህ እንደሚወራጨው ተወራጨ። ፈገግታዬን መደበቅ እያቃተኝ ረዳሁት!!
ዛሬ ላይ እንዴት ተገኘሁ? ይህችኛዋን እኔ አድርጎ እሱ በሰይጣናዊ እጁ አቡክቶ ሳያበለሻሸኝ በፊት እግዚአብሔር የሰራት እኔ ምን አይነት ነበርኩ?
አልጨረስንም ……………………………..


https://t.me/yemeri_terekoch
4.3K viewsedited  18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 04:53:34
ለፍልስፍና አፍቃሪዎች በሙሉ እነሆ ምርጥ ቻናል ተከፍቶላችዋል

@Zephilosophy
ፍልስፍና ለነፃ አስተሳሰብ
https://t.me/joinchat/RVzIu0-BTYG_XaN8

በዚህ ቻናል ከተለያዪ የአለም ዳርቻዎች የተነሱ የታላላቅ ፈላስፋዎች አስተሳሰቦች እና ፍልስፍናዎች ይቀርባሉ።ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ፤ ከሰሜን እሰከ ደቡብ የአለምን የአስተሳሰብ ኮምፓስ የቀየሩ ፈላስፋዎች እና ሃሳቦቻቸው ከየመፅሀፉ እየተጨለፉ ለናንተ ይቀርባሉ። ከሶቅራጥስ እስከ ኒቼ ፤ ከቡድሃ እስከ ኦሾ ፤ ከማርክስ እስከ ሌኒን አለም ላይ የማይፋቅ አሻራዎቻቸውን ያሳረፋ ሰዎች ፤ ከክርስትና እስከ ቡዲሂዝም ፣ከእስልምና እስከ ሂንዲይዝም ፣ከሶሻሊስት እስከ ካፒታሊስት በዘመናት ውስጥ የተፈጠሩ ሀይማኖቶች ፣ስርዓቶች ርዕዮተ ዓለሞች ሁሉ ይዳሰሳሉ። ለዓለም ያስገኙት ሞራላዊና መንፈሳዊ ትሩፋቶች ይወዳሳሉ። ታሪካዊ ህፀፆቻው ደግሞ ያለምህረት ይተቻሉ ፣ይወቀሳሉ።

ፍልስፍናን ከተደበቀችበት ጓዳ አውጥተን በአደባባይ እናሰጣታለን። ማህበረሰቡ የሚሳሳላቸው ባህሎቹ እና እምነቶቹ በነፃነት ይጠየቃሉ ፣ይመረመራሉ ይፈተናሉ። እንደ ጣት ቁስል የተፈሩ እውነቶች መሀረባቸው ይገለጣል። እንደ ማህበረሰብ በጉያችን የጋረድናቸው እባጮች የግንባር ስጋ ይሆናሉ።ከግለሰብ እስከ ቡድን ፤ከሀይማኖት እስከ ርዕዮተ -ዓለም
፤ ከኋለቀር ባህሎች እስከ ዘመናዊ ስልጣኔዎች ያለምንም ፍርሃት በግላጭ ይሞገታሉ፣ ይመረመራሉ፣ይጠየቃሉ ውስጣቸው የተደበቀው እውነት እስኪገለጥ ድረስ በአውድማው ላይ መንሽ እየተፈለገ ፍሬው ከገለባ ይለያል።
መንሻችን የሰላ አምክንዮዊ አእምሮ፣ የሰከነ የሞራል ልዕልና እና ንፁህ ሰዋዊ ህሊና ናቸው።

Join

@Zephilosophy
@Zephilosophy
3.5K views01:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 20:16:00 ጓደኛ
''''''''''''
የጭንቀቴ ሸክም
አላራምድ ብሎ፥ሲያስድኸኝ በዳዴ፤
የኑሮ ውጥረቷ
ላይታች ጠፍሮ፥አለምድ ሲል ሆዴ፤
"ምን ሆንክ?" በለኝና
ችግሬን አብርረው፥ተው አግዘኝ ጓዴ፤
ጭንቅህ ጭንቄ ይሁን፥መንገድህ መንገዴ!

ከአንድ ሆድ ባናድር
. . . ኖረን በአንድ መንደር፤
በአንድነት ገምደውን
. . . እምነትና ፍቅር፤
ዛሬ እንደ ባይተዋር
ችግሬን ታቅፌ ለምን ብቻ ልቅር?
.
ከየት ተደብቆ?
.
ላንተ መቼ ጠፍቶ
ውስጤን እያነበብክ፥በፊት ገፄ መድረክ፤
ዓይኔን ካየኃቸው
ከሊቅ እስከ ደቂቅ፥የለም የሚደበቅ፤
ክፍተትህን ልሙላ
ከጎኔ ሁንና፥ሸፍን የኔን ስንጥቅ፤
አንተም በኔ ፈንድቅ፤
እኔም በአንተ ልድመቅ..!

ላርም ስህተትህን
. . . የአይምሮህን ፍዳ፤
ጥረገው ሰንኮፌን
. . . ከህይወቴ ሜዳ፤
አይደለሁ የአዞ አልቃሽ
. . . አይደለህ እንግዳ...

ከጥንት ከበፊቱም
የህይወት ቀኖናን፥ከአስተምሮት ጓዳ፤
ንዋይ አሸንፎት
አሳልፎ ባይሰጥ፥ወዳጁን ባይከዳ፤
ከልቡ የመረጠው
ጓደኛው ነበረ፥ለኢየሱስ ይሁዳ!


አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
5.1K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 18:49:52
ዱአና ፀሎት
"""""""""""""""
አላህ የፈጠረኝ እኔም የሰላም ሰው፤
እግዜር የፈጠረህ አንተም የሰላም ሰው፤
ለምን ማን እንዳሻው?
ከልባችን ኩሬ ፍቅርን ያደፍርሰው፤
ለምን ማን እንዳሻው?
የእውነት ዋንጫችን ውሸት ይበርዘው፤
ለምን ማን እንዳሻው?
የእምነት ገመዱን ገዝግዞ ይበጥሰው፤
በል ክንዴን ተንተራስ
እኔም ተጠግቼ ክንድ'ን ልንተራሰው!

ተጣብቀን እንኑር
እቅፍ አርገኝ ጓዴ......
....... እቅፍ ላርግህ ጓዴ፤
እንዲህ ባንሆን ኖሮ
በኛ ደም ከባሪ ሊፈጀን ወንበዴ!

ማንም ከቀመረው
አንገት ብሎ ደፊ የነገር ካራቴ፤
ማንም የሆድ መሪ
ሰውነቴን ትቶ መድቦኝ በእትብቴ፤
በዘር ጎጥ ከፋፍሎ
የትብታቡን ገመድ ቢከተው ባ'ንገቴ፤
ዱአዬ ሸሸገህ
ፀሎትህ መሸገኝ
አወጣኝ እምነትህ አወጣህ እምነቴ!

አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)


@getem
5.9K viewsedited  15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-27 20:20:25
ለፍልስፍና አፍቃሪዎች በሙሉ እነሆ ምርጥ ቻናል ተከፍቶላችዋል

@Zephilosophy
ፍልስፍና ለነፃ አስተሳሰብ
https://t.me/joinchat/RVzIu0-BTYG_XaN8

በዚህ ቻናል ከተለያዪ የአለም ዳርቻዎች የተነሱ የታላላቅ ፈላስፋዎች አስተሳሰቦች እና ፍልስፍናዎች ይቀርባሉ።ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ፤ ከሰሜን እሰከ ደቡብ የአለምን የአስተሳሰብ ኮምፓስ የቀየሩ ፈላስፋዎች እና ሃሳቦቻቸው ከየመፅሀፉ እየተጨለፉ ለናንተ ይቀርባሉ። ከሶቅራጥስ እስከ ኒቼ ፤ ከቡድሃ እስከ ኦሾ ፤ ከማርክስ እስከ ሌኒን አለም ላይ የማይፋቅ አሻራዎቻቸውን ያሳረፋ ሰዎች ፤ ከክርስትና እስከ ቡዲሂዝም ፣ከእስልምና እስከ ሂንዲይዝም ፣ከሶሻሊስት እስከ ካፒታሊስት በዘመናት ውስጥ የተፈጠሩ ሀይማኖቶች ፣ስርዓቶች ርዕዮተ ዓለሞች ሁሉ ይዳሰሳሉ። ለዓለም ያስገኙት ሞራላዊና መንፈሳዊ ትሩፋቶች ይወዳሳሉ። ታሪካዊ ህፀፆቻው ደግሞ ያለምህረት ይተቻሉ ፣ይወቀሳሉ።

ፍልስፍናን ከተደበቀችበት ጓዳ አውጥተን በአደባባይ እናሰጣታለን። ማህበረሰቡ የሚሳሳላቸው ባህሎቹ እና እምነቶቹ በነፃነት ይጠየቃሉ ፣ይመረመራሉ ይፈተናሉ። እንደ ጣት ቁስል የተፈሩ እውነቶች መሀረባቸው ይገለጣል። እንደ ማህበረሰብ በጉያችን የጋረድናቸው እባጮች የግንባር ስጋ ይሆናሉ።ከግለሰብ እስከ ቡድን ፤ከሀይማኖት እስከ ርዕዮተ -ዓለም
፤ ከኋለቀር ባህሎች እስከ ዘመናዊ ስልጣኔዎች ያለምንም ፍርሃት በግላጭ ይሞገታሉ፣ ይመረመራሉ፣ይጠየቃሉ ውስጣቸው የተደበቀው እውነት እስኪገለጥ ድረስ በአውድማው ላይ መንሽ እየተፈለገ ፍሬው ከገለባ ይለያል።
መንሻችን የሰላ አምክንዮዊ አእምሮ፣ የሰከነ የሞራል ልዕልና እና ንፁህ ሰዋዊ ህሊና ናቸው።

Join

@Zephilosophy
@Zephilosophy
5.3K views17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ